Wednesday, November 28, 2012

ሚስጥረኛው መንግስታችን


  • ኢጣልያኖች የምኒሊክን ሐውልት ሲያወርዱ የተመለከተ አንድ ትንሽ ልጅ ጮሆ አለቀሰ፡፡ ኢጣልያኖችም ለምን እንደጮህና እንዳለቀሰ  ልጁን ጠየቁት፡፡ልጁም የንጉሴን ምስል ስላወረዳችሁ ነው አላቸው፡፡ ኢጣልያኖችም ከሙሶሎኒ ሌላ ንጉስ እንደሌለ ነግረውና ገርፈው አባረሩት…” ኒውዮርክ ታይምስ የካቲት 13 ቀን 1937 ዓ.ም እትም
(አንድ አድርገን ህዳር 20 ቀን 2004 ዓ.ም)፡-  ለዚች ሀገር እጅጉን ብዙ ውለታ ከዋሉት የሀገር መሪዎች ግንባር ቀደም መሪ ዳግማዊ አጼ ምኒሊክ ናቸው ቢባሉ ማጋነን አይሆንም፡፡ እንደ አለመታደል ሆኖ ሚኒሊክ ከጂቡቱ አዲስ አበባ ድረስ ተዘርግቶ ማየት የፈለጉት ከ10 ዓመት በላይ በርካታ ዋጋ የከፈሉበትና የደከሙበት  የባቡር ዝርጋታው በርካታ መቶ ኪሎ ሜትሮችን አቋርጦ የአዲስ አበባ ምስራቅ መውጫ  አቃቂ ከተማ እንደደረሰ ህይወታቸው እንዳለፈ ታሪክ ይናገራል ፡፡ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትርም የዛሬ 100 ዓመት ሚኒሊክ ሊያዩት ያሰቡትን ባቡር እሳቸውም ማየት ቢመኙትም ስራው በእሳቸው ዘመን ተጀምሮ ስራው ሳይጠናቀቅ  ለህዝቡ ሚስጥር በሆነ ህመም ህይወታቸው ሊያልፍ ችሏል፡፡ የሚኒሊክ ሞት ህዝቡን ክፉኛ ይረብሸዋል ሀገሪቱ ላይም አለመረጋጋት ያመጣል ተብሎ ስለታሰበ  ከሞቱ በኋላ ከ1902 -1906 ዓ.ም ድረስ   ሞታቸው ለህዝብ ሚስጥር ነበር በማለት ታሪክ ይነግረናል ፤ የጠቅላይ ሚኒስትር የአቶ መለስ ዜናዊም  ህዝቡ ነሐሴ 15 2004 ዓ.ም  አረፉ ተብሎ ቢነገረውም ፤ ሌሎች ጉዳዩን በቅርብ እናውቃለን የሚሉ ሰዎች ከሞቱ 40 ቀን አልፏቸው ሞታቸው ይፋ እንደወጣ ይናገራሉ፡፡

