Saturday, February 9, 2019

‹‹የቤተ-ክርስቲያን ደውል ተደውሎ ቤት አልቀመጥም›› ብሎ አምልጦ በወጣ ወዲያው “ልጅሽ ሞተ› ተብሎ ተነገረኝ



(አንድ አድርገን የካቲት 03 2011 ዓ.ም )፤- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በየዓመቱ ጥር 21 የሚከበረው የአስተርእዮ ማርያም በዓት ዕለት በሱማሌ ክልል ርዕሰ ከተማ ጅግጅጋ ግጭት ተከስቶ ነበር፡፡ ከጅግ-ጅጋ ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ-ክርስቲያን ተነስተው 110 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ የምትገኝው እጅግ ጥንታዊቷ ገሪ ቆጨር ቅድስት ማርያም ቤተ-ክርስቲያን ተጉዘው መንፈሳዊ በዓሉን አክብረው በመመለስ ላይ ያሉ የጅግ-ጅጋ ከተማ ምዕመናን ‹‹ዱደሂሳን›› የሚባል ቦታ ላይ ሲደርሱ ከሱማሌ ገሪ ጎሳ የተወጣጡ ግለሰቦች “የጃርሶ ጎሳ አባላት ከመካከላችሁ አውጡ” በማለት በአራት የሕዝብ መኪናዎች ላይ የድንጋይ ናዳ ማውረድ ጀመሩ፡፡ በዚህ ጥቃት ምክንያት የአንዲት እናት ጥርስ ከመርገፍ ጀምሮ  በአራቱም መኪናዎች ላይ የሚገኙ ምዕመናኖች ላይ  ጉዳት በመድረሱ በጅግ-ጅጋ በዕለቱ ከፍተኛ ውጥረት ሊነግስ አንደቻለ በግጭቱ ዙሪያ ያነጋገርናቸው የከተማዋ ነዋሪዎች ለመረዳት ችለናል፡፡