Monday, June 17, 2013

‹‹ይህ ቤተክርስቲያን ለኢንደስትሪ ልማቱ ትልቅ እንቅፋት ነው›› የቦሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ



  •  ቤተ ክርስቲያኑ እንዲፈርስ የተደረገው ለሶስተኛ ጊዜ ነው፡፡ ከዚህ በፊት ቀበሌው ቤተክርስቲያኑን አፍርሶ ታቦታቱን በግብረ ሃይል(በኢ-አማንያን) እንዲነሱ ካደረገ በኋላ በቀበሌ መጋዘን ውስጥ እንዲቀመጡ አድርጓል፡፡
  •  የቅዱስ ሩፋኤል ፤ የበአታ ለማርያም ፤ የቅዱስ ገብርኤል እና ኤዎስጣጢዎስ ታቦታት በሚያሳዝን ሁኔታ ከነ መንበራቸው ሜዳ ላይ ተጥለዋል፡፡
  • ‹‹ቀበሌው በራሱ ፍቃድ ነው ቤተክርስቲያኑን ያፈረሰው›› የቤተክርስቲያኑ አስተዳዳሪ

(ከቆንጆ መጽሄት)፡-ቦሌ ሰሚት ኮንዶሚኒየምና በአካባው የሚገኙ የኦርቶዶክስት ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች እንዲገለገሉበት የተተከለው  የቦሌ ለሚ ቅዱስ ሩፋኤል ወአውስጣጢዎስ ቤተ ክርስቲያን ከተተከለበት ከ2001 ዓ.ም ጀምሮ የአካባቢው ማኅበረ ካህናትና ምዕመናኑ ሃይማኖታዊ ስርዓትና መንፈሳዊ አገልግሎት እያገኙ ስርዓተ አምልኮትን በነጻነት እያከናወኑ ባሉበት ሰዓት ባልታወቀና ባልተጠበቀ ሁኔታ ቅድመ ማስጠንቀቂያ ሳይሰጥበት የወረዳ 11 ስራ አስፈጻሚ በቀን 09/08/05 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ ማስጠንቀቂያ ከሰጠ በኋላ በነጋታው እንዲፈርስ ተደረገ፡፡

የቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ወ/ሮ ኤልሳቤጥ መንግስቱ ለብጹዕ አቡነ ዳንኤል በቀን 09/08/05 በቁጥር በቦ/ክ/ከ/ወ 11/001/22/15 በጻፉት ደብዳቤ ላይ ‹‹በወረዳ 11 ቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ ዞን በተተከለ መንግሥት ካሳ በከፈለበት ቦታ ላይ ቅዱስ ሩፋኤል ቤተክርስቲያን በሕገወጥ መገንባቱ ይታወቃል ፡፡ ይህ ቤተ ክርስቲያን ለኢንደስትሪ ልማቱ በአሁኑ ሰዓት ትልቅ እንቅፋት በመሆኑ ከዚህ በፊት ለቤተክርስቲያን እና ለሃይማኖቱ ክብር በመስጠት በተደጋጋሚ ቤተ ክርስቲያኑን  እንዲያሱ ስንጠይቅ መቆየታችን ይታወቃል፡፡ ይሁንና እሰከ ዛሬ ድረስ ቤተ ክርስቲያኑን ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡ በዚህ መሰረት ቅዱስ ሲኖዶስ በ09/08/2005 ዓ.ም በግብረ ሃይል የምናነሳ  መሆኑን አውቆ  በቤተክርስቲያኑ ውስጥ ያለውን ጽላት እና ንዋየ ቅድሳት እንዲያነሱልን ለቤተክርስቲያኑ አስተዳደርም መመሪያ እንዲሰጡልን በጥብቅ እናሳስባለን›› ይላል፡፡

Tuesday, June 4, 2013

Presidency, Church prepare joint Ethiopia trip to discuss controversial dam



(egyptindependent )፡- Egypt's presidency and the Coptic Orthodox Church are coordinating for a joint trip to Ethiopia by President Mohamed Morsy and Pope Tawadros II, where they will discuss with Ethiopian officials a means to resolve a dispute over Ethiopia's Millennium Dam.
Last week, Ethiopia announced the diversion of the Blue Nile's stream as a step towards beginning work on its Millennium Dam. However, the declaration and the project in general prompted apprehension by Egypt and Sudan that it would affect their shares of water which they obtained under British occupation.
Both the presidency and the church are arranging for a meeting by Morsy and Tawadros II to be held after the latter returns from his current visit to Austria, stated sources.
Tawadros II welcomed requests for him to interfere with Abune Mathias of the Ethiopian Orthodox Church and appeals for his support for Egypt's bid to preserve its share of Nile waters, the sources added. Egypt's pope is scheduled to meet with his Ethiopian counterpart on 19 June in Cairo to congratulate him on his ordination.
Tawadros II had delegated Archbishop Daniel of Maadi to attend Morsy's meeting with political figures on Monday, where ways to handle the crisis are currently being discussed.

‹‹የግብጽ ከፍተኛ የመንግሥት ተወካዮች እና የኮፕት ኦርቶዶክስ ተወካዮች በታላቁ የሕዳሴ ግድብ ዙሪያ ለመነጋገር አዲስ አበባ ሲመጡ መንግሥትም ሆነ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በእየሩሳሌም የሚገኝውን የዴር ሱልጣንን ጉዳይ ማንሳት ይገባቸዋል ›› አንድ አድርገን