Monday, April 30, 2012

" ከሀይማኖት ወዲያ ምን አለ፣ ለሀይማኖት መሞት ጽድቅ ነው።" የገዳሙ አባቶች

  •  በሺዎች የሚቆጠሩ የሰሜን ጎንደር ነዋሪዎች ወደ ዋልድባ መጓዛቸውንነና "ሁለት ነጮች ተገድለዋል ሌሎች ሰራተኞች አካባቢውን ለቀው ወጥተዋል" ብሏል የኢሳት ዜና፤

(ደጀ ሰላም፤ ሚያዚያ 23/2004 .ም፤ April 30/2012 )፦፦ "በሺዎች የሚቆጠሩ የሰሜን ጎንደር ነዋሪዎች ወደ ዋልድባ መትመማቸውን እንዲሁም ሁለት ነጮች መገደላቸውን፣ ሌሎች ሰራተኞች አካባቢውን ለቀው መውጣታቸውን" ኢሳት የተባለው ብቸኛው ከአገር ውጪ የሚገኝ ነጻ የዜና ተቋም በሚያዚያ ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፬ / ዘገባው አስታወቀ። "የገዳሙ አባቶች ለሰሜን ጎንደር ነዋሪዎች ባቀረቡት ጥሪ መሰረት እስከ 200 ኪሎ ሜትር ርቀት የሚገኙ የሰሜን ጎንደር ነዋሪዎች ወደ አካባቢው መትመማቸውን ተከትሎ ሁለት ነጮች መሞታቸውን፣ ሌሎች ሰራተኞች ደግሞ እኛ ከህዝብ ጋር አንጣላም በማለት አካባቢውን ለቀው ወጥተዋል" ያለው ዜና ተቋሙ "የሟቾቹ እና አካባቢውን ለቀው የወጡት ነጮች ምዕራባውያን ይሁኑ የቻይና ዜጎች አልታወቀም" ሲል አክሏል።

በዋልድባ ገዳም ከ4 በላይ ፌደራል ፖሊሶች በጅብ ተበሉ


( አንድ አድርገን ሚያዚያ 23 2004ዓ.ም)፡-በዋልድባ ገዳም በጥበቃ ላይ የሚገኙ ከ4 በላይ ፌደራል ፖሊሶች በጅብ ተበልተዋል ፤ ይህ ሶስተኛው ምልክት እንጂ የመጨረሻ አይደለም ፤ ይህ ጉዳይ ቦታው ላይ የሚገኙትን ፌደራል ፖሊሶች ጭንቀት ላይ ጥሏቸዋል ፤ ከፍተኛ ውጥረትም ነግሷል ፤  ቀጥሎ ማን እንደሚጎተት ስላላወቁ በሁኔታው እንቅልፍ አልወስድ ያላቸው ፌደራል ፖሊሶች በዝተዋል ፤ ለዚህ ሁሉ ነገር ተጠያቂ ግን መንግስት ነው ፤ በየጊዜው ለስራ ወደ ዋልድባ እየተላኩ ያሉ ባለሙያዎች እየታመሙ ይገኛሉ ፤ ስራውን የሚሰሩ መኪኖች እየተበላሹ ይገኛሉ ፤ በተጨማሪ አንድ አካባቢ የሚገኙ የማህበረሰቡ አባላት ስራው አይሰራም በማለት ስራውን ለ2 ቀናት ማስቆም ችለዋል ፤ ወደፊትም ከአካባው ይነሳሉ የተባሉት 8ሺህ አባዎራዎች መነሳታቸው አጠራጣሪ እየሆነ ይገኛል ፤ በማለት ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል::

ምላካችን ታጋሽ ነው ፤ ‹‹እግዚአብሔር መሐሪ፥ ሞገስ ያለው፥ ታጋሽም፥ ባለ ብዙ ቸርነትና እውነት፥ እስከ ሺህ ትውልድም ቸርነትን የሚጠብቅ፥ አበሳንና መተላለፍን ኃጢአትንም ይቅር የሚል፥ በደለኛውንም ከቶ የማያነጻ፥ የአባቶችንም ኃጢአት በልጆች እስከ ሦስትና እስከ አራት ትውልድም በልጅ ልጆች የሚያመጣ አምላክ›› ኦሪት ዘጸአት 346 የምትሰሩት ስራ ከእርሱ የተደበቀ ሆኖ አይደለም ፤ ትንቢተ ኤርምያስ 17፤10 ላይ ‹‹እግዚአብሔር ለሰው ሁሉ እንደ መንገዱ፥ እንደ ሥራው ፍሬ እሰጥ ዘንድ ልብን እመረምራለሁ ኵላሊትንም እፈትናለሁ።›› ተብሎ ተጽፏል አንዳች ከእርሱ የሚደበቅ ስራ የላችሁም አሁንም ከስራችሁ ተመለሱ በተጨማሪ የዮሐንስ ራእይ 223 ላይ ‹‹ኩላሊትንና ልብን የምመረምር እኔ እንደ ሆንሁ ያውቃሉ፥ ለእያንዳንዳችሁም እንደ ሥራችሁ እሰጣችኋለሁ።›› ይላል ፡፡ 