Tuesday, November 27, 2012

በእንተ ሐውልት

From :- Abel Wabella

ለአንዳንድ ኦርቶዶክሳውያን
(አንድ አድርገን ህዳር 19 ፤ 2005 ዓ.ም)፡- የሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስን ሐውልት መነሳት አስመልክቶ ጥቂት ያሳዘኑኝ ጉዳዮች አሉ፡፡ የመጀመሪያውሐውልቱ መነሳቱ ካልቀረ ቢነሳ ችግር የለውም” የሚለው ነው፡፡ ለኔ እንደሚገባኝ እንዲህ ማለት አቡኑ የከፈሉትን መስዋዕትነት ማቃለል እና ዋጋ ማሳጣት ነው ፡፡ ይህን የምልበት ምክንያት መጀመሪያ ስርዓቱ (ሕወሓት መር) ቤተ ክርስቲያኒቷን ሆን ብሎ ከስሯ ለመንቀል እንደሚንቀሳቀስ የታወቀ ነው፡፡ ከትጥቅ ትግል እስካሁን ድረስ ይህ አቋሙ አልተለወጠም ፤ ትላንት ደብረ ዳሞ ገብተው ቤተ ክርስቲያኒቷን እንዲሰልሉና እንዲሰነጥቁ የሐሰት መነኮሳት እያሰለጠነ ሲያሰርግ የነበረው ስብሐት ነጋ ዛሬ ደግሞ ትልቁ ስኬታቸው የኦርቶዶክስ እና የአማራ(አማራ የሚባል ነገር?) “የበላይነት”(quote unquote ) ማስቀረት እንደሆነ በድፍረት ተናግሯል፡፡ ይህ የሚያሳየው ስርዓቱ በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ የጠነከረውን በትር ቤተ ክርስቲያኒቷ ላይ እንደሚያሳርፍ ነው፡፡ ስኳር ፋብሪካ ሲባል ተነስቶ ዋልድባ ላይ መንገድ ሲባል ደግሞ ተነስቶ የሰማዕቱ ሐውልት የሚታይ ከሆነ ለምን ? ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡ በሰለጠነው አለም የአንድ ግለሰብ መኖሪያ አከባቢ አዲስ ነገር ሲሰራ  የሚሰራው ነገር በሰውዬው የወትሮ እንቅስቃሴ፣ አስተሰሳሰብ ልማድ ላይ ያለው ተጽእኖ ታይቶ በንድፍና በሞዴል ቀርቦለት የግል አስተያየቱን እንዲሰጥ ይጠየቃል፡፡ የአንድ ግለሰብ፣ የአንድ ነፍስ፣ የአንድ ንፋስ መብት! እኛ ግን ብዙ ሚሊዮኖች ሳለን እንደማንኛውም ተራ ዜና፣ እንደ ማንኛውም የሐማስ ሮኬት ከሬዲዮ መስማታችን እጅግ ያሳዝናል፡፡ እውነታው ይህ ሆኖ ሐውልቱ እንደማንኛውም ድንጋይ እናነሳዋልን ሲሉን ተሸቀዳድመንየሚመለስ ከሆነ” ብለን እሺ ማለታችን  እጅግ የሚያሳፍር ነው፡፡

“እኛ የክርስቶስን መስቀል በመካከላችን አድርገን መወያየት አለመቻላችን ያስተዛዝባል፡፡” መጋቢ ሀዲስ እሸቱ አለማየሁ


  • በሁሉ ነገር ላይ እኛ ቤተክርስቲያናችን እናስቀድም ፤ እኛ ከመነቃቀፍ ይልቅ ተከባብረን ፤ ከመራራቅ ይልቅ ተቀራርበን አንድ ሆነን ብንነጋገር የማይፈታ  ችግር የለም” አቡነ መርቆርዮስ ለሰላም ኮሚቴው የተናገሩት
  • አቡነ መርቆርዮስን ለማውረድ ቅዱስ ሲኖዶስ በተሰበሰበበት ወቅት የተጻፈውን ቃለ ጉባኤ እንዳየሁት    “እኔ ከዚህ አልስማማም ፤ የኔ ድምጽ በልዩነት ይያዝልኝ” ያሉ አቡነ በርናናስ ብቻ ነበሩ...... ዲ/ን ዳንኤል ክብረት
  • ትልቁ ነገር ሁለቱም ሲኖዶሶች ተገናኝተው ቤተክርስቲያኒቱን ማዕከል አድርገው የሚነጋሩ ከሆነ የማይፈታ ችግር አይኖርም፡፡” ሊቀ ካህናት ኃ/ሥላሴ
  • “ቤተክርስቲያን ያለ ፓትርያርክ የቅርብ አመራር ለብዙ ዘመን የቆየች ቤተክርስቲያን ናት ፤ ያለ አንድነቷ ግን መኖር ከባድ መሆኑን በተለያየ ጊዜ አይተዋለች፡፡” ዲ/ን ዳንኤል ክብረት
  • “አሜሪካ ሆነው ስንት ጆሮ በተከፈተበት ፤ ምላስ በበዛበት ፤ የዜና ማሰራጫዎች በበዙበት ቦታ ቁጭ ብለው ምንም አይነት ነገር ባለመናገራቸው በዘመኑ ቋንቋ እጅግ በጣም  አድናቂ ነኝ፡፡ የእስከ  ዛሬ ዝምታቸው ተገቢ ነው ፤ የአሁኑ ዝምታቸው ግን ይህን ያህል አስፈላጊ ነው ብዬ አላስብም ፡፡” መጋቢ ሀዲስ እሸቱ አለማየሁ

(አንድ አድርገን ህዳር 18 2005 ዓ.ም)፡የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ እሁድ 15/03/2004 ዓ.ም  ከአዲስ አበባ መጋቢ ሀዲስ እሸቱ አለማየሁ እና  ዲያቆን ዳኤል ክብረትን ከአሜሪካ ደግሞ ከሰላምና የእርቅ ኮሚቴ ሊቀ ካህናት ኃ/ሥላሴ አለማየሁ ከዴንቨር እና ጉዳዩ የማይመለከታቸው በቅዱስ ሲኖዶስ ስለ ምፍቅናቸው ተጠይቀው መልስ መስጠት ያልቻሉት አባ ሰረቀ ብርሀንን በማቅረብ አወያይቷል ፡፡ በዚህ ውይይት ቀሲስ ዘበነ ተገኝተው ሃሳባቸውን ይሰጣሉ ተብሎ ቢጠበቅም በውይይቱ ወቅት ሳይመቻቸው በመቅረቱ ውይይቱን ሊካፈሉ አልቻሉም ፡፡ 

Monday, November 26, 2012

ስለ ቤተክርስቲያን እርቀ ሰላም በአሜሪካ ድምጽ የተደረገ ውይይት



  •   “የመንግስት ተጽህኖ  መኖሩን ፈጽሞ አላውቅም” ብጹእ አቡነ ገብርኤ
  •   “መንግሥትን አባቶች ግልጽ ባለ ቋንቋ አናስገባም ብለው መከራከር የሚችሉበት ሁለተኛ እድል እግዚአብሔር ለዚች ቤተክርስቲያን የሰጠው አሁን ነው፡፡”
  •  “ፓትርያርክ የመሾምና የመምረጥ ጉዳይ ፍጹም መንፈሳዊ ነው ፤ እንኳን መንግሥት ይቅርና የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት  እኛ ነን መምረጥ የምንችለው ማለት አይችሉም ፤ ይህ እግዚአብሔር  የሚመርጠው ነገር ነው፡፡” ዶ/ር ተክሉ
  •   “መንግሥት ከቤተክርስቲያን ላይ እጁን አንስቶ አያውቅም” ዶ/ ር ተክሉ

(አንድ አድርገን ህዳር 16 2005 ዓ.ም)፡- አንድ አድርገን በአሁኑ ሰዓት ትልቅ መነጋገሪያ በሆነው በቤተክርስቲያኒቱ እርቀ ሰላም ዙሪያ በአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ አማካኝነት ህዳር 14 2004 ዓ.ም የተደረገውን ከሁለቱም ሲኖዶሶች አንድ አንድ አባት የተወከሉበትን እና በቤተክርስቲያን ዙሪያ በቂ እውቀት አላቸው የተባሉ ሁለት ዶክተሮች መካከል የቀረበውን ውይይት እንደሚቀጥለው አቅርበዋለች፡፡


ቀኖና ፈረሰ ሕገ ቤተክርስትቲያን ተጣሰ በሚል ሰበብ ለ20 ዓመታት የተለያዩትና እስከ መወጋገዝ የደረሱት የቤተክርስቲያኒቱ አባቶች ወደ እርቀ ሰላም እያመሩ መሆናቸው ቢታወቅም ቤተክርስቲያኒቱን ለሁለት የከፈለው ችግር መፍትሄ የማግኝቱ ነገር አጠያያቂ እየሆነ ችግሩም እየተወሳሰበ መምጣቱ ይነገራል ፤ ለምን ? መፍትሄውስ ምንድነው? 

