Saturday, January 26, 2013

“መናገር የማልፈልገው ብዙ ነገር አለ” ብጹእ አቡነ ሕዝቅኤል



ከላይፍ መጽሄት የተወሰደ
(ቅጽ 7 ቁጥር 99 … ጥር 2005 እትም)
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ለቀናት ያደረገው ስብሰባ በመጠናቀቅ ባሳለፍነው ሳምንት ባወጣው መግለጫ አሜሪካን ሀገር የሚገኝው ሲኖዶስ ያቀረበውን ጥያቄ ለመቀበል ሕገ ቤተክርስቲያን እንደማይፈቅድለት በመግለጽ  ስድስተኛውን የቤተርክርስቲያን ፓትርያርክ ለመምረጥ መወሰኑን ማስታወቁ አይዘነጋም፡፡ የላይፍ መጽሄት አዘጋጆች ከመግለጫው በኋላ ወደ ሲኖዶስ ዋና ጸሀፊ አቡነ ሕዝቅኤል ቢሮ በማምራት አቡኑን ማብራሪያ ጠይቀዋል፡፡ አቡነ ሕዝቅኤል የስራ ጫና ውስጥ የነበሩ ቢሆንም  መጠነኛ ጊዜ መስዕዋት በማድረግ ጥያቄዎቻችንን በመቀበል ተገቢ ነው ያሉንን ምላሽ  ሰጥተውናል፡፡ ነገር ግን አቡኑን በምናነጋግርበተ ሰዓት ማንነቱ ያልለየነው አንድ ሰው ቢሮ ውስጥ ተቀምጦ ጥያቅና መልሱን ይከታተል ነበር፡፡ ለብጹእ አቡነ ሕዝቅኤል የምናቀርብላቸው ጥያቄ እኛን እየተመለከቱ ምላሽ መስጠት ይገባቸው የነበረ ቢሆንም በእያንዳንዱ አረፍተ ነገር  ግለሰቡን እየተመለከቱ ማረጋገጫ እንደሚጠይቅ ሰው አይናቸውን ገጽታው ላይ ያንከራትቱ ነበር፡፡ ጥያቄያችን ጨርሰን ከቢሮ ልንወጣ ስንልም “አቡኑን ለማስለፍለፍ ሞክራችሁ ነበር እሳቸው ግን ብልጥ በመሆናቸው አንዳች ነገር አልተናገሩም” ብሎናል፡፡ ለማንኛውን ቃለ ምልልሱን እነሆ፡፡

ላይፍ፡- የአገር ውስጥ ሲኖዶስ ባወጣው መግለጫ በቀጥታ ስድስተኛውን ፓትርያርክ ወደ መምረጥ እንደሚገባ አስታውቋል ፡፡ በዚህ ዙሪያ ከግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የምትወስዱት ትምህርት ምንድነው ?
አቡነ ሕዝቅኤል፡- እኛ ከግብጽ ኦርቶዶክስ እንለያያለን ፤ ምናልባት ልዩነታችን በቋንቋ ብቻ አይደለም፡፡ በሐይማኖት በኩል አንድ ነን፡፡ በፓትርያርክ ምርጫ በኩል የራሳችን መንገድ አለን፡፡ ቤተክርስቲያናችን ከግብጽ ባርነት ወጥታ  ራሷን ችላ እየተራመደች በመሆኗ ከእነሱ የምትዋሰው ነገር የላትም፡፡

Thursday, January 24, 2013

የአጉስታ ጽዮን ማርያም ቤተክርስቲያን ወቅታዊ ሁኔታ




(አንድ አድርገን ጥር 16 2005 ዓ.ም)፡- ቦታው ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ከጦር ኃይሎች ወደ ወይራ ሰፈር ሲሄዱ ከ2 ኪሎሜትር በኋላ ከአጉስታ ልብስ ስፌት ፋብሪካ አለፍ ብሎ ይገኛል፡፡ በ14/05/2005 ዓ.ም ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ ምክንያቱ እስከ አሁን ያልታወቀ አሳት የአጉስታ ጽዮን ማርያም ቤተክርስቲያን ላይ ከፍተኛ አደጋ አድርሷል ፤ ቤተመቅደሱ የተዘጋው ከጠዋቱ 3 ሰዓት በፊት ቢሆንም እሳቱ ግን የተነሳው 7 ሰዓት አካባቢ መሆኑ ሰዎችን አነጋግሯል ፤ ከቤተክርስቲያኒቱ በጣሪያ በኩል ትንሽ ትንሽ ጭስ መውጣት ከታየ በኋላ ብዙም ጊዜ ሳይሰጥ ነዳጅ የተርከፈከፈበት እስኪመስል ድረስ ተንቦገቦገ ፤ በደቂቃዎች ውስጥ በርካታ ሰዎች ከአካባቢው በመሰባሰብ እሳቱን ለማጥፋት ከፍተኛ ጥረት አደረጉ ፤ እሳቱን ለማጥፋት አካባቢው ላይ ባለው ነገር ከፍተኛ ጥረት ቢደረግም በወቅቱ እሳቱን ማጥፋት ግን አልተቻለም ፤ ይህ ጉዳይ ከአቅም በላይ መሆኑን በመገንዘብ ለአዲስ አበባ እሳት አደጋ መስሪያ ቤት ስልክ ተደውሎ የነበረ ቢሆንም እነርሱ እስኪመጡ ድረስ እሳቱ ከፍተኛ ጉዳይ አድርሶ ነበር ፤ በቦታው የደረሱበት ሰዓትም ብዙ ነገሩ ወደ አመድነት የተቀየረበት ጊዜ ነበር ፤ ሕዝቡን እጅጉን ያስገረመው በውስጡ የነበሩት የእመቤታችን ፤ የቅዱስ ኡራኤልና ፤ የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሀንስ ታቦታት ምንም ያለመሆናቸው ጉዳይ ነበር ፤ ከዚህ በተጨማሪ ማገሩን የበላው እሳት አባቶች ቅዳሴ ላይ የሚይዙት የእንጨት  የነሀስና የብር መስቀሎች እና የተለያዩ ቅዱሳት መጻህፍት ምንም እሳት ሳይነካቸው መገኝታቸው በምዕመኑን ዘንድ አግራሞትን ፈጥሯል ፡፡

Tuesday, January 22, 2013

አዲስ አበባ አጉስታ ጽዮን ማርያም ቤተክርስትያን ተቃጠለች



ዛሬ ጠዋት 2 ሰዓት ላይ የተነሳ ፎቶ




ቤታቸውን በፍቃደኝነት ዳግም በመስራት ላይ ያሉ ወጣቶች


ቀድሞ ቤተክርስቲያኒቱ እዚህ ቦታ ላይ ነበረች


  • ትላንትና ከቀኑ 7 ሰዓት በተነሳ እሳት ቤተክርስትያኒቱ ውስጥ ከሚገኙ ታቦታት   ከመጽፍትና ከመስቀል ውጪ ሙሉ በሙሉ አውድሟታል :: ቤተክርስቲያኒቱ በጠራራ ጸሀይ ፤ በቆርቆሮ የተሰራው ግድግዳ እና ድንገት በተነሳ እሳት በአንድነት በመሆን የደረሰውነ ጉዳት  ከፍ አድርገውታል
  • እስከ ዛሬ ከቀኑ 6 ሰዓት ድረስ ከ200 ሺህ ብር በላይ ተሰብስቧል ፤ በአሁኑ ሰዓት በርካታ ምዕመናኖች ቦታው ላይ በመገኝት ቤተክርስቲያኒቱን እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ 
    •      ከትላንት ማታ ጀምሮ የተጀመረው ስራ አሁንም ቀጥሏል ፤ ቤተክርስቲያኒቱ ከተቃጠለች 24 ሰዓት ሳይሞላት ማገር አቆመው የጎን ቆርቆሮ የማልበስ ስራ ተጠናቋል፡፡
      •     አካባቢው ያለው ሰው ስራውን ለሚሰሩት ሰዎች እንጀራ ወጥ ፤ ለስላሳ ውሃ እና አስፈላጊ ነገሮችን በማቅረብ ከ48 ሰዓት በፊት ስራን ለመጨረስ እየተረባረበ ይገኛል
      •                የእሳቱን መነሻ አሁንም እየተጣራ ይገኛል  ; እሳት አደጋ ተደውሎለት በሰዓቱ ባለመምጣቱ አደጋውን የከፋ አድርጎታል 
  • የእመቤታችን የቅዱስ ዮሃንስና የቅዱስ ኡራኤል ታቦቶች ምንም አለመሆናቸው እጅጉን አስገርሟል
  • በርካታ ሰዎች እሳቱን ለማጥፋት ተረባርበው ነበር
  • ትላንትና 70 ሺ ብር ከምዕመኑ መሰብሰብ ተችሏል ፤ ዛሬ ጠዋትም ቤተክርስቲያኒን ለመስራት ብር እየተሰበሰበ ይገኛል
  • ዛሬ ጠዋት በርካታ ወጣቶች ቤተክርስቲያኒቱን ዳግም ለማቆም እየተረባረቡ ይገኛ
  • የአካባቢው ወጣቶች እሳቱን ለማጥፋት ያደረጉት መረባረብ እጅግ ያስገረመ ነበር ፤ አሁንም ቤቷን ለማቆን ያለ እረፍት እየሰሩ ይገኛል ፤
     