በባቦጋያ ምስራቀ ፀሐይ ቤተክርስቲያን ለተፈጠረዉ ዉዝግብ በፍትሐብሔር ሕግና በቃለዓዋዲዉ አኳያ ሲታይ


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
በባቦጋያ ምስራቀ ፀሐይ ቤተ ክርስቲን ለጠፈጠረዉ ዉዝግብ መነሻ የሆነ በደብሩ የሰበካ ጉባኤ ተወካዮችና በአቶ ታዲዎስ ጌታቸዉ መካከል የተፈረመዉ ዉል በፍትሐብሔር ሕግና በሕገመንግስቱ እንዲሁም በቃለ ዓዋዲዉ ሲታይ
1.1 በፍትሐብሔር ሕግና ሕገ መንግስት ዉሉ ሲተነተን
የባቦጋያ ምስራቃ ፀሐይ መድሃኒአለም ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ ሰኔ 2/1999ዓ.ምያሳለፈዉን ዉሳኔ መሰረት ማድረግ ሰኔ 10/2000ዓ.ም በበጎ ፈቃደኝነት የተደረገ የዉል ስምምነት በሚል ርእሰ የኩሪፍቱ ሪዞርትና ስፖ ባለቤት ከሆኑት ከአቶ ታዲዎስ ጌታቸዉ ጋር ባደረጉት የመንደር ዉል የቤተ ክርስትያንቱን የመስቀልና የጥምቀት በዓላት ማክበሪያ የነበረዉን 13,020 ካሬ ሜትር ስፋት ያለዉን ፤ በስተ ደቡብ ከኩሪፍቱ ሐይቅ ጋር የሚዋሰነዉን ቦታ እንድታጣ አድርጓታል፡፡ይኼ በወቅቱ የደብሩ ሰበካ ጉባኤ አስተዳደርና በአቶ ታዲዎስ ጌታቸዉ መካከል የተደረገዉ ስምምነት ከኢትዮጵያ የፍትሐብሔርና ሕገመንግስት ሕግ ማእቀፍ ዉጭ የሆነ፣የስምምነቱ ርእሰ ጉዳይ ወይም የዉለታዉ ጉዳይ (object of the contract) ተለይቶ የማይታወቅ እና ይልቁንም በዉስጡ የተገለፀዉን ለአቶ ታዲዎስ የቤተ ክርስቲያንቱን መሬት በነጻ የመስጠትን ዓላማ ማረጋገጥ የማይቻል ሲሆን በአንፃሩ ቤተ ክርስቲያንቱ ሐይማኖታዊና ብሔራዊ በዓላቶቿን የምታከብርባቸዉን ቦታዎች ያለ አንዳች ጥቅም እንድታጣ ያደረገ እና የቢሾፍቱ ከተማን ማዘጋጀ ቤት በማወቅም ሆነ ባለማወቅ በቸልተኝነትም ይሁን ሆን ተብሎ ሕገ-ወጥ እና ኢ-ፍትሐዊ የሆነና የሚያስወቅስ ድርጊት እንዲፈፅም ምክንያት የሆነ ስምምነት ነዉ፡፡

