Wednesday, February 12, 2020

ጎጠኞች ቤተ ክርስቲያንን ካቆሰሏት በላይ ያቆስሏት ዘንድ ዕድል አይሰጣቸው!!


የኦሮሚያ ቤተ ክህነት አደራጅ ኮሚቴ ብሎ ራሱን የሾመው አካል በከፍተኛ የመተማመን ወይም የመቅበዝበዝ ስሜት ውስጥ ሆኖ እንደሆነ ግራ በሚገባ መልኩ አስቸኳይ የሲኖዶስ ስብሰባ መጠራቱ ከተነገረበት ጊዜ ጀምሮ እየፎከረ ነው፡፡ ቀሲስ በላይ ከአሜሪካእስኪ ውግዘቷን ይሞክሯትና እንታያያለንሲል ኃይለ ሚካኤል ደግሞ ከሀገር ቤት በተደጋጋሚ የቀጥታ ሥርጭት እየገባ ለሰኞ የተጠራውን የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤእናንተ ፖለቲከኞች ለፖለቲካችሁ ስትሉ ነው የጠራችሁት፣ ብታርፉ ይሻላል፣ ጉባኤው የጉባኤ ከለባት (የውሾች ጉባኤ) እንዲሆን አንፈልግም፣ ቄሮና ቀሪቲ ለሁሉም ነገር ራሳችሁ አዘጋጁበማለት ከወዲሁ ጉባኤውን ዘልፎ፣ ነቅፎና አውግዞ ይባስም ብሎ ውሳኔውን በአመፃ ለመመለስ የራሱን ሠራዊት አሰልፎ እየጠበቀ ይገኛል፡፡

Tuesday, February 11, 2020

ቅዱስ ሲኖዶስ ቤተ ክርስቲያን ጥቃት ላይ መኾኗን ያውጅ !

ዲያቆን አባይነህ ካሴ
(አንድ አድርገን 02/6 2012 ዓ.ም):-  ለየካቲት ቀን ፳፻፲፪ .. አስቸኳይ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ጥሪ መቅረቡን ከሲኖዶሱ ዋና ጸሐፊ ከአቡነ ዮሴፍ ከተሰጠው መግለጫ ለማወቅ ተችሏል፡፡ አስቸኳይ ጉዳይ ሲገጥም እንዲህ መፋጠን ይገባልና በአክብሮት ተቀብለነዋል፡፡ ጉባኤው ከመሰብሰብ ባሻገር ጠልቆ ይመለከታል ብለንም ተስፋ እናደርጋለን፡፡

ቅዱስ ሲኖዶስን በተመለከተ ሁሉም ኦርቶዶክሳዊ የሚግባባበት አንድ ጉዳይ አለ፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ ይወሥናል አፈጻጸሙን ግን አይመረምርም፡፡ ለዚህም ምክንያቱ እና መፍትሔው ምን እንደኾነ ብዙ ጊዜ ስንወተውት ቆይተናል፡፡ አሁንም የአስቸኳይ እና የመደበኛ ስብሰባ ሸብረብ እንጅ የወሠናቸው ጉዳዮች ከምን እንደደረሱ፣ ምን እንቅፋት እንደገጠማቸው፣ ምን ዓይነት ማረሚያ እንደሚሹ በጥሞና ለመመልከት ትዕግስቱ ሊኖረው ካልቻለ ከጉባኤው ማግሥት ታላላቆቹ አጀንዳዎቹ ሁሉ ውኃ ይበላቸዋል፡፡

ለአንዱ ቦታ እያመቻቹ ሌላውን በራሱም ቦታ ማንገላታት

(በዲ/ን ብርሃኑ አድማስ)
(አንድ አድርገን 02/6 2012 ዓ.ም):-  መምህር ምሕረተ አብን ለማስደንገጥም ይሁን ጉባኤዎችን ለመረበሽ ትላንት ማታ እንደተደረገ የሰማሁት ነገር ብዙ ነገር የሚጠቁም ነው። ሰሞኑን ወንድሞቻችን ሰማዕትነት የተቀበሉበትና አዲስ ቤተ ክርስቲያን የፈረሰበት 24 ቀበሌው ቦታ ያን ሁሉ መዓት ያመጣው ፓስተር ዮናታን ቦታውን እርሱ እመራዋለሁ ለሚለው የመልካም ወጣት ፕሮጄክት በጠየቀው መሠረት ለማስረከብ በጥድፊያ ላይ ስለነበሩ ነው።

ምሕረት የምሕረት ወንጌል ስባኪ እንጂ ፥የወንጀል ስባኪ አይደለም !!


(በዲ/ን ታደሰ ወርቁ)
(አንድ አድርገን 02/6 2012 ዓ.ም):- ወንድማችን መምህር ምሕረተ አብ አሰፋ በእጁ የያዘው የፍቅር እና የስማዕትት ትእምርት የሆነውን ጧፍ እንጂ፥ጎመድና ሰይፍ አይደለም። ከአንደበቱ የሚወጣው ቃል እግዚአብሔር እንጂ ጥላቻና ልዮነት አይደልም። ዘመኑን ለቤተ ክርስቲያን ዘመነ ሰማዕታት ያድረጉባትን እንደ ጃዋር መሐመድ እና እንደ አህመዱን ጀበል ዐይነቱን የስይፍና የጎመድ፤ የሀገራዊ ልዮነትና ጥላቻ፤ የቤተ እምነቶች መቃቃሪያና መጠያያ ምንጮችና የአስተሳስብ አባቶችን የሚከባከብ ፖሊስ ፥መምህራችንን አይደለም የማዋከብ፥ ጠርቶ የማናገር የሞራል እና የሕግ መሠረት የለውም።እገሌ ያስተምር፤ እገሌ አያስተምር የማለት ሙሉ ሥልጣን የኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን እንጁ፥የፖሊስ አይደለም

ቅ/ሲኖዶስ አስቸኳይ ስብሰባ ጠርቷል።


(አንድ አድርገን 02/6 2012 ዓ.ም)  :-የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ በወቅታዊ የቤተ ክርስቲያኒቱ ጉዳዮች ላይ ለመነጋገር ለየካቲት 9 ቀን 2012 . አስቸኳይ የስብሰባ ጥሪ ማድረጉን ቋሚ ሲኖዶስ አስታውቋል። አስቸኳይ ጉዳይ ካልገጠመው በስተቀር የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ (ጥቅምት እና ግንቦት) የሚካሄድ እና በቤተክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ሰጪ አካል ነው። ኦርቶዶክሳውያን የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ምልዐተ ጉባኤ በሚከተሉት አንኳር ጉዳዮች ላይ እንዲመክር እና ቁርጥ ውሳኔ እንዲያሳልፍ ይጠብቃሉ።