Monday, July 28, 2014

‹‹መቅረዝ ዘተዋሕዶ - የውዳሴ ማርያም ማብራርያ›› መጽሐፍ በቅርብ ቀን በገበያ ላይ





መቅረዝ ዘተዋሕዶ መንፈሳዊት ድረ ገጽ አድራሻ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እምነት ፣ ሥርዓት ፤ ትውፊትና ታሪክ መሠረት ያደረጉ ትምህርታዊ የሆኑ ጽሑፎች የዘመኑን ቴክኖሎጂ በመጠቀም  በአራት በተለያዩ ቋንቋዎች(በአማርኛበትግርኛበኦሮምኛ እና በእንግሊዝኛ)  ላለፉት ዓመታት ወጥተዋል፡፡ እነዚህ ትምህርቶች ጸሐፊው በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ የኢንተርኔት አቅርቦት ላላቸው ምዕመናኖች በተቻለ መጠን ለማድረስ ሞክሯል፡፡ ነገር ግን እነዚኽን መንፈሳውያን ጽሑፎች በዓቅም ማነስ ምክንያት ቴክኖሎጂውን መጠቀም ላልቻሉ  ምእመናን ሊዳረሱ አልቻሉም፡፡

Tuesday, July 22, 2014

“ኦርቶዶክስን መሳደብ ማለት እናቴን እንደመሳደብ እቆጥረዋለሁ” አርቲስት ጥላሁን ጉግሳ


(አንድ አድርገን ሐምሌ 15 2006 ዓ.ም)፡- ከዓመታት በፊት በተሰራ አንድ ድራማ ላይ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነትን ፤ የእምነቱን አባቶችና ፤ ቤተ ክርስቲያኒቱ ያከበረቻቸው ጻድቃን ሰማዕታት ላይ የሚሳለቅ ድራማ በመስራት ለሕዝብ አቅርቧል በማለት ስሙ የሚነሳው የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ የሆነው አርቲስት ጥላሁን ጉግሳ እና ድራማው ላይ የተሳተፉ የሙያ ባልደረቦቹ በምዕመናን ዘንድ በተፈቀደ መድረክ ቤተክርስቲያኒቱን የማይመጥን ፤ ከስድብ ባለፈም አባቶች ላይ የሚያላግጥ ድራማ ነው በማለት ሰዎች ቅሬታቸውን ሲያሰሙ እንደነበር ይታወቃል፡፡(የድራማውን አንዱን ክፍል ይመልከቱ )፡

Monday, July 21, 2014

ወላይታ ፡ የፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት መገኛ


(አንድ አድርገን ነሐሴ 15 2006 ዓ.ም )፡-  ዳግማዊ ምኒልክ (ሕዝቡ በፍቅር እምዬ ይላቸው ነበር) ኅዳር ፳፯ቀን ፲፰፻፹፰(1888).. ወላይታ ከጦና ዋና ከተማ ደልቦ ደረሱ፡፡ እዚኽ የመገኘታቸው ምስጢር የወላይታው ንጉሥ ጦናአልገብርም› ብሎ በመሸፈቱ እሱን ለማረም ነበር፡፡ “…አገር ከጠፋ በኋላ ሲያቀኑት ያስቸግራል፡፡ ገንዘብም በግድ ካልሆነ በቀር በፈቃድ የሰጡት አያልቅም፡፡ አገርህን አታጥፋ፡፡ግብርህን ይዘኽ ግባ፡፡ ብለው በሽምግልና ቢሞክሩም መልሱ እምቢታ በመሆኑ አጤ ምኒልክ ዳሞት ተራራ ላይ ያሰፈሩትን ጦራቸውን አዘው በአንድ ጊዜ ወላይታን አስጨነቋት ፣ ንጉሥ ጦናም ቆስለው ተማረኩ፡፡የሚገርመው ግን መፍቀሬ ሰብዕ እና የዲፕሎማሲ ሰው የሆኑት አጤ ምኒልክአይ ወንድሜን እንዲያው በከንቱ ሕዝብ አስጨረስክብለው የንጉሥ ጦና ቁስል እንዲታጠብና እንዲታከም ካስደረጉ በኋላ የተማረከው የባላገሩ ከብት እንዲመለስ አድርገው ፣ ንጉሥ ጦና እስኪያገግሙ በእግዚአብሔር ቸርነትና ብርቱ በሆነው ተጋድሎአቸው የረቱት ጠብቀው የወላይታን ሕዝብ ሰብስበው “…እንግዲህ ወዲህ የሚያስተዳድርህ ልጄ ወዳጄ ጦና ነውና ተገዛለት፡፡ አውቆ ሳይሆን ሳያውቅ እኔን የበደለ መስሎት ሰው አስጨረሰ እንጂ ከድሮም ከአያቶቻችን ቂም የለንምና መልሼ እሱን ሾሜልሃለው፡፡እንግዲህ ወዲህ ብታምጽ በራስህ ዕወቅ፡፡ ግብሬን አግባ፡፡…” የሚል አዋጅ አስነግረው የወጉዋቸውን ጦናን ሾመው ጥር ፲፩ ቀን አዲስ አበባ ገቡ፡፡(አጤ ምኒልክ መጽሐፍ በጳውሎስ ኞኞ)

Sunday, July 20, 2014

ምንፍቅናን በ‹‹ምክር›› ወይስ በ‹‹ንስሐ›› ?

(አንድ አድርገን ሐምሌ 13 2006 ዓ.ም)፡- በደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስያን አስተዳዳሪ “መልአከ ብርሃናት አባ” ማርቆስ ብርሃኑ ከምዕመኑ እና ከማኅበረ ካህናት በተነሳባቸው አስተዳደራዊ እና  ሃይማኖታዊ ህጸጽ ጥያቄ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከትአስፈላጊውን ማጣራት ካደረገ በኋላ በ28/02/06  ዓ.ም አባ ማርቆስን ከአስተዳዳሪነት ሥራቸውን ከደመወዝ ጋር ማገዱ ይታወቃል ፡፡ ጉዳዩም በመንበረ ፓትያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት እንዲታይ መወሰኑ ይታወቃል…


መንበረ ፓትርያርክ ጽ/ቤት የሰጠው ውሳኔ እንደሚቀጥለው አቅርበነዋል

“መልአከ ብርሃናት አባ” ማርቆስ ብርሃኑ ከምዕመኑ እና ከማኅበረ ካህናት የተከሰሱባቸው ዋና ዋና ነጥቦች
  • ‹‹አማላጅነት የጌታ ተግባር ነው፤ ኢየሱስ አማላጃችን ነው እሱ ሁሉን ፈጽሞልናል›› ብለው መስበካቸውን
  • ‹‹ማርያምን ስሰብክላችሁ ደስ ይላችኋል ፤ ስለ ኢየሱስ ግን ይከፋቸዋል ፤ ማርያም እኮ ከእግዲህ ዋጋ የላትም›› ብለው ማስተማራቸውን
  • ተአምረ ማርያም ፤ ድርሳናት ፤ ገድላት በጸበል ቤት እንዳይነበቡ ማገዳቸውን በርካታ ምዕመናንና ሊቃውንተ ቤተክርስቲያና በምስክርነት ቆመው መስክረውባቸዋል፡፡

Friday, July 18, 2014

ቋሚ ሲኖዶስ ለፓትርያርኩ ከፍተኛ ማስጠንቀቂያ ሰጠ




  • አስቸኳይ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ለመጥራት ታቅዶ ነበር፡፡
  • ፓትርያርኩ በአ/አበባ የአድባራት አለቆች ዝውውት ስሕተት መፈጸማቸውን አምነዋል፡፡
  • ‹‹የቤተክርስቲያንን ሥራ ይጎዳል በሚል እንጂ ተመራጩ ነገር ከእሳቸው ጋር(ፓትርያርኩ) ጋር መሥራት ማቆም ነበር፡፡›› የቋሚ ሲኖዶስ አባል የተናገሩት

