Thursday, October 13, 2011

‹‹የተሐድሶ መናፍቃን ዘመቻ በኢትዮጵያ ቤተክርስትያ ላይ››

ቤተ ክርስቲያናችን በተለያዩ ዘመናት ከደረሱባት መከራዎችና ስደቶች ተርፋ ለዚህ ትውልድ የደረሰችው በጠንካራዎቹ አባቶቻችን ተጋድሎና በደሙ በመሠረታት በመድኃኒተ ዓለም ክርስቶስ ቸርነት እንደሆነ አባቶቻን ያስተማሩን የታሪክ እውነት ነው፡፡ የግራኝ አህመድን ሰይፍ፤ የዮዲትን እሳት፤ የነአልፎንሱ ሜንዴዝና ተከታዮቹን ቅሰጣ አልፋ እነሆ ለእኛ ደርሳለች፡፡ ተጋድሎ ለቤተ ክርስቲያን የተሰጣት ጸጋ ነውና አባቶቻችን ያለፉበት መከራ ዛሬም መልኩን ቀይሮ መከሰቱ አልቀረም. .. . ‹‹ተሐድሶ››

እንደ እግዚሐብሔር መልካም ፍቃድ ማህበረ ቅዱሳን በተሐድሶ ዙሪያ ያዘጋጀውን ‹‹የተሐድሶ መናፍቃን ዘመቻ በኢትዮጵያ ቤተክርስትያ ላይ›› መፅሀፍ ስካን አድርገን በpdf መልክ መፅሀፉን አግኝተው ማንበብ ላልቻሉ ሰዎች ራሳቸውን ፤ ቤተሰባቸውን እና ቤተክርስትያንን ነቅተው እንዲጠብቁ ብሎጋችን ላይ የምናቀርብ መሆኑን ቃል ገብተን ነበር:: እነሆ ማንበብ ፈልጋችሁ መፅሀፉን ላላገኛችሁ አገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ ላላችሁ ምዕመናን በpdf መልክ አዘጋጅተንላችዋል በማስተዋል ያንብቡት፡፡

‹‹ራስዎን ቤተሰብዎን በአጥቢያዎ የምትገኝውን ቤተክርስትያንን ከተሐድሶና ከመናፍቃን እንቅስቃሴ ነቅተው ይጠብቁ››
አርዕስት፡-‹‹የተሐድሶ መናፍቃን ዘመቻ በኢትዮጵያ ቤተክርስትያ ላይ››
አዘጋጅ፡- የማህበረ ቅዱሳን ዶክመንቴሽን ክፍል
የታተመበት ጊዜ፡- ሚያዚያ 2003
የገፅ ብዛት:- 103
Soft Copy Size:- 20 MB
ዋጋ:- 15 ብር
‹‹እኛ ይህን መፅሀፍ እርስዎ ጋር በማድረስ ሀላፊነታችንን ተወጥተናል እርስዎ ላላነበቡት እንዲያነቡት በማድረግ ሃላፊነትዎን ይወጡ፡፡››
To Read in Pdf Click here


To Download By Pdf Click here
ሌሎች ስለ ተሐድሶና መናፍቃን እንቅስቃሴ የተፃፉ መፅሀፍትን ለማውጣት በዝግጅት ላይ እንገኛለን፡፡
‹‹የመረጃ ምንጭዎ ሆነን እንሰራለን››
‹እግዚሐብሔር ቤተክርስትያንን ይጠብቅ››

2 comments: