Friday, May 30, 2014

የቤተ ክህነቱ ጨለምተኛ ምሁራዊ ድባብ ፡ Cynical Intellectual Atmosphere

                                                              
                                                              በታደሰ ወርቁ ተጻፈ
  • ዛሬ ሊቃውንቱ የቤተክርስቲያኗ መቁሰል አልታይ ብሏችዋልና ቤተክርስቲያን አለቃ አያሌውን ከሙታን መንደር ትጣራለች፡፡

(አንድ አድርገን ግንቦት 23 2006 ዓ.ም)፡- በዚህ ዐውድ(Context)ምሁር የምለው ከቤተ ክርስቲያኒቱ የአብነት ትምህርት ቤቶች ሊቅነታቸውን ያስመሰከሩ ፤ ከመንፈሳዊ ኮሌጆች የተመረቁ እንዲሁም በቤተ ክርስቲያኒቱ ዙሪያ ጥናትና ምርምር አድርገው የጥናት ወረቀቶቻቸውን ያበረከቱ ፤ መጻሕፍትን ያሳተሙትን ጭምር ነው፡፡ በጥቅሉ በቤተ ክርስቲያኒቱ በአዕምሮ ሥራ ላይ የተሰማሩትን ነው፡፡

በዚህ መልኩ ያስቀመጥናቸው ሊቃውንት ቁጥር በአንጻራዊነት እያደገ ቢሄድም በቤተ ክርስቲያኒቱ እና በምእመኑ ውስጥ ቀድሞ የነበራቸው ቦታና የኑሮ ደረጃ በማሽቆልቆል ላይ ይገኛል፡፡ አንዳንዶቹም ሊቃውንት በቤተ ክርስቲያኒቱ  አገልግሎታቸውን እየሰጡ ቢሆኑም  በአሁን ጊዜ በቤተ ክርስቲኒቱ ውስጥ እንደሚታየው የቀድሞውን የመንፈስ ልዕልና እና ሐሳባዊ መሪነት አጥተዋል፡፡ ለመኖር የሚያስፈልጋቸውን ከማድረግ በተረፈ ምሁር የሚያሰኛቸውን ተግባር የሚፈጽ አሉ ብሎ ለመናገር አያስደፍርም፡፡

Thursday, May 29, 2014

የቅዱስ ሲኖዶስ “ሰብኣዊ ገጽ”


በታደሰ ወርቁ ተጻፈ
(አንድ አድርገን ግንቦት 21 2006 ዓ.ም)፡- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በኦሪት የታዘዘውን ፤ በወንጌል የተፈጸመውን መሠረታዊና አማናዊ ሕግ በተገቢው መልኩ ስትፈጽም ቆይታለች፡፡ በዚህ አግባብም ካህናቷንና ምዕመኗን  ለዘመናት ስታስተዳድር ቆይታለች፡፡ዐይነተኛ አገልግሎቷም እስከ ዘመናችን ድረስ ጉልህ ሆኖ ይታያል፡፡

ቤተ ክርስቲያኒቱ በየጊዜው የደረሰባት መስክ ወለድ ትግልና ድካም አሸንፋ ፤ መንፈሳዊ አገልግሎቷ እስከ ጽንፍ ኢትዮጵያ እና ዓለም ዳርቻ ሲሰማና ሲነገር ፤ ሲመለክና ሲከበር የኖረው ሰብኣዊ ገጻቸውን በሃይማኖት ገጽ ልዕልና ባሸነፉ አባቶቿ ነጻ ፤ ጠንካራ እና ቆራጥ አመራር ነው፡፡የቤተ ክርስቲያኒቱ ዐይናማ ሊቃውንት ሰብኣዊ ገጻቸውን በመንፈስና በሞራል ልዕልና ገርተው ለአንድ ሺህ ስድስት መቶ ዓመታት ቤተ ክርስቲያቱን ተጭኗት የነበረውን የግብጻውያንን ቀንበር በማወገድ “ለአንዲት ነጻ አገር አንድ ፓርላማ እንዳላት ሁሉ ለአንዲት ነጻ ቤተ ክርስቲያን አንድ ቅዱስ ሲኖዶስ ብቻ” በሚል የራሷ ቅዱስ ሲኖዶስ እንዲኖራት አስችለዋታል፡፡

‹‹ቤተ ጊዮርጊስ›› ከዓለም 19 አስደናቂ ቦታዎች አንዱ ሆነ



(ሪፖርተር ግንቦት 20 2006 ዓ.ም)፡-  በቅዱስ ላሊበላ ከተማ የሚገኘው ቤተ ጊዮርጊስ ውቅር ቤተ ክርስቲያን በዓለም ላይ ካሉ እጅግ አስደናቂ የተቀደሱ ሥፍራዎች ውስጥ ተካተተ፡፡

በቅርቡ ሀፊንግተን ፖስት ባወጣው መረጃ መሠረት፣ በዓለም ላይ ካሉና የተመልካችን ቀልብ ገዝተው ከተገኙ 19 ቦታዎች ውስጥ ቤተ ጊዮርጊስ አንዱ ሆኗል፡፡ 12ኛው መቶ ክፍለ ዘመን (800 ዓመታት በፊት) በአፄ ላሊበላ ከተሠሩት 12 ውቅር አብያተ ክርስቲያናት አንዱ የሆነው ቤተ ጊዮርጊስ፣ ከሌሎቹ በተለየ በተደጋጋሚ በጎብኚዎች ፎቶግራፍ የተነሳ ሲሆን፣ የበርካታ ቱሪስቶች መዳረሻ በመሆን ከተቀሩት አብያተ ክርስቲያኖች የበለጠ ዝናን የተቀዳጀ ነው፡፡

Wednesday, May 28, 2014

ወርሀ ግንቦት ……….1983 ዓ.ም

  • ደርግ ለ17 ዓመት ብዙ ግፍና በደል ያደረሰባትን ቤተ ክርስቲያንን  በ1983 ዓ.ም ግንቦት ወር ላይ ምህላ እንድታደርግ  በደብዳቤ  ቤተክህነቱን  ጠይቆ ነበር፡ 

(አንድ አድርገን ግንቦት 20 2006 ዓ.ም)፡-  በቀደምት  አባቶቻችን  ዘመን  እንኳን  በሃገሪቷ  ለየት  ያለ ክስተት ፤ ረሃብ ፤ ቸነፈር ፤ ጦርነት  ሲነሳ  ቤተ ክርስቲያን  አዋጅ አውጃ  ጸሎት  ምህላ ታደርግና በረከትን ከእግዚአብሔር ከአምላካችን ታሰጠን እንደ ነበር በቀደምት ዘመና የተጻፉ ድርሳናት ይናገራሉ፡፡ ከ23 ዓመት በፊት በ1983 ዓ.ም በወታደራዊው መንግስት መጨረሻ  የስልጣን  ቀናት ህዝቡ  ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ  ወድቆ  ነበር፡፡  እያንዳንዱ  ቀን ሊያስከትል የሚችለው ነገር ፤ ይዞት የሚመጣውን እልቂት እና ችግር ማንም እርግጠኛ  ካለመሆኑ ጋር አንዱ ካንዱ ይሻላል  ብሎ ሊመርጣቸው ከማይችል  ከሁለት ኀይሎች  ጋርም  የተፋጠጠበት ወቅት ነበር ፡፡  በአንድ በኩል  ‹‹አለሁ አልሞትኩም›› እያለ የሚፎክረው  ወታደራዊ  መንግሥት  በሌላ በኩል  ደግሞ  ወደ ፊት  እየገፋ  የነበረው  ተቃዋሚ  ኃይል አካሄድ ብዙ ግልጽ  ስላልነበረ በወቅቱ የህዝቡን  ጭንቅ ይበልጥ አብሶት ነበር፡፡ 

ቀሲስ ዶክተር መምህር ዘበነ ለማ













 . .  እንኳን ደስ ያለዎት . . . 

‹‹በአሁኑ ሰዓት ከራሱ ከባለቤቱ በቀር ይህቺን ሃይማኖት የሚያጸናት ፤ ይህቺንም ቤተ ክርስቲያን የሚታደጋት አካል የለም›› መምሕር ተስፋዬ

 (አንድ አድርገን ግንቦት 20 2006 ዓ.ም)፡-
ዕንቁ፡- ሁሉም ሰባኪን ወንጌል መንፈሳዊ ጥሪ ተደርልኝ  ጸጋ ተሰጥቶኝ ነው ሲሉ ይስዋላሉ፡፡ ተግባራቸው ግን ይህንን አይገልጽም ፡፡እውተኛ ጥሪና ጸጋ እንዴት ይታወቃል ?

መምሕር ተስፋዬ፡- እግዚአብሔር የሚያመሰግነው እንጂ ራሱን የሚያመሰግን ሁሉ እርሱ ተፈትኖ አይወጣም ተብሎ በመጽሐፍ ተጽፏል፡፡ የሃሳውያን መታወቂያቸው እኔ እኔ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ‹‹እኛ ከሰበክንላችሁ የእውነት የሕይወት ወንጌል ሌላ ከሰማይ መልአክም መጥቶ ቢሰብክላችሁ አትቀበሉ፡፡›› ተብሎ የተጻፈ ስላለ ምዕመን በጣም መጠንቀቅ ይገባዋል፡፡ ከፍሬያቸው ታውቋችዋላችሁ ከበለስ ወይን ሊለቀም አይችልም ተብሏል፡፡ ሃሳውያንም እውነት የላቸውም፡፡ በመንፈስ ቅዱስ ያብላሉ፡፡ ከእነርሱ መራቅ ያስፈልጋል፡፡ ትልቁ አላማቸው በጸሎታቸው ርዝመት እያመካኙ እመበለቲቱ ቦርሳ ጎልማሳው ኪስ መግባት ነው፡፡ይኸ ደግሞ ሥጋቸውን ብቻ ሳይሆን ነፍሳቸውንም የሚያደኽይ ነው፡፡ አሁን አሁን በቤተክርስቲያኗ አካባቢ ሁሉን በገንዘብ ማድረግ እንደ ሥርዓት እየተለመደ መጥቷል ፤ ሰውን በከፍተኛ ሁኔታ በሚያስገብዝ መልኩ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ ግን ደግሞ በገንዘብ መርገም መግዛት እንዳለ  ከጽድቁም ከገንዘቡም ሳይኮን ሜዳ ላይ  እንደሚያስቀር ማስተዋል ያስፈልጋል፡፡ የቤተ ክርስቲያን ሀብቷ ሰው እንጂ ገንዘብ አይደለም፡፡

Monday, May 19, 2014

አቡነ ማትያስ ለቅዱስ ሲኖዶስ ያቀረቡት ተግሳጽ ፤ ምክር፤ አቤቱታና ጩህት



  •  ‹‹የእግዚአብሔር ባለ አደራ መሆን ቀላል ስላይደለ እያንዳንዳችን በእግዚአብሔር ፤ በታሪክና በሃይማኖት በምንመራቸው ምዕመናን ዘንድ በኃላፊነት እንጠየቃለን፡፡››
  • ‹‹ፓትርያርኩ በተቃራኒ መንገድ በመጓዝ ምን አይነት ጥቅምና የኅሊና ደስታ እንደሚሰጣቸው በፍጹም ሊገባን አልቻለም፡፡ ›› አቡነ ማትያስ ለአቡነ ጳውሎስ
  • ቆቡ እንደው አንድ ጊዜ ከተሰቀለ በኋላ በቀላሉ የሚወርድ ወይም የሚሻሻል አይደለም፡፡ “ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ” (የጳጳሳትን ሹመትን በተመለከት ለቅዱስ ሲኖዶስ ያሳሰቡት)
  • በስመ ሲኖዶስ  የሚጠቀሙት ባለስልጣኖች ሲኖዶሱን ባያሰድቡ መልካም ነው፡፡

(አንድ አድርገን ግንቦት 12 2006 ዓ.ም)፡-  በአሁኑ ሰዓት ስድስተኛ ፓትርያርክ አድርጋ ቤተክርስቲያን የሾመቻቸው አባት ከአመታት በፊት የሰሜን አሜሪካ ሊቀ ጳጳስ ሆነው ማገልገላቸው ይታወቃል፡፡ ከ14 ዓመት በፊት በርካታ አስተዳደራዊ ግድፈቶችን ተመልክተው ማለፍ ያልቻሉት አቡነ ማትያት ለቅዱስ ሲኖዶስ የሚደርስ 20 ገጽ ደብዳቤዎችን ከበርካታ አባሪ ማስረጃ ደብዳቤዎች ጋር ለወቅቱ የቅዱስ ሲኖዶሱ ዋና ጸሀፊ ለብጹዕ አቡነ ኒቆዲሞስ ጥቅምት 12 1992 ዓ.ም አድርገው ልከው ነበር፡፡ ይህ የተላከው ሰነድ ቅዱስ ሲኖዶስ ተነጋግሮበት ውሳኔ እንዲሰጥበት መሆኑን አቡነ ማትያስ በመልዕክታቸው ይገልጻሉ ፡፡ ነገር ግን ከቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ያገኙት መልስ ቢኖር አልደረሰንም የሚል ነበር፡፡ ይህ በሴራ ለቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ እንዳይቀርብ የተደረገው ደብዳቤ የግል ጋዜጦች እንዲያወጡትን በቀድሞ ፓትርያርኩ እና በዙሪያቸው ያሉ ሰዎች  እያደረጉት ያለውን ነገር ህዝቡ እንዲያውቅ ለማድረግ በአስቸኳይ የፖስታ አገልግሎት በወቅቱ ህትመት ላይ ለነበረው “ኢትኦጵ” መጽሄት ዋና አዘጋጅ ለአቶ ተስፋዬ ተገኝ ከተላከው ሰነድ እና በጊዜው ለህትመት ከበቃው ጋዜጣ ላይ መለስ ብለን ምን አይነት ስሞታዎችንና ቅሬታዎችን ለቅዱ ሲኖዶስ እንዳቀረቡ ለማየት እንሞክራለን፡፡