Sunday, November 25, 2012

ቤተክህነት የቱሪዝም ተቋም ልትመሠርት መሆኗን አስታወቀች


በሔኖክ ያሬድ(From Reporter )
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአገር ውስጥና በውጭ አገር በተለይም በኢየሩሳሌም የሚገኙ ገዳማቷንና የቱሪስት መዳረሻዎቿን የሚያስተዋውቅ የቱሪዝም መምርያ ለመመሥረት በእንቅስቃሴ ላይ መሆኗን አስታወቀች፡፡ በተለይም ወደ ኢየሩሳሌም የሚደረጉ የምዕመናን ጉዞዎችን በኃላፊነት ለመምራትም አቅዳለች፡፡

በጠቅላይ ቤተክህነት የውጭ ግንኙነት መምርያ ኃላፊ መምህር ሰሎሞን ቶልቻ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ቤተ ክርስቲያኒቱ በያዘችው ዋና ዓላማ ከመንፈሳዊ አገልግሎቷና አገራዊ ልማት ተሳትፎ ባሻገር፣ በቱሪዝሙ መስክ ከአገልጋይነት ባለፈ ተጠቃሚ ባለመሆኗ የቱሪዝም መምርያን ለመመሥረት በእንቅስቃሴ ላይ ትገኛለች፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቷ እምነቷ፣ ቀኖናዋና ሥርዓቷም ሳይፋለስ ተከብሮ ትውልድ ተሻጋሪ እንዲሆን ለማስቻል የቱሪዝምና ቅርስ አገልግሎት ተጠናክሮ እንዲቀጥል በቅዱስ ሲኖዶስ መወሰኑን መምህር ሰሎሞን አስታውሰዋል፡፡ ለዚህም ተግባራዊነት የቱሪዝም መምርያ ማቋቋም አስፈላጊ በመሆኑ ቅድመ ጥናቶች እየተሠሩ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

Friday, November 23, 2012

የባቡር መስመሩና የሁለቱ ሐውልቶች እጣ ክፍል በፎቶ

ይህ ፎቶ የተነሳው በ14/03/2005 ዓ.ም ነው

ቆሞ ሰሪውን የሚታዘበው የምኒሊክ ሀውልት


ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድን በህይወት ኖረው የአቡነ ጴጥሮስ ሃውልት ይፈርሳል ቢባሉ ምን ይሉ ይሆን?


ሐውልቶቹንና ስራውን እየታዘቡ ያሉ ሰዎች

ታሪክን የኋሊት “የኢትዮጵያ ጥቁር ጠባሳ”




(አንድ አድርገን ህዳር 13 ፤ 2005 ዓ.ም)፡- “የእናት ምጥና አብዮት ምን ይዞ እደሚመጣ አይታወቅም” ይባላል ፤ አንድ ወዳጄ “የእናት ምጥና የአገር አብዮት አንድ ናቸው ፤ ሁለቱም ምን እንደሚያወልዱና ምን እንደሚያመጡ በርግጠኝነት መናገር አይቻልምና” ይላል ፤ እናቲቱ በድሮ ዘመን ወንድ ትውለድ ሴት ፤ ጤነኛ ልጅ ትውለድ በሽተኛ ፤ ተመራማሪ ትውለድ አማራሪ ፤ ጻድቅ ትውለድ ርኩስ ፤ መሪ ትውለድ ተመሪ ፤ መልካም ሰው ትውለድ ክፉ ሰው ከአንድ አምላክ በቀር ማንም አያውቅም፤ ሁሉም ነገር የሚገለጠው በጊዜ ሂደት ውስጥ ነው፡፡

