Friday, April 15, 2016

የግብፅ ቤተ ክርስቲያን ከተሐድሶ እንዴት ተላቀቀች?


በዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ

ጊዜው እንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠር 18ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ነበር፡፡ ለአንዳች ተልዕኮ የተነሡ ሞራቪያውያን (የቼክ ሪፐብሊክ ዜጎች የሆኑ) ፕሮቴስታንት ሚስዮናውያን ወደ ግብጽ ገቡ፡፡ ጌታችን ከእናቱ ጋር ወደ ተሰደደባት በፈጣን ደመና ተጭኖ እየበረረ ወደ ደረሰባት ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ ወዳስተማረባት ሐዋርያዊት የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንጌታን እንሰብካለንብለው ዘመቱ፡፡ የእነዚህ ሚስዮናውያን እንቅስቃሴም በግብጽ ቤተ ክርስቲያን ላይ ላለፉት ሁለት መቶ ዓመታት ሲነድና ሲበርድ ለቆየው የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ሴራ መነሻ ነበር፡፡