Friday, January 18, 2013

ጉባኤ ኬልቄዶን Vs የጥር 6 የሲኖዶስ ጉባኤ




ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን
ጉባኤ ኬልቄዶን ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን በመልካም አርአያነት ሊወሰድ ይገባልን?

(አንድ አድርገን ፤ ጥር 10 2005 ዓ.ም)፡- ቤተክርስቲያን እስከ 451 ዓ.ም ማለትም እስከ ጉባኤ ኬልቄዶን ድረስ በመላው ዓለም  ባሉ ክርስቲያኖች ዘንድ አንድ ዶግማና አንድ ቀኖና ነበራት፡፡ ይህ ጉባኤ ግን ቤተክርስቲያንን ከሁለተ ከፈላት፡፡ ነባሩን ሐዋርያዊ አስተምህሮ የያዙት ተዋህዶዎች  የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት(Oriental Churches) በመባል የሚጠሩት  ኢትዮጵያ ፤ ግብጽ ፤ አርመን ፤ ሶርያና ሕንድ  የያዙት መለካውያን በመባል የሚታወቁት ደግሞ የምዕራብ አብያተክርስቲያናቱ (Occidental Churches) ላቲኖችና ግሪኮች ናቸው፡፡ በእነኚህ ሁለት ክፍሎች ጉባኤው ቤተክርስቲያንን ለሁለት ከፈለ፡፡  አስቀድሞ በ325 ዓ.ም በኒቂያ  ፤ በ381 ዓ.ም  በቁስጥንጥኒያ ፤ በ431 ዓ.ም በኤፌሶን የተደረጉት ጉባኤዎች (ሲኖዶስ) ቤተክርስቲያን የገጠማትን ፈተና በመጋፈጥና በአንድ ድምጽ በመወሰን  የተዋጣላቸው ነበሩ፡፡  ጉባኤዎቹ የሚጠሩበት  ምክንያትም ሐዋርያዊ ያልሆነ አዲስ የክህደት ትምህርት ተከሰተ ሲባል ነበር፡፡

Monday, January 14, 2013

በዋልድባ አራት መነኮሳትና ሶስት አርሶ አደሮች ታሰሩ


አንድ አድርገን (ጥር 05 -2005)፡- መንግሥት በዋልድባ አካባቢ እገነባዋለሁ የሚለውን የስኳር ፕሮጀክት ከጀመረ ወራት ተቆጥረዋል ፡፡ አንድ ጊዜ በጸባይ ሌላ ጊዜ ደግሞ በፈርኦናዊው ጡንቻው በማስፈራራት አላማውን ከግብ ለማድረስ ብዙ እየሞከረ ይገኛል ፡፡ መነኮሳቱን በጎጥና በቋንቋ እንዲከፋፈሉ ሁለትም ሃሳብ እንዲሆኑ ብዙ ጥሯል ፤ ዋልድባ ገዳም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ታላቅ ገዳም መሆኑን ወደ ኋላ በማለት ቦታውን የትግራይ ክልላዊ መንግስት አካል እንጂ የአማራ ክልላዊ መንግስት አይደለም ስለዚህ በገዳሙ ላይ ሃሳብ መስጠት የሚችሉት የክልሉ ተወላጅ የሆኑት መነኮሳት እንጂ ማንም አይደለም የሚል ሃሳብ በማንሳት ጉዳዩን ወደ ሌላ መንገድ ለመውሰድ ተሞክሯል ፤  በየጊዜው በቦታው ላይ የሚካሄደው ነገር ለመገናኛ ብዙሃን በማሳወቅ ሃይማኖታዊ ግዴታቸውን በመወጣት ላይ የሚገኙትን አባት እሳቸውን ለጠቆመ የኮንዶሚኒየም ቤት እና ብዙ ሺህ ብር እንደሚሰጠው መንግሥት ለአካባቢው ነዋሪዎች ሲገልጽ ተስተውሏል ፤ ግንባታውን የጀመሩት አንድ ሀገር በቀል እና አንድ አለም አቀፍ ተቋማት ስራውን በተለያዩ ምክንያቶች መስራት ተስኗቸው በአሁኑ ወቅት ሶስተኛ አለም አቀፍ ኮንትራክተር ወደ ቦታው ለሁለቱ ያልተሳካውን ሊሞክር ስራውን ጀምሯል ፡፡ የሥኳር ኮርፖሬሽን ኃላፊ አቶ አባይ ጸሃዬ ለኢቲቪ እንደተናገሩት ከሆነ ሶስተኛው ኮንትራክተር ስራውን ከመጀመሩ በፊት በዛሬማ አካባቢ የሚሰራው ግድብ ጥቂት በሚያሰራ መልኩ ማስተካከያ እንደታከለበት ጠቁመዋል፡፡ የቦታውን ሁኔታ ለቪኦኤ የገለጹት መነኩሴ እንዳሉት አዲስ የገባው ኮንትራክተር የጣሊያል ዜግነት ያላቸው ሲሆኑ “መነኮሳቱ ከአካባቢው ካለቀቁ ስራውን ለመስራት እንቸገራለን” እንዳሉ ገልጸዋል፡፡

Sunday, January 13, 2013

የቅ/ሲኖዶስ አስቸኳይ የምልአተ ጉባኤ ስብሰባ ሰኞ ይጀመራል

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ የምልአተ ጉባኤ ስብሰባውን የፊታችን ሰኞ፣ እንደሚያካሂድ ተገለጸ፡፡ በሲኖዶሱ አቸስኳይ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ፣ በሀገር ውስጥ እና በሰሜን አሜሪካ በስደት በሚገኙት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት መካከል በተጀመረው የዕርቅና ሰላም ውይይት ቀጣይነት ላይ በመነጋገር ዐቢይ ትርጉም ያለው ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
አዲስ አድማስ ከጠቅላይ ቤተክህነቱ ምንጮች እንደተረዳው፤ ሲኖዶሱ በዕርቅና ሰላም ውይይቱ ቀጣይነት ላይ የሚወያየው፣ ከኅዳር 26-30 ቀን 2005 ዓ.ም በዳላስ ቴክሳስ በተካሄደው የዕርቀ ሰላም ጉባኤ የተሳተፈው ልኡክ በሚያቀርበው ሪፖርት ላይ በመመሥረት ነው፡

Tuesday, January 8, 2013

የጳጳሳቱ ማረፊያ



የጳጳሳቱ ማረፊያ
from face book (by Henok Haile)
 116ኛው የግብፅ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቄርሎስ 6 በፓትርያርክነት ዘመናቸው ይቀመጡበት የነበረው በቅዱስ ማርቆስ ካቴድራል የሚገኝ አንድ ያረጀ ክፍል ነበር፡፡ በዚህ ክፍል ሲኖሩ አንድ የካቶሊክ መነኩሴ ሊጎበኛቸው መጣ፡፡ ፓትርያርኩን ማረፈያ ቤትና ዕቃዎቻቸውን ሲመለከት ለክብራቸው የሚመጥን ባለመሆኑ ደነገጠ፡፡ (ፓትርያርክ የሚሆኑ አባቶች በደህና ማረፊያ ሊኖሩ ይገባል ይህም ለእነርሱ ሳይሆን ለቤተ ክርስቲያን ክብር ሲባል ነው፡፡) መነኩሴው አቡነ ቄርሎስን እንዲህ ሲል ጠየቃቸው ‹‹እባክዎን በእንዲህ ዓይነት ቤት ውስጥ መኖር ለእርስዎ የሚመጥን አይደለም፡፡ ፈቃድዎ ከሆነ እኔ ቤትዎን ላድስልዎትና ምርጥ ምርጥ ዕቃዎችን ላስገባልዎት?›› ፓትርያርኩ ይህንን ጥያቄ ሲሰሙ ፈገግ ብለው በፍቅር ዓይን ከተመከቱት በኋላ ‹‹የእኔ ልጅ አመሰግናለሁ! እርግጥ ነው ይህ ቤት በጣም የተጎሳቆለ ነው፡፡ እንደዚህም ሆኖ ግን ጌታችን ከተወለደበት በረት ይሻላል!!›› አሉት፡፡
በእኚህ አባት እግር የተተኩት ፓትርያርክ አቡነ ሺኖዳ ደግሞ በግብፅ መንግሥት በታሰሩ ጊዜ  ምእመናኑ ከእስር ቤት ወጥተው ማረፊያ ቤት እንዲሰጣቸው በመጠየቅ ሰልፍ ወጥቶ ነበር፡፡ በዚህ ጊዜ አቡነ ሺኖዳ ለሕዝቡ ንግግር አድርገው ማረፊያ ይሰጣቸው በሚል የተወጣውን ሰልፍ እንዲበትኑ ተጠየቁ፡፡ እኚህ አባትም ሕዝቡን  እንዲህ ሲሉ አረጋጉት፡፡ ‹‹ለእኔ ማረፊያ እንዲሰጠኝ ብላችሁ ሰልፍ ወጥታችኋል ነገር ግን በፍቅር ከተሞሉት ከእናንተ ልቦች የተሻለ ማረፊያ ለእኔ አያስፈልገኝም!››  

Wednesday, January 2, 2013

አቶ በጋሻው ደሳለኝና አቶ ያሬድ አደመ ያለፍቃድ የሄዱበት ደብር በጉሸማ እና በፖሊስ እንዲመለሱ ተደረገ

  • “ወንጌል ያልገባቸው የኦሪት ሰዎች” አቶ በጋሻው የአካባቢው ምዕመን የተናገረው

(አንድ አድርገን ታህሳስ 24 2005 ዓ.ም)፡- ቅዱስ ሲኖዶስ ባለፈው አመት ባደረገው ጉባኤ በቤተክርስቲያናችን ውስጥ መናፍቃን ሆነው በውስጣችን የተሰጎሰጉትን ሰዎች ማውገዙ ይታወቃል ፤ ከዚህ ጋር በተያያዘ የአቶ በጋሻው ደሳለኝ እና መሰሎቹን ጉዳይ ለማጣራት በማለት ለዚህኛው ዓመት መሸጋገሩን ይታወሳል ፤ በአሁኑ ሰዓት 6ተኛ ፓትርያርክ ወይስ እርቀ ሰላም በሚባልበት ወቅት አቶ በጋሻው ደሳለኝ በጎንደር አዘዞ ሎዛ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ባለፈው ቅዳሜ ማስተማሩ ለማወቅ ተችሏል ፡፡ ይህ ሰው የቀድሞ ስራዎቹ እስኪፈተሹ እና በሊቃውንተ ጉባኤ ውሳኔ እስኪሰጥበት ድረስ በየትኛውም አውደ ምህረት ላይ እንዳይቆም የተደረገ ሰው ቢሆንም አሁን ቤተክርስቲያኒቱ ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት በማስገባት በቦታው ቀድሞ ካፈራቸው ሰዎች ጋር በመነጋገር ከቤተክህነትና ከሀገረ ስብከቱ  ፍቃድ ውጪ ሊያስተምር ችሏል ፡፡ ቅዳሜ አስተምሮ በሚቀጥለው ቀን ያለ ፍቃድ ለምን አስተማረ? በማለት በተነሳ አለመግባባት በአካባቢው ወጣቶች ጉሸማ እና በፖሊስ አማካኝነት ቦታውን ለቆ እንዲሄድ የተደረገ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡በወቅቱም ያሬድ አደመ ለሚጠየቀው ጥያቄ የንቀትና በማሾፍ መልኩ መልስ ሲሰጥ ተስተውሏል ፤ ወጣቱም “እነዚህ ሰዎች በባለፈው የሲኖዶስ ጉባኤ እስኪጣራ ተብለው ጉዳያቸው በእንጥልጥል ያለ በመሆኑ ከሊቃውንት ጉባኤ ውሳኔ በፊት እንዳይመጡብን ፤  እነዚህ ሰዎች በሀዋሳ ምን  እንዳደረጉ እናውቃለን ለምን መጡብን?” በማለት የአካባቢው ወጣቶች ጥያቄ አንስተዋል ፡፡ አቶ ያሬድ አደመን “ እናውቅሃለን እኮ በሌላው ሃገር ሃይማኖትን ሳይሆን ገንዘብን እየሰበክ እንደዘረፍክ ከዚህ ምን ፈልገህ መጣህ?” በማለት ጥያቄ ሲጠይቁት አቶ ያሬድም ለተጠየቀው ጥያቄ በማሾፍ መልስ በሚሰጥበት ጊዜ ወጣቶቹ ብስጭት ውስጥ በማስገባቱ ወደ አልሆነ አምባጓሮ ሁኔታው እንደተቀየረ ለማወቅ ተችሏል ፤ በጊዜው ፓሊስ በቦታው በመገኝት ሰዎቹን ወደ መጡበት  እንዲመለሱ አድርጓል፡፡ ከዚያ ወጣቶቹ ከንቲባ ጽ/ቤት ድረስ በመሄድ “እነዚህ ሰዎች እዚህ ምንም የላቸውም በሰላም የቆየውን ምዕመን ሁለት ቦታ ሊከፍሉትና የአካባቢያችንን ሰላም ሊያሳጡን የመጡ ሰዎች በመነሆናቸው የአካባቢው አስተዳደር አውቋቸው ወደዚህ አካባቢ እንዳይመጡ የበኩሉን ያድርግልን” በማለት አመልክተው ፡፡ ከንቲባ ጽ/ቤቱም  ከሀገረ ስብከቱ እና ከቤተክህነት ውጪ ያለፍቃድ  የአካባቢውን ሰላም እንደ ሀዋሳው ሊያናጉ የሚፈልጉ ሰዎችን ከህዝቡ እና ከቤተክርስቲያኒቱ አስተዳደር ጋር በመነጋገር መልክ እንደሚያስይዘው ቃል ገብቶላቸዋል፡፡
  አሁንም እያየንና እየተመለከትን ያለነው ነገር በተሀድሶነት የሚንቀሳሱት ሰዎች እንደ እባብ የሞቱ ይመስላሉ እንጂ ጊዜ ጠብቀው ፤ ወቅቱን አገናዝበው እንደሚነሱ ነው ፡፡ በየሀገረ ስብከቱ ያለ ሀገረ ስብከት ፍቃድ ማንም የትኛውም ቤተክርስትያን መጥቶ ማስተማር እንደሌለበት የሚታወቅ ቢሆንም እነርሱን በመሰሉ ሰዎች አማካኝነት አሁንም የቀድሞውን ውዥንብር ለመፍጠር ያለመታከት እንደሚሰሩ ማሳያ ምልክት ነው፡፡ ይህ እንቅስቃሴ ከባለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር በጣም በከፍተኛ ሁኔታ የቀነሰ እና የጠፋ ቢመስልም አፈር እንዳልገባ ግን በየጊዜው በአሳቻ ሰዓት የሚደረጉ እቅስቃሴዎች ማወቅ ይቻላል ፡፡አቶ በጋሻው ዳሳለኝ እና ግብር አበሮቹ በስተመጨረሻ ሲባረሩ አቶ በጋሻው “ወንጌል ያልገባቸው የኦሪት ሰዎች” ብሎ ሲናገር ተደምጧል፤