Thursday, November 22, 2012

የሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ሃውልት ሊፈርስ ነው

  • የእምዬ ሚኒሊክ ሐውልትም ሊፈርስ ይችላል


(አንድ አድርገን ህዳር 13 2005 ዓ.ም)፡-  የግብፅ ቤተ ክርስቲያን ከአንድ ሺ ስድስት መቶ ዓመታት በኋላ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዕውቀት መንፈሳዊ ከእርሷ ተወልደው በእቅፏ ውስጥ ባደጉ ኢትዮጵያውያን ጳጳሳት እንድትመራ ፈቃዷን ስትገልጽ ከተመረጡት አባቶች አንዱ በመሆን ግንቦት 18 ቀን 1921 ዓ.ም. በእስክንድርያው መንበረ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ማዕረገ ጵጵስናን ተቀበሉ። ከዓመት በኋላም “አቡነ ጴጥሮስ ጳጳስ ዘምሥራቅ ኢትዮጵያ ተላዌ አሠሩ ለአቡነ ኢየሱስ ሞዓ” ተብለው ተሾሙ።



በ1928 ዓ.ም. አረመኔው የኢጣልያ ፋሺስት በግፍ አገራችንን ለመውረር ክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት በማለት ውቅያኖስ አቋርጦ በመምጣት ኢትዮጵያን ሲወርና ሕዝቧን፣ ሊቃውንቷን፣ ገዳማቷንና አድባራቷን በግፍ ሲጨፈጭፍ ያዩት ብፁዕነታቸው ወራሪውን ኃይል ከኢትዮጵያውያኑ አርበኞች ጋር በመሆን በጸሎት ሊዋጉት ቆረጡ። የወቅቱ የአገሪቱ መሪ ግርማዊ ንጉሠ ነገሥት በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ከአረመኔው ፋሺስት ጦር ጋር በመፋለም ላይ የነበረውን አርበኛ ለማበረታታት ወደ ማይጨው በሔዱ ጊዜ ብፁዕነታቸው ተከትለው ሔዱ። ከዚያ እንደ ተመለሱም በታላቁ የደብረ ሊባኖስ ገዳም ተሰባስበው የቤተ ክርስቲያን አምላክ በኢትዮጵያውያን ላይ የመጣውን ችግር እንዲያስታግሥ በጸሎት እየተጉ ወደነበሩት አባቶችና አርበኞች በመሔድ ለአገርና ለነጻነት መሞት ቅዱስ ተግባር መሆኑን በመስበክ ሁሉም እንዲጋደሉ ማሳሰብ እና ማትጋት ጀመሩ። ኋላም የገዳሙ መነኮሳትና የሰላሌ አርበኞች ይባሉ የነበሩት አርበኞች ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ተሳታፊ ሆኑ። ከዚያም አርበኞቹ የቻሉትን ሁሉ አድርገው ወደ ሰላሌ ሲመለሱ ብፁዕነታቸው አዲስ አበባ ቀሩ። ብዙም ሳይቆዩ በጠላት እጅ ተያዙ። ከጥቂት ጊዜ በኋላ በስምንት ጥይት አሁን ሃውልታቸው ከሚገኝበት ቦታ ዝቅ ብሎ ባለው ቦታ ላይ ሰማዕትነትን ተቀበሉ፡፡

Monday, November 19, 2012

የዋልድባ መነኰሳት “ኳሬዳ” በተሰኘ ትልና ምስጥ ተቸግረዋል

  • ለመነኰሳቱ የአስቸኳይ ጊዜ የምግብና የአልባሳት እርዳታ ጥሪ ቀርቧል
(አንድ አድርገን ህዳር 10 2005 ዓ.ም)- በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት ዓዲ አርቃይ ወረዳ የሚገኘው የጥንታዊው ዋልድባ ደልሽሐ ኪዳነ ምሕረት ማኅበረ ደናግል ገዳም ሴት መነኰሳት ኳሬዳ በተሰኘ ትልና በአካባቢው በብዛት በሚፈላው ምስጥ መቸገራቸውን ለገዳሙ የራስ አገዝ ልማት ርዳታ ለማሰባሰብ የተቋቋመው ኮሚቴ ገለጸ፡፡ ትሉ መነኰሳቱ ለዘመናት የኖሩባቸውን ጎጆ ቤቶች /የሣር መክደኛ/ ምቹ መራቢያ እንዳደረገው የተገለጸ ሲሆን ትሉን በምትገበው ