Monday, October 20, 2014

ዝክረ አበው


አንድ አድርገን ጥቅምት 10 2007 ዓ.ም
ቀድሞ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን የመሩ ከአጸደ ሥጋ ዓለም በሞት ተለይተው በአጸደ ነፍስ የሚገኙ ቅዱሳን ፓትርያኮችና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፤ ጥቅምት 9 ቀን 2007 ዓ.ም በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ጸሎተ ፍትሐት ተደርጎላቸዋል፡፡  ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ፣ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ፣ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ እንዲሁም ለብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳትን በጊዜው ጸሎተ ፍትሐት ተደርጎላቸዋል፡፡ ያለፉትን አባቶቻችንን እንዲህ ለማስታወስ ሞከርን፡፡

1.     ቀዳማዊ አቡነ ባስልዮስ (፲፰፻፹፬ዓ/ም (ሚዳ ሚካኤል) - ፲፱፻፷፫ ዓ/ም (አዲስ አበባ)) የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት እና የመጀመሪያው ፓትርያርክ ነበሩ።የመናገሻ አምባ ማርያምን ገዳም እያስተዳደሩ ሳሉ፤ ከዚህ ሥልጣናቸው በተጨማሪ የአዲስ አበባ መንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም መምህርነት በየካቲት ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፬ ዓ/ም ተሰጣቸው። ከዚያም ቀጥሎ መጋቢት ፲፪ ቀን ፲፱፻፳፭ዓ/ም በኢየሩሳሌም ያሉ የኢትዮጵያን ገዳማት በመንፈሳዊ መሪነት አስተዳዳሪ ሆነው ተሹመው ለሁለት ዓመታት ካገለገሉ በኋላ ወደአገራቸው ተመለሱ። 

Sunday, October 19, 2014

‹‹አባ ማትያስ አላበደም ፤ መልዕክቱን እያስተላለፈ ነው›› አቡነ ማትያስ ለጉባኤው የተናገሩት



  • እግዚአብሔር ላበዱት አይምሯቸውን ይመልስልን ፤ ላላበዱትና ለማበድ ለተዘጋጁት አይምሯቸውን ይጠብቅልን፡፡

 አንድ አድርገን ጥቅምት 9 2007 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላለፉት ኻያ አንድ አመታት በርዕሰ አበውነት ‹ሲገዙ› የነበሩትን የብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስን ሞትን አስከትሎ ስድስተኛውን ዘመነ ፕትርክና  የምደባ ያህል  የተረከቡት ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ  የቤተ ክርስቲያኒቱን ቀናኢ ሊቃውንትና ምእመናን ለዘመናት ሲያንገሸግሽ የቆየውን አድሏዊ አሠራር ፤ ጎጠኝነትና ሙስና በመጠኑም ቢኾን ይፈታሉ የሚል ግምት ተሰጥቷቸው ነበር፡፡



በበዓለ ሲመታቸው ወቅት ንግግር ሲያደርጉ የቤተ ክርስቲያኒቱን ሊቃውንትና ምእመናን ብሶትና የዕለት ከዕለት ምሬት የተሰማቸው  በሚመስል ሁኔታ  ትኩረት ሰጥተው ከሚንቀሳቀሱባቸው  የሥራ ዘርፎች  መካከል ፤ በዋነኝነት ሙስናንና ጎጠኝነትን መዋጋት እንደሚሆን መጥቀሳቸው ይታወሳል፡፡

Saturday, October 18, 2014

ሰዶማዊነትና ሰብዓዊ መብት


አንድ አድርገን ጥቅምት 9 2007 ዓ.ም
 አባ ሳሙኤል (ሊቀ ጳጳስ)

   የቅዱስ ሰኖዶስ አባልና
            የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን ሊቀጳጳስ

የእግዚአብሔር ዕቅድና ፈቃድ ከፍጥረታቱ የተለየ ወይም የራቀ አይደለም። ዓለምን የፈጠረው ከሰዎች ጋር ዘለዓለማዊ  መቀራረብ ወይም ግንኙነት እንዲኖረው ፈልጎ ነው። ይህ የሚያልፈው ዓለም (ምድር) እንኳን በጊዜው ቢያልፍ በማያልፈው ሰማያዊ ዓለም ፈጥሮአል። ይህ የሚታየው ዓለም (Physical world) የተፈጠረው ለሰዎች መገልገያ እንደሆነ መፅሐፍ ቅዱስ ይናገራል።ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሉአት፣ ግዙአትምዘፍ1÷28ሰማየ ሰማያት ለእግዚአብሔር ወምድርስ ወሀበ ለእጓለእመሕያው ሰማይ ለእግዚአብሔር መንበሩ ነው ምድርን ግን ለሰው ልጆች ሰጣትእንዲል። መዝ.13÷16


Friday, October 17, 2014

የቤተ ክርስቲያን አውደ ምህረትን ከ‹‹ድምጻችን ይሰማ ›› አይነት ኦርቶዶክሳዊ ካልሆነ አካሄድ መጠበቅ የሁላችን ሃላፊነትና ግዴታ ነው፡፡


  • “ ተግዳሮቶቼን የምፈታው በምክክርና በጸሎት ነው፡፡” – ማኅበረ ቅዱሳን (አዲስ አድማስ፤ ሚያዝያ ፬ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም.)
አንድ አድርገን ጥቅምት 8 2007 ዓ.ም
በቅርቡ ፓትርያርኩ እና አጋሮቼ የሚሏቸው ሰዎች የፈጠሩት ስም ማጥፋትን በተመለከተ ብዙ የእምነቱ ተከታዮች ስሜታቸው እንደተነካ እና ፓትርያርኩ እየሰሩት ያለው ስራ አግባብነት እንደሌለው ከበታች ምዕመን ጀምሮ እስከ ጠቅላይ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅ ድረስ ተቃውሞ እንደደረሰባቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡ ስሜ ያለ አግባብ ጠፍቷል ያለው ማኅበረ ቅዱሳንም ጉዳዩን አገልግሎቱን በቤተክርስቲያኒቱ ጥላ ሥር ሆኖ እንዲያካሂድ ለፈቀደለት ለቅዱስ ሲኖዶስ በማቅረብ ምላሹን እየተጠባበቀ መሆኑን ከመግለጹም በተጨማሪ በቀጣይ ያለ ምንም ማስረጃ ይሁን መረጃ ጆሮ ስላገኙና አጨብጫቢ ስለከበባቸው ብቻ በማኅበሩ ላይ ለሚደረግበት ስም ማጥፋት በሕግ እንደሚጠይቅም ለቅዱስ ሲኖዶስ በላከው ደብዳቤ ገልጿል፡፡

Thursday, October 16, 2014

የወቅቱ አጀንዳ ፡- ሕገ ወጥ ሰባኪያንን እና አጥማቅያንን መቆጣጠር

 አንድ አድርገን ጥቅምት 6 2007 ዓ.ም ፡ -

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጥቅምት 5 ቀን 2ዐዐ7 . የተጀመረው የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ እንደቀጠለ ይገኛል፡፡ እስከ አሁን 24 አህጉረ ስብከቶች ሪፓርቶቻቸውን አቅርበዋል፡፡ ጉባኤው ከተነጋገረበት አንዱ ጉዳይ ‹‹ሕገ ወጥ ሰባኪያንን እና አጥማቅያንን መቆጣጠር›› የሚል መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡በሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን ማጥመቅ የሚችለው የቅስና ሥልጣነ ክህነት ያለው አባት ብቻ ነው፡፡ ቅስና የሌለው ሰው አያጠምቅም  አያናዝዝም   አይባርክም /ፍት....አን.3 .21/  ቅዱሱን ቅባት  መቀባት የሚችለው የክህነት ሥልጣን  ያለው ብቻ ነው፡፡  /ያዕ.5÷14/  ሀብተ መንፈስ ቅዱስ በገንዘብ  አይሸጥምና አጥማቂው ካህን መማለጃ መቀበል አይገባውም፡፡ /....አን.7/ አሁን ግን እየተመለከትን እና እየታዘብን ያለነው ሕገ ወጥ ሰባኪያንና ሕገ ወጥ አጥማቂያን የማህበረሰቡን ችግር በመረዳት ጥረው ግረው በወዛቸው የምድርን ፍሬ ከማግኝት ይልቅ  በብልጣ ብልጥ አካሔድ የአባቶችን ኪስና የእናቶችን መቀነት መፍታት ላይ መዝመታቸውን ነው፡፡