Sunday, September 28, 2014

ዘመን እና ሰው

  • እንኳን ከዘመን ዘመን (ለዚህ 2007 .. ከዘመነ ማርቆስ ወደ ዘመነ ሉቃስ) በሰላም አሸጋገረን፡፡

በዲ/ን ብርሃኑ አድማስ
አንድ አድርገን መስከረም 18 2007 ዓ.ም
ሁለት ዓይነት ጊዜ እንዳለ ቅዱሳት መጻሕፍት ይናገራሉ፡፡ አንደኛውና ይህ ዛሬ "እንኳን ከዘመን ዘመን... " የምንባባልበትና ፍጥረትና ድርጊቱ በቅደም ተከተል የሚሰነዱበት ጊዜ ነው፡፡ ይህንን ጊዜ ከዚህ በኋላ "የፍጥረት ጊዜ" ወይም ታሪካዊ (Historical time) ጊዜ የምንለው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ከሥነፍጥረትም በፊት በፍጥረትም ጊዜ ከፍጥረት ማለፍም በኋላ የሚኖረውና በፈጣሪ ሕልውና የሚለካው (አስተውሉ እርሱ ራሱ ይለካል እንጂ የፈጣሪን ድርጊት የሚለካ አይደለም) ከአሁን በኋላ "ዘላለማዊ ጊዜ" ወይም እንደኛ ሊቃውንት "ዮም" የምንለው ሌሎቹ በእንግሊዝኛ "የተቀደሰ ወይም ዘላለማዊ ጊዜ" (Sacred time)የሚሉት ጊዜ ነው፡፡ ዮም የግእዝ ቃል ሲሆን ትርጓሜውም ዛሬ ማለት ነው፡፡ ይህ ሁለተኛው ጊዜ በእኛ ሊቃውንት ዘንድ "ዮም" የሚባልበት ምክንያት ከመዝሙረ ዳዊት "እግዚአብሔር ይቤለኒ ወልድየ አንተ፤ ወአነ ዮም ወለድኩከ" እግዚአብሔር አንተ ልጄ ነህ፤ እኔ ዛሬ ወለድሁህ (መዝ 27)የሚለውን ጥቅስ መነሻ አድርገው ትርጓሜውን ሲያብራሩ እግዚአብሔር ስለ ራሱ የገለጸው የጊዜ መጠሪያ ዮም ወይም ዛሬ መሆኑን ስለሚያመሰጥሩ ነው፡፡ ይህም ማለት በእግዚአብሔር ዘንድ ትናንት እና ነገ፤ አምናና ከርሞ፤ ጥንትና መጪው ጊዜ ወይም ከዚህ ዘመን በኋላ የሚባል ነገር የለም ማለት ነው፡፡

ኅዳር 25 ቀን 2006 ዓ.ም ፡ ‹‹የመስቀል በዓል›› በዩኔስኮ የሰው ልጅ መንፈሳዊ ባህላዊ ቅርስ ሆኖ የተመዘገበበት ቀን

·  በብሔራዊ ደረጃ መስቀል የኢትዮጵያ መንፈሳዊ ባህላዊ ቅርስ ተብሎ በቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን ነሐሴ 14 ቀን 2003 .. በቁጥር 0001 ተመዝግቧል፡፡
  • በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከሚከበሩት የአደባባይ በዓላት አንዱ የሆነው የጥምቀት በዓል በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ እንደምትሠራ ቤተ ክህነት አስታወቀች፡፡ 
        አንድ አድርገን መስከረም 18 2007 ዓ.ም
 
ከብሔራዊ እስከ ዓለም ቅርስነት  ኦርቶዶክሳዊቷ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ካሏት ቅዱሳን በዓላት መካከል በዐውደ ምሕረትም በሕዝብ አደባባዮችም ከምታከብራቸው ውስጥ መስከረም 17 ቀን በየዓመቱ የሚከበረው የመስቀል በዓል ይገኛል፡፡  

መስቀል በዋነኛነት ክርስቲያናዊ ሃይማኖታዊ በዓልነቱን የያዘ ከባህል መገለጫዎች ጋር ምእመኑና ኅብረተሰቡ በመላዋ ኢትዮጵያ በአንድነትና በኅብረት የሚያከብረው ታላቅ በዓል ነው፡፡
ከአንድ ሺሕ አምስት መቶ ዓመታት በላይ ሲከበር የኖረው የመስቀል በዓል ከኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንና ከምእመኖቿም አልፎ ካለው መንፈሳዊና ባህላዊ እሴት በመነሣት ዩኔስኮ (በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት) 2006 .. ኅዳር ጀምሮ በዓለም ቅርስነት መዝግቦታል፡፡ 

Wednesday, September 24, 2014

ቤተክህነት የጥምቀት በዓልን በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ እንደምትሠራ አስታወቀች

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከሚከበሩት የአደባባይ በዓላት አንዱ የሆነው የጥምቀት በዓል በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ እንደምትሠራ ቤተ ክህነት አስታወቀች፡፡ 
በጠቅላይ ቤተክህነት፣ የቅርስ ጥበቃና ምዝገባ ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር መምሪያ ኃላፊ ቀሲስ ሰሎሞን ቶልቻ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ጥር 11 ቀን በመላው አገሪቱ የሚከበረው የጥምቀት በዓል ከመስቀል በዓል ቀጥሎ ሁለተኛው የዓለም ቅርስ ሆኖ እንዲመዘገብ ሥራ እየተሠራ ነው፡፡ 
ከዋዜማው ጀምሮ እስከ ማግስቱ የሚቆየው የጥምቀት ከተራ በዓል ከመንፈሳዊ በዓልነቱ ባሻገር ባህላዊ ትስስርም ያለው በመሆኑ በዓለም አቀፍ ደረጃ ትኩረት እየሳበ ነው፡፡ 
ለዚህም በዓሉን እንደ መስቀል በዓል ሁሉ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የትምህርት የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በረቂቅ ባህላዊ ቅርስ (Intangible Cultural Heritage) ለማስመዝገብ የሚመለከታቸው አካላት ትኩረት እንዲሰጡበት የአንትሮፖሎጂና የፎክሎር ባለሙያዎች በየጊዜው የሚያነሱት ነጥብ መሆኑ ይታወቃል፡፡ 
በሌላ በኩል ዘንድሮ የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባና በየክልሉና ዞን ከተሞች በሚገኙት መስቀል አደባባዮች እንደሚከበር የገለጹት ቀሲስ ሰሎሞን ቶልቻ፣ በዓሉ የዓለም ቅርስ ሆኖ በተመዘገበ ከስምንት ወራት በኋላ የሚከበር በመሆኑ ልዩ እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡ መስቀል ከሃይማኖቱ ጎን ለጎን ለኢትዮጵያ ብሔረሰቦች የባህል ግንባታ አስተዋጽኦ ማድረጉንም ገልጸዋል፡፡