Monday, December 31, 2018

Help the Martyrs' families - የሰማዕታቱን ቤተሰቦች እንርዳ

Click here to support

በሀገራችን ከተከሰቱ የቅርብ ጊዜያት ቀውሶች ሁሉ በዘግናኝነቱ ተወዳዳሪ የሌለው ክስተትና የጅምላ ጭፍጨፋ ባለፈው 2010 ሐምሌ ወር መጨረሻ በሀገራችን በሱማሌ ክልል በሚኖሩ "መጤ" በተባሉ ዜጎች መድረሱ ይታወቃል፡፡ በደረሰው የጅምላ ግድያና ዘረፋ በተለይም በእናቶች እና ሕጻናት ላይ ደርሶ የነበረው የጅምላ ደፈራ፣ የካህናት በቤተ መቅደሳቸው ውስጥ መታረድ፣ በድንጋይ ተወግረው መገደልና በአገልግሎት ላይ እያሉ ማቃጠል፣ የአብያተ ክርስቲያናት መውደም እንዲሁም የብዙኃን ለዘመናት ከኖሩበት ቦታ መፈናቀልና መበተን ዘመን የማይሽረው ክስተት ሆኖ አልፏል፡፡  
ከዚያ ዘግናኝ ጭፍጨፋ የተረፉትም ቢሆን በከፍተኛ የአእምሮ መታወክ ውስጥ እና በሕክምና እርዳታ ጥላ ሥር እንዳሉም ይታወቃል፡፡ "መጤ" የተባሉ ነዋሪዎች በሙሉ የዚያ ጭፍጨፋ ሰለባ እንደነበሩና ንብረታቸውም በጅምላ የወደመና የተዘረፈ እንደሆነም ይታወቃል፡፡ 

Abune Tewophilos and Emperor Haile Selassie I: Their Invaluable Contributions to the Ethiopian Orthodox Church


by Fikre Mariam Workneh

As a former celibate priest or monk, I had the privilege of serving both Abune Tewophilos and Emperor Haile Selassie I, and I would like to share my indelible memories about these two giant Ethiopians.
From left, Abune Tewophilos and Emperor Haile Selassie I.
Abune Tewophilos:
It has been nearly forty years since His Holiness Patriarch Tewophilos was murdered by the Ethiopian military/communist government in 1979. This barbaric act by the Ethiopian government against His Holiness was performed with the blessing of some members of the Orthodox Church clergy. Although many years have passed since His Holiness was strangled to death, for me it feels as though it happened just few days ago. I am still going through a profound sadness, an overwhelming sorrow and outrage about the fact that he was murdered in such an inhumane manner. No one had to die with such savagery. The Church, instead of preaching the gospel of love, mercy and forgiveness, became a collaborator to the military regime’s brutality. The Ethiopian Orthodox Church was left with an immeasurable loss of a wise leader. Those who came after him did not measure up to his intellectual caliber or vision.

Thursday, July 26, 2018

‹‹ኦርቶዶክስ ሀገር ናት ፤ በጣም ደስ ብሎኛል እንኳን ደስ አላችሁ ›› ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አሕመድ

  • ሀገራችን ካለ እናንተ ጸሎት ውጪ ሰላሟም ልማቷም ሊረጋገጥ አይችልም
  • ዛሬ በኢትዮጵያ ወገኖቻችን ላይ ተገንብቶ የኖረው የመጀመሪያው የጥላቻ ግንብ ዋንኛው ምሰሶ በይፋ ተንዷል


(አንድ አድርገን ሐምሌ 19 2010 ዓ.ም)፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አሕመድ በእርቀ ሰላም ጉባኤ ላይ የተናገሩትን እንዲህ አቅርበነዋል


‹‹በጣም ደስ ብሎኛል እንኳን ደስ አላችሁ ፤ ኢትዮጵያ ከዚች ታላቅ ቤተ ክርስቲያ ውጪ አትታሰብም ፤ እርቁ እንዲመጣ ያስፈለገበት ምክንያት ኦርቶዶክስ ሀገር ስለሆነው ነው ፤ ታላቅ ታሪክ ፣ ዝና እና ክብር ያላት ቤተክርስቲያን ናት ፤ እዚህ ሰላም ሲሆን ሁላችንም ሰላም እንሆናለን ፤ እዚህ ሰላም ሲጠፋ ደግሞ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪነት እያንዳንዳችንን ይነካናል ፤ አንድነቷ ከተጠበቀ ሌሎችን መርዳት ትችላለች ፤ የታሪክና የትውፊት ባለቤት የሆነች ቤተ ክርስቲያን ራሷ አንድነቷን በማጣቷ እሷ እያለች ሌሎች እኛን ሲያግዙን ኖረዋል ፤ የእሷ አንድነት ከምስራቅ አፍሪካ አልፎ ለአፍሪካ ትልቅ ዜና ፣ ትልቅ ብስራት እንደሆነ ይሰማኛል ፣ በተግባርም የምናየው ይሄንኑ ነው ፤ በህብረት ውስጥ የሚገኝ ትርፍ ፣ ሥምና ዝና አጥተናል ፤ ኦርቶዶክስ አንድ ሆና ቢሆን ኖሮ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ጉዳይ እርቀ ሰላም እስከ አሁን ባልዘገየ ነበር፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰው ከራሱ እንዲጣላ ፣ ከጎረቤትና ከሃይማኖቱ እንዲጣላ ፤ የሃይማኖት አባቶችን እንዳያከብር ፤ ሲገሰጽ እንዳይመከር ያደረገው አንዱ ነገር በዚች ታላቅ እና ቅድስት ቤተክርስቲያ ያጋጠመው ጸብ ነበር ማለት ይቻላል፡፡ እኛ አንድ ስንሆን ለክርስትና እምነት ብቻ ሳይሆን ለእስልምናና ኢትዮጵያ ውስጥ ላሉ ዜጎች በሙሉ ክብር ፣ አንድነትና ሰላም የሆነ ዜና መስማት እጅጉን የሚያስደስት ነገር ስለሆነ ዛሬ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናት ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ሙስሊሞችም እንኳን ደስ አላችሁ ማለት እፈልጋለሁ፡፡

Saturday, July 21, 2018

እርቀ ሰላም



( አንድ አድርገን  ሐምሌ 15 ፤ 2010 ዓ.ም ) መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል “ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም ፤ ነገር ግን  ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው ። ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል።” 

የፍቅር እጦት እንጂ ሰውም በወንድሙ ላይ በክፋትና በአመፅ አይነሳምና ቃየል አቤልን በምቀኝነትና በጥላቻ ተነሳስቶ እንደገደለው ሁሉ ዛሬም ብዙ ቃየላውያን በወንድሞቻቸው ላይ በትዕቢት እና በእብሪት ተነሳስተው የሚሞት ስጋቸውን ለመግደል ያሴራሉ። መግደል ለእነርሱ እጅግ የቀለለ ተግባር ነው፤ ቀድመው ህሊናቸውን ገድለዋልና። ማሳት ለእነርሱ እጅግ የቀለለ ተግባር ነው፤ ቀድሞ ህሊናቸውን ስተዋልና። ነገር ግን ዛሬም አሁንም በዚች ቅጽበትም በንስሃ ለተመለሰ ሁሉ ምህረት አለ። ከጥፋት መንገድ ዘወር ላለ መዳን ይሆንለታል። ነገር ግን እንደቀደመው ጊዜ በክፋትና በተንኮል ለመመላለስ ልቡን ያደነደነ፣ ፍቅርን የገፋ፣ ምህረትን የናቀ፣ ለወገኖቹ መጥፊያ ያሴረ፣ ጥላቻን ያነገበ እርቅን የጠላ ሰው ወይም ቡድን የኋላ ኋላ በታላቅ አወዳደቅ መንኮታኮቱ አይቀርም።

Wednesday, May 23, 2018

የወይንዬ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተመረቀ



(አንድ አድርገን ግንቦት 15 2010 ዓ.ም)፡- በኢትዮጵያ በረሃዎችና አውራጃዎች እየተዘዋወሩ በልዩ ልዩ አምልኮ የነበረውን ሕዝብ የክርስቶስ ወንጌለ መንግሥትን አስተምረውና አጥምቀው የክርስቶስን መንግሥት እንዲወርሱ ያደረጉት  ቅዱስ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት እግዚአብሔር በመራቸው መሠረት የሐዋርያ አሠረ ፍኖት በመከተል ዘር ልዝራ ፣ ትዳር ልያዝ ሳይሉ ታላላቅ ተዓምራትን ካከናወኑባቸው ቦታዎች  ውስጥ በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ከደብረ ብርሃን አካባቢ የሚገኝው ወይንዬ ተክለ ሃይማኖት ስፍራ አንዱ ነው፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወይን ተክለው ለ12 ዓመታት በቦታው በመቀመጥ ሲጸልዩበት የነበሩበትና በርካታ ተዓምራትን ያከናወኑበት  ፤ ጸበል አፍልቀው አህዛብን ሲያጠምቁበት የነበረውን ቦታ ያዩበታል፡፡ (በገድለ ተክለሃይማኖት ላይ ምድረ ደርደሬ ይለዋል)፡፡

ይህ ቦታ የሚገኝው ከደብረ ብርሃን ከተማ  በስተሰሜን ምዕራብ አቅጣጫ በግምት 5 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ቀጥ ባለ ገደል ተከቦ ሲሆን እዚህ ቦታ ላይ ጻድቁ አቡነ ህጻኑ ሞአ የተወለዱበትና እንደ በሬ ተጠምደው በማረስ ገድላቸውን የፈጸሙበት ታላቅ ስፍራ ይገኛል፡፡ በዚሁ ስፍራ ላይ ‹‹እስትንፋስ›› የሚባል ቦታ ከመሬት ሳያቋርጥ በሚወጣው እስትንፋስ አማካኝነት በርካቶች ከተለያዩ በሽታዎች የዳኑበትና እየዳኑ የሚገኙበት ልዩ ስፍራ ይገኛል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በቦታው ቀድሞ  ከኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ትላልቅ ገዳማት የመጡ አባቶች የሚያገለግሉበትና የሚገለገሉበት ታላቅ ቦታ  ፡፡

Sunday, March 11, 2018

ድንጋይ በድንጋይ ላይ



በዲ/ን ብርሃኑ አድማስ አንለይ


ሐዋርያት ከጌታችን ጋር በደቀ መዝሙርነት በነበሩበት ዘመን ምንም ያህል ኃይልና ተአምራት የማድረግ ነገር ቢሰጣቸውም ከሌላው ሕዝብ ጋር ሲኖሩ ቀድመው የወሰዱት ጠባይ ገና አልለቀቃቸውም ነበር፡፡ ለዚህ ምሳሌ ሊሆኑን ከሚችሉት ብዙ ማስረጃዎች አንዱ ዛሬ ደብረ ዘይት እያልን በምናከብረው በዓል ላይ በሚነበብልን ወንጌል የተገለጸው ምስክር ሊሆን ይችላል፡፡ ምንም እንኳ አምላክነቱን አምነውና አውቀው ቢከተሉትም ብዙ ጊዜ ግን እነርሱን የሚያስደንቃቸው ነገር እርሱንም የሚያስደንቀው፣ ለእነርሱ የተለየ የሚመስላቸው ነገርም ለእርሱም የተለየ የሚሆን ይመስላቸው ነበር፡፡ ለዚህም ነበር ቤተ መቅደሱን እያደነቁ እርሱም የሚደነቅ መስሏቸው የነገሩት፡፡

ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ቤተ መቅደስ ከተናገራቸው መካከል ድንጋይ በድንጋይ ላይ ሳይፈርስ አይቀርም የሚለውና በበዓለ ደብረ ዘይት የሚነገረው ይህ አስደናቂ ትምህርት አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ ይህም ማለት ለቤተ መቅደስ መሥሪያነት በመደራረብ ከታነጹትና ድንጋይ ከመባል ቤተ መቅደስ ወደ መባል ከደረሱት ውሰጥ እንደገና ተመልሰው አንዱም ሳይቀር ይነሡና ቤቱም ቤተ መቅደስ ከመባል ወጥቶ ቦታው ሜዳ ምድረ በዳ፣ ድንጋዮቹም ተመልሰው ድንጋይ ከመባል አይተርፉም ማለት ነው፡፡በርግጥ ቤተ መቅደሱ ቤተ መቅደስ መሆኑ የሚቀረው እግዚአብሔር የተለየው ጊዜ ነው፡፡ እርሱም በትምህርቱ ወቅት ራሱን ቤተ መቅደስ ብሎ ከመጥራቱ በቀር ይህን እነርሱ የሚመኩበትን ቤተ መቅደስ ቤተ መቅደስ ብሎ አልጠራውም፤ ምክንያቱም አይሁድ ቤተ መቅደስ ከመባል በግብር እያስወጡት ነበርና፡፡