  • ፓትርያርኩ ከአሁኑ መንገዳቸው ካልተጠቆማቸው ፤ ስህተታቸው ካልተነገራቸው ቤተክርስቲያኒቱን አደጋ ላይ ሊጥሏት ይችላሉ፡፡


አንድ አድርገን ሐምሌ 12 2006 ዓ.ም፡- 
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕግን የመተርጎምና የማስፈጸም መብት ያለው ቋሚ ሲኖዶስ ፤ ውሳኔዬን አክብረው አላስከበሩኝም ፤ ጠብቀው አላስጠበቁኝም ላላቸው ብጹዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ከፍተኛ ማስጠንቀቂያ መስጠቱ ተገለጸ፡፡

Tuesday, July 15, 2014

ዐይናማው ሊቅ መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ


እምየዋ! እምየ አድማሱ ጀምበሬ። ምነው በዕድሜ ደርሰን ዐይንዎን አይተን ድምፅዎን ሰምተን በነበር። ዛሬማ ቸልታችንን ዕድሜ ይንሳው እና ኹሉን ነገር ችላ ብለን ለነአባ እንቶኔ ስለተውነው፤ እንደናንተ ያሉቱን ሊቃውንት አሟጥጠን ጨርሰን፤ ቤተ ክርስቲያናችን ቀኝ እና ግራቸውን በማይለዩ ገላግልት እየተወከለች የነውር ማዕድ ትፈተፍት ይዛለች።



Saturday, July 12, 2014

የላሊበላን አብያተ-ክርስቲያናትና የፋሲል ቤተመንግስትን በናኖ ቴክኖሎጂ ለማደስ ታቅዷል

From Addis Admass 
            ጥንታውያኑ የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትና የጎንደር ፋሲለደስ አብያተ መንግስታት ህንፃዎች ለዘመናት ሳይፈራርሱ እንዲቆዩ ለማድረግ ያስችላል በተባለው ናኖ ቴክኖሎጂ ለማደስ ታቅዷል፡፡ በጎንደር ዩኒቨርሲ የእውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰለሞን መስፍን፤ ቴክኖሎጂው በዓለም ላይ እየተስፋፋ እንደሆነ ጠቁመው፣ ጎንደር ዩኒቨርሲቲም የናኖ ቴክኖሎጂ ማዕከል አቋቁሞ በቅድሚያ በአብያተ ክርስቲያናቱና ቤተመንግስቱ ህንፃዎች ላይ ቴክኖሎጂውን ቻመተግበር እቅድ መያዙን፤ በቀጣይ ዓመትም ፕሮጀክቱ እንደሚጀመር ተናግረዋል፡፡ 

Monday, July 7, 2014

መለያየት የወቅቱ የቤተ ክርስቲያን አደጋ





የአንድ ምዕመን አስተያየት
(አንድ አድርገን ሰኔ 30 2006 ዓ.ም )፡- መስቀል ለእኛ ለምናምንበት ድህነትን ያገኘንበት፤ ተለያይተው የነበሩትን እግዚአብሔርና ሰዎችን እንዲሁም ሰዎችና ሰዎችን አንድ ያደረገና ያስታረቀ ለሰው ልጆች ሰላምን፤ ፍቅርን፤ እርቅን፤ አንድነትን ፤ ጽድቅን ያደለ ሁሌም ከልባችን የማይጠፋ ውለታ የተዋለበት ነው፡፡ ይሁንና ጌታ በመስቀሉ ያደለንን ነጻ ስጦታ ገፍተን በማወቅም ሆነ ባለማወቅ በተቃራኒው ጠብንና መለያየትን እያስፋፋን ወደ ከፋ ደረጃ እየሄድን እንገኛለን፡፡

ቤተ ክርስቲያን ባለፉት ዘመናት ብዙ ፈተናዎችና አደጋዎችን አልፋለች፡፡ ይህም ሊሆን የቻለው በእግዚአብሔር እርዳታ አባቶቻቸንንና ምእመኖቿ በጋራ ባደረጉት ከፍተኛ ተጋድሎ የተነሳ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ብዙ የምንታወቅበት ነገር ምንም አይነት ልዩነት ቢኖረን ሀገርንና ሃይማኖትን ሊነካ የውጭ ጠላት ሲመጣ ተባብረን አሳፍረን በመመለሳችን ነው፡፡ ይህ የውስጥ አንድነት ለጥንካሬያችን መሰረቱ ነው፡፡