Friday, April 27, 2012

‹‹ቤተክርስትያኒቱ አትዘጋም›› ያሉ 16 ክርስትያኖች ታሰሩ


ኢትዮጵያ ውስጥ ብሎጋችንን ለማንበበብ ይህን ሊንክ ይጠቀሙ


(አንድ አድርገን ሚያዚያ 19 ፤ 2004ዓ.ም)፡- የባቦጋያ መድሀኒአለም ቤተክርስትያን የቦታ ጉዳይ ለያዥ ለገናዥ እያስቸገረ ይገኛል ፤ አቶ ጌታቸው ዶኒ እንዳሰበው ነገሮች እየሄዱ አለመሆናቸውን ሲረዳ የቤተክርስትያኒቱን ቄሰ ገበዝ ትላንት አመሻሽ ላይ የመቅደሱን ቁልፍ ካለመጡ ብሎ ጠይቋቸው ነበር ፤ እርሳቸውም ‹‹አንተ ማነህና ነው የቤተክርስትያኒቱን ቁልፍ የምሰጥ ›› በማለት እምቢ ሲሉት ጉልበት ተጠቅሞ ቁልፉን እጁ ለማስገባት ሙከራ አድርጎ  ነበር ፤ ቄሰ ገበዙ የመቅደሱን ቁልፍ አልሰጥም በማለት ለአካባቢው ክርስትያኖች ስልክ ደውለው በአጭር ጊዜ ውስጥ ክርስትያኖቹ የተሰበሰቡ ሲሆኑ ከደቂቃዎች በኋላ ጌታቸው ‹‹አመጽ ለማስነሳት ሰዎች ተሰብስበዋል›› ብሎ በደወለላቸው ፖሊሶች አማካኝነት በጊዜው የነበሩትን 16 ክርስትኖችን  እስር ቤት ሊያስገቧቸው ችለዋል ፡፡ ከእነዚህ ውስጥም ሶቶች ጎልማሶችና ፤ ወጣቶች ይገኙበታል ፤  የእነዚህ ንጹሀን ክርስትያኖች  ተቃውሞ ‹‹አቶ ጌታቸው ዶኒ  የቤተክርስትያኒቱን ቁልፍ ለምን ይቀበላል ? ቁልፉን ተቀብሎ ከዚህ በፊት ሲናገር እንደነበረው የባቦጋያን መድሀኒአለም ቤተክርስትያን ለመዝጋት የሚያደርገውን ተግባር እንቃወማለን ፤ ›› በማለታቸው ነው ለእስር የበቁት፡፡

Thursday, April 26, 2012

የገዳማቱ ፤ የአድባራቱና የባቦጋያ መድሀኒአለም የመሬት ይዞታ ጉዳይ

ለወደፊት ኢትዮጵያ ውስጥ ብሎጋችንን ለማንበበብ ይህን ሊንክ ይጠቀሙ
  • 120 ገዳማትና አድባራት የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ተሰጣቸው
  • ጌታቸው ዶኒ ‹‹ቤተክርስትያኒቱን አዘጋለሁ›› በማለት ያበጠ ልቡን በአንደበቱ ሲናገር ለመስማት ተችሏል፡፡ 
(አንድ አድርገን ሚያዚያ 18 2004 ዓ.ም)፡- በአዲስ አበባ የሚገኙ 120 ገዳማትና አድባራት የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ተሰጣቸው፡፡በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት መጋቢ ካህናት ኃይለስሴ ዘማሪያም የማረጋገጫው ካርታ በተሰጠበት ወቅት እንደገለጹት ከመስከረም 9 1998 ዓ.ም በፊት የተሰሩት ገዳማትና አድባራ የጸበል ቦታዎች ፤ የመካነ መቃብር ፤ የበዓለ ጥምቀት ማበሪያ እና መሰል ስፍራዎች ሙሉ ይዞታቸውን ሳይቀነስ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ተዘጋጅቶላቸዋል፡፡

Tuesday, April 24, 2012

መንግስት ለምን ‹‹ማህበረ ቅዱሳንን›› ጥምድ አድርጎ ያዘው?

ይህ የአንድ ሰው ሀሳብ ነው ፤ የማንም አቋም አይደለም

(አንድ አድርገን ሚያዚያ 17 ፤ 2004 ዓ.ም )፡- መቼስ በባለፈው የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ንግግር ያልተናደደ ቢኖር ማህበረ ቅዱሳንን የማያውቅ ያለበለዚያ በተቃራኒ የቆመ ሰው ብቻ ነው ፤ ማህበሩ ወጥ የሆነ ተጠያቂነትና ግልጽነት ያለው ማህበር ነው ፤ እንደ ጠላት ተደብቆ ስራውን የሚሰራ መንፈሳዊ ተቋም አይደለም ፤ በርካታ በመቶ ሺዎች የሚቆጠር አባላት ያለው ፤ በተቻለው እና አቅሙ በፈቀደ መጠን ቤተክርስትያንን ለመርዳት ፤ የተዘጉትን ለማስከፈት ፤ የሰባኪ ወንጌል ችግር ያለባቸውን መምህር በመመደብ ፤ ለገዳማትና የተቸገሩ አብያተክርስትያናት ፕሮጀክት በመቅረጽ በቋሚነት የሚረዳ ፤ ምዕመኑ በመንፈሳዊ ህይወቱ ጠንካራ እንዲሆን የቤተክርስትያኒቱን መንፈሳዊ ትምህርት ከማስተማሩም በላይ በርካታ አሁን ዘርዝሬ የማልጨርሳቸውን ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነ የሚገኝ መንፈሳዊ ተቋም ነው ፤ ከወራት በፊት ዲ/ን ዳንኤል ክብረት በማህበሩ ላይ ያለው ተቃውሞ ባነሳበት ጊዜ የብዙዎች መነጋገሪያ ርዕስ መሆኑ የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነው ፤ ይህን የመሰለ አስቸጋሪ ሁኔታም ቢፈጠር ችግሮችን በመነጋገር መፍትሄ በመስጠት በችግር ጊዜ ጥንካሬውን አሳይቷል ፤ መንፈሳዊ ህይወትና ወንጌሉ እንደሚያዘውም በወንድሞች መካከል የተፈጠረውን ቅራኔ ይቅር በማስባባል ያጠፋው ይቅርታ እንዲል ፤ የተበደለውም ይቅርታውን እንዲቀበል አድርጓል ፤ እኛም በሁኔታዎቹ ብናዝንም በስተመጨረሻ ደስ ብሎናል ፤ ፈተና ተቋሙን በሚያናጋ መልኩ ከግለሰብ ሊነሳ ይችላል ፤ ከማህበሩን ከተቃራኒ መንገድ የቆሙ ሰዎች ሊነሳ ይችላል ፤ ከቤተክህነቱም ሊነሳ ይችላል ፤ ከመንግስትም ሊነሳ ይችላል  ፤ እንደ ባለፈው ሳምንት ደግሞ ከጠቅላይ ሚኒስትሩም ሊነሳ ይችላል ፤ ነገር ግን ፈተና በየጊዜው መፈጠሩ ሊያስገርመን አይገባም ፤በዮሐንስ ወንጌል 16፤33 ‹‹በእኔ ሳላችሁ ሰላም እንዲሆንላችሁ ይህን ተናግሬአችኋለሁ። በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዞአችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ።›› ተብሎ ተጽፏል ፡፡ ስለዚህ መከራም ይሁን ፈተና በጌታችን በመድሀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እናልፈዋለን እንጂ የሚመጣውን ፈተና ፈርተን ወደ ኋላ አንልም ፤ በፊትም ፈተና ነበር ፤ ዛሬም አለ ፤ ነገም የህይወትን መስዋእትነት የሚጠይቅ ፈተና ሊመጣ ይችላል ፤ ግን ሁሉም እንደ አመጣጡ ያልፋል፡፡

Friday, April 20, 2012

‹‹ደርግ VS ኢህአዴግ ›› የቤተክርስትያን ፈተና


ይህን ጽሁፍ ስታነቡ
‹‹አንድ አድርገን›› ብሎግ ኢትዮጵያ ውስጥ ይሰራል ማለት አይደለም  ፤ መረጃም ከናንተ ዘንድ ለማድረስ የሚገታን አንዳች ነገር ፤ የለም የምንጽፈው ጽሁፍ የምናስተላልፈው መረጃ ሰዎች ዘንድ እንዳይደርስ ተደርጓል

 
(አንድ አድርገን ሚያዚያ 16 ፤ 2004 ዓ.ም )፡- የኢትዮጵያ ቤተክርስትያን ክብር ባህል እምነትና ስርዓት መንግስትና ቋንቋ ያቋቋመች የማትናወጥ ከመሆኗ ጋር ከሔኖክ ፤ ከኖህ ፤ ከመልከ ጼዴቅ ከነብያትና ከሀዋርያት ተላለፈውን ትምህርት ስርዓት ፤ እምነት ከትውልድ ወደ ትውልድ ስታስተላልፍ የኖረች በማስተላለፍ ላይ ያለች ፎኖተ ህይወት መሆኗ የተረጋጠ ነው፡፡ ቅዱሳን አበውን ፤ ኃያላን ነገስታትን ፤ ልዑላን መሳፍንትን ፤ ክቡራን መኳንንትን ፤ ዐይናሞች ሊቃውንትን በስጋ በነፍስ ወልዳ ያሳደገች ፤ የሌላ የማትፈልግ የራሷ የማትለቅ ዕጥፍ እናት ፤ ስንዱ እመቤት ናት፡፡

Thursday, April 19, 2012

በዋልድባ መንግስት ሬሳ መልቀምን ተያይዞታል


(አንድ አድረገን ሚያዚያ 11 2004 ዓ.ም)፡- የዋልድባ ጉዳይን በቅርቡ በአካል ቦታው ድረስ ሄደው የተመለከቱት ሰዎች ምን አይነት ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ በጥቂቱም ቢሆን ያዩትንና የሰሙትን አካፍለውናል ፤ ቦታው በፖሊሶች እንደተከበበ ገዳሙ የጸሎት ቦታ መሆኑ የቀረ እስኪመስል ድረስ የጦር አውድማ በሚመስል መልኩ በታጠቁ ወታደሮች ተከቧል ፤ አበው መነኮሳቱን ከበአታቸውን እንደ ወንጀለኛ  በጠገበ ወታደር እያዳፉ ሲወስዷቸው በዓይናቸው ተመልክተዋል ፤ በተነሳ ጥያቄ መሰረት ጥይት ተኩሰውባቸዋል ፤ ስውራን አባቶችም እናንተ ባላችሁበት ጸልዩ በማለት ቦታው ላይ በተገኙ ወንድሞቻችን አማካኝነት ለእኛ መልዕክት አስተላልፈውልናል ፤ መንግስትስም ለፕሮጀክቱ መፋጠን መኪኖችን ወደ ቦታው እያመሩ መሆኑን ለማወቅ ችለናል ፤ ባለፈው ቅዳሜ 08-08-2004 ዓ.ም በቪኦኤ ላይ የገዳሙን አንድ አባት አግኝተው እንዳናገሯቸው መንግስት አሁንም አጠናክሮ ስራውን እየሰራ መሆኑን ለቪኦኤ አስረድተዋል ፤ በፊት ቃለ መጠይቅ ያደረጉት አባት አንዳች ስህተት እንዳልሰሩ የተናገሩት ሁሉ ትክክል እንደሆነ ተነግሯቸዋል ፤ ግን ምንም ማድረግ እንዳልቻሉ አክለው ገልጸዋል፡፡ ብጹእ አቡነ ጳውሎስና ጥቂት ጳጳሳት ለገዳሙ አባቶች ያልተከፈተ ጆሯቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሚሰጡት ወቅታዊ አስተያየት የላይኛውን የተወካዬች ምክር ቤት ወንበር ተቆናጥተውት በኢቲቪ ተመልክተናል ፡፡


Wednesday, April 18, 2012

ታሪክን የኋሊት ‹‹ለትግራይ ተወላጆች የቀረበ ጥሪ››


(አንድ አድርገን ሚያዚያ 11 ፤ 2004 ዓ.ም) ፡-  ቀኑ ህዳር 6 1985 ዓ.ም ነበር ፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ሰሜን አቅጣጫ በምትገኝው በመንበረ መንግስት ቁስቋም ቤተክርስትያን ብዙ ህዝበ ክርስትያን ተሰብስቧል ፡፡ ምክንያቱ በዓለ ቁስቋምንና የጾመ ጽጌን ፍቺ በዓል ለማክበር ነበረ ፡፡ የዕለቱም አስተማሪ አለቃ አያሌው ታምሩ ነበሩ፡፡ አለቃ ‹‹በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን›› ብለው ጀመሩ፡፡ በትምህርታቸውም ስለ እመቤታችን ስደት ፤ ስለ ቁስቋም ታሪክ ፤ ወደ እየሩሳሌም ስለ መመለሷ ፤ ከእመቤታችን 300 ዓመት በኋላ በግብጽ ስለተሰራው የመታሰቢያ ቤተክርስትያን ፤ በዚህ በዓል ምክንያት ኢትዮጵያውያን ነገስታትና ንግስታት ስላደረጓቸው መንፈሳዊ ተሳትፎዎች ፤ ስመ ጥሩዋ ኢትዮጵያዊት ንግስት እቴጌ ምትዋብ በጎንደር ስላሰሯት የደብረ ቁስቋም ቤተክርስትያን  ፤ ስለ ጾመ ጽጌ ፤ ስለ ማህሌተ ጽጌ በዝርዝር አስተማሩ፡፡ ከዚያም በመቀጠል ፤ በእመቤታችን በቅድስት ማርያምና በልጇ ስደት በረከትን ካገኙ የኢትዮጵያ አውራጃዎች አንዱ የሆነው ምድረ ትግራይ ከሌሎች ቅዱሳን የኢትዮጵያ መካናት ጋር የተጣመረ የታሪክ ተዛምዶ ያለው ከመሆኑ ባሻገር ከታቦተ ጽዮን ጀምሮ ለኢትዮጵያ ለተሰጡ ልዩ ልዩ ስጋዊ እና መንፈሳዊ በረከቶች ምንጭና ቦይ ሆኖ የኖረ ነው ፡፡ ዋልድባ ገዳምም ይህን መንፈሳዊ በረከት ከሚገኝባቸው ቦታዎች አንዱ ነው ፤  በአሁኑ ወቅት ህዝቡ የተሰጠውን  ስጋዊ ስልጣን አገሪቱንና ቤተክርስትያንን ከውድቀት ለማንሳት ሊሰራበት ይገባል፡፡ ይህ ሳይሆን ቀርቶ ህዝብና እግዚአብሔርን የሚያሳዝን ስራ ቢሰራ ግን ትዝብትና የታሪክ ተወቃሽነትን ያተርፋል ፤ ያለው ሰፊት ትምህርት ሰጥተዋል ፡፡(የአለቃ አያሌው ታምሩ የመንፈቅ መታሰቢያ ገጽ 26)

Tuesday, April 17, 2012

‹‹የማህበረ ቅዱሳን ተቃራኒ›› ማለት ምን ማለት ነው?

ይህ የግሌ አስተያየት ነው ፤ የማንም አቋም አይደለም
(አንድ አድርገን ሚያዚያ 10 2004ዓ.ም)፡- በትላንትናው ቀን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በምክር ቤቱ አባላት በተነሱላቸው ጥያቄዎች መልስ ሰጥተው ነበር ፤ ስለ ሀይማኖት አክራሪነት ላይ በተነሳው ጥያቄ ላይ በተነሳ ጥያቄ ላይ ውሀቢዝምን ካስረዱ በኋላ አንዳንድ የዚህ አይዲዎሎጂ ተከታይ የሆኑ ሰዎችን ‹‹የማህበረ ቅዱሳን ተቃራኒ›› በማለት መስለዋቸዋል ፤ ይህ ምን ማለት ነው? ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር የተረዱት ማህበረ ቅዱሳን የሀይማኖት አክራሪነት የሚያራምድ ማህበር አድርገው ነው የሚያስቡት ፤ ሰው ሀይማኖቱን ሲጠብቅ እንዴት አክራሪ ይባላል? ፤ ከአባቶች የተረከቡትን እምነታቸውን ለቀጣይ ትውልድ ለማስተላለፍ ስራ ቢሰሩ እንዴት የሀይማኖት አክራሪዎች ሊባሉ ይችላሉ ? ፤ ጠቅላይ ሚኒስትራችን የእውቀት ማነስ ከሌለብዎ በስተቀር ይህን ማለት ባልቻሉ ነበር ፤ እኔ በበኩሌ ወሀቢዝም የሚለውን አይዲዎሎጂ በመሰረቱ የገባዎት ራሱ አይመስለኝም ፤ አለማወቅ ሀጥያት አይደለም ነገር ግን አለማወቅን እንደ እውቀት ቆጥሮ ለኢትዮጵያ ህዝብ በምክር ቤቱ ተገቢ ያልሆነ አስተያየት መስጠት ተገቢ አይደለም ፤

ማህበራትና የቤተክርስትያን ፈተናዎች

…. በየጊዜው የተቋቋሙ መንፈሳዊ ማህበራት ለቤተክርስትያን ያመጡትን ጥቅምና ጉዳታቸውን ከወደፊት ስጋቶች ዳሰሳ ያደርጋል ፤ በአንድ ግለሰብ የተመሰረተን ማህበር ቤተክርስትያን ላይ ያሳደረው ተፅህኖ ያንብቡ

(አንድ አድርገን ሚያዚያ 9 2004ዓ.ም )፡- የቀለም ቀንዱ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ እንደተረጎሙት ማህበር ማለት ‹‹በቁሙ አንድነት ፤ ሸንጎ ፤ ብዙ ሰው ›› ማለት ነው ፡፡ በሌላም አተረጓጎም ‹‹ወገን ፤ ነገድ ፤ ቤተሰብ ፤ ጭፍራ ፤ ሰራዊት›› የሚል ትርጓሜ ተሰጥቶታል ፡፡ ጠቅለል ባለ መንገድ ማህበር አንድነትና ህብረትን የሚያመላክት ነገር ነው፡፡ ቤተክርስትያናችንም ወጣቶች በሰንበት ትምህርት ቤት ፤ አዛውንቶች ደግሞ በሰንበቴ ማህበራት በመታቀፍ አንድነታቸውን የሚፈጽሙበት ሁኔታ አመቻታላችዋለች ፡፡በዚህም ከ50 ዓመት በላይ ስትሰራበት ቆይታለች ነገር ግን ከ1980 ወዲህ ቤተክርስትያኗ አስቀድማ ካስቀመጠችው አወቃቀር የተለየ በተለየ በ1990 ዎቹ መጨረሻ የማበራት ቁጥር እጅግ እየበዛ መጣ፡፡

Monday, April 16, 2012

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ዋልድባን በማስመልከት ዛሬ ይተነፍሳሉ ተብሏል

(አንድ አድርገን ሚያዚያ 9 2004 ዓ.ም)፡- ክቡር የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በየጊዜው የመንግስታቸውን የስራ ክንውን እንደሚያቀርቡ ይታወቃል ፤ አብዛኛውን ጊዜ የሚቀርቡት ሪፖርቶች ወቅታዊ ነገሮችን የሚመለከቱ ናቸው ፤ ከወራት በፊት ስለተለያዩ ጉዳዮች ላይ መሰረት አድርገው ለምክር ቤቱ ያቀረቡት ሪፖርት ነበር (ስለ ኤርትራ ጉዳይ ፤ ስለ ባልደረባችን ‹‹ኑሮ ውድነት›› ፤ ስለ ነገ ህልማችን ትራንስፎርሜሽን …… etc) ፤ አሁን ባለንበት ጊዜ በርካታ አነጋጋሪ ነገሮች በሀገሪቱ ላይ ተከስተዋል የመጀመሪያው ቀድሞ የተጀመረው እንቅስቃሴ የሙስሊሞች ‹‹መጅሊስ ይውረድ ፤ ያልመረጥነው መጅሊስ እኛን አያስተዳድርም›› የሚል ሲሆን ነገሩ ለወራት ተንከባሎ ባለፈው የካቲት 26 የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር አማካኝነት ጉዳዩን ለዘብ የሚያደርግ መልስ ተሰቷቸዋል ፤ መንግስት በሰጠው መልስ ‹‹ ህጋዊ መጅሊስ ለመምረጥ ጊዜ ይጠይቃል እና ጥያቄያችሁን ተቀብለናል ነገር ግን በትእግስት ጠብቁ››የሚል ነበር ፤ ትእግስት እስከ መች እንደሚያስቆይ ባናውቅም ፤

Thursday, April 12, 2012

በሁለት ሱባኤ ሁለት መንግስት የገለበጡ አባት

(አንድ አድርገን ሚያዚያ 4 2004 ዓ.ም)፡- የልጅነት እድሜ ስማቸው ናዚር ጋይድ ሩፋኤል ፤ የጉልምስና እድሜ የሶሪያ አባ አንቶኒዮስ በኋላም ጵጵስናን ሲቀቡ ሺኖዳ ሳልሳዊ  ተባሉ፡፡ የግብጽ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ሊቀ ጳጳስ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ የልጅነት የጉልምስናና የእርጅና ዘመናቸው ያለ ድካም አገልግለው በ88 ዓመታቸው ጉልበታቸው ደክሞ ፤ ጤናቸው ታውኮ ህልፈታቸው ሆነ፡፡ በህልፈታቸው የአሌክሳንድርያ ኮፒቲክ ኦርቶዶክስ ዕምነት ተከታይ ብቻ አይደለም ያዘነው ፤ የግብጽም ህዝብ ብቻ አይደለም ያዘነው ፤ የክርስትያን እምነት ተከታይ ብቻ አይደለም ያዘነው በአቡኑ ሞት ዓለም ሁሉ አዝኗል፡፡  ጌታችን በወንጌል ‹‹በኋላዬ ሊመጣ የሚወድ ቢኖር፥ ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ።›› የማርቆስ ወንጌል 834 እንዳለ ይህን ቃል መሰረት በማድረግ ህይወት ዘመናቸውን በታማኝነት መስቀሉን ተሸክመው ተከትለዋል ፤ ‹‹ መልካሙን ገድል ተጋድዬአለሁ፥ ሩጫውን ጨርሼአለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤ ወደ ፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል፥›› 2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 4፤ 7-8 በማለት እኛን ልጆቻቸውን ከተለዩን ሳምንታት ተቆጥረዋል ፤ በህይወት ዘመናቸው ሳሉ ያለፉበትን መንገድ ለእኛ አሁን ላለንበት ጊዜ ትምህርት ከሆነን ብዬ በማሰብ ዞር ብየ ለመቃኝት ወደድኩኝ፡፡ ቤተክርስትያናቸው ፈተናዋን እንደ አባትነት ከእግዚአብሔር ጋር እንዴት መወጣት እንደቻሉ ከእኛ ጋር በጥቂቱ በማቆራኝት ፅፌአለሁ፡፡

Tuesday, April 10, 2012

‹‹ማኔ ቴቄል ፋሬስ›› ብሎ የሚፅፈው ጣት ቀርቧል

(አንድ አድርገን ሚያዚያ 2 2004 ዓ.ም)፡
የመቅደሱንም ዕቃዎች በፊትህ አመጡ፥ አንተም መኳንንትህም ሚስቶችህም ቁባቶችህም የወይን ጠጅ ጠጣችሁባቸው ከብርና ከወርቅም ከናስና ከብረትም ከእንጨትና ከድንጋይም የተሠሩትን የማያዩትንም የማይሰሙትንም የማያውቁትንም አማልክት አመሰገንህ ትንፋሽህንና መንገድህን ሁሉ በእጁ የያዘውን አምላክ አላከበርኸውም።  ስለዚህም እነዚህ የእጅ ጣቶች ከእርሱ ዘንድ ተልከዋል ይህም ጽሕፈት ተጽፎአል። የተጻፈውም ጽሕፈት። ማኔ ቴቄል ፋሬስ ይላል። የነገሩም ፍቺ ይህ ነው ማኔ ማለት፥ እግዚአብሔር መንግሥትህን ቈጠረው ፈጸመውም ማለት ነው። ቴቄል ማለት፥ በሚዛን ተመዘንህ፥ ቀልለህም ተገኘህ ማለት ነው። ፋሬስ ማለት፥ መንግሥትህ ተከፈለ፥ ለሜዶንና ለፋርስ ሰዎችም ተሰጠ ማለት ነው። የዚያን ጊዜም ብልጣሶር ለዳንኤል ሐምራዊ ግምጃ እንዲያለብሱት፥ የወርቅ ማርዳም በአንገቱ ዙሪያ እንዲያደርጉለት አዘዘ በመንግሥትም ላይ ሦስተኛ ገዥ እንዲሆን አዋጅ አስነገረ። በዚያ ሌሊት የከለዳውያን ንጉሥ ብልጣሶር ተገደለ። ሜዶናዊውም ዳርዮስ መንግሥቱን ወሰደ ዕድሜውም ስድሳ ሁለት ዓመት ነበረ። ትንቢተ ዳንኤል 5 23-31

Monday, April 9, 2012

በዋልድባ የመጀመሪያው ምልክት


(አንድ አድርገን ሚያዚያ 1 ፤ 2004 ዓ.ም)፡- ዋልድባ ላይ የሚሰራው ስኳር ፋብሪካ ውዝግቡ ያለ መፍትሄ እንደቀጠለ ነው ፤ መንግስት አልደረስኩም በማለት ስራውን እያከናወነ ይገኛል፤ አባቶችም በጸሎት እየበረቱ ይገኛሉ ፤ አሁን በደረሰን መረጃ መሰረት  በቦታው ላይ ያለው ስራውን የሚያከናውን ተቀጣሪ መሃንዲስ ባልታወቀ ምክንያት ሞቷል ፣ ስው ለመስራት የተቀመጡ  ኮንስትራክሽን ማሽነሪዎቹ በየሰአቱ እየተበላሹ ይገኛሉ ካልታወቀ ቦታ የተለያዩ አውሬዎች እየወጡ ሰራተኛውን መተናኮል ጀምረዋል ፣እነዚህን እና የመሳሰሉት መከራዎች በቦታው በስራ ላይ በስራ በሚገኙ ሰዎች ላይ እየደረሰ ነው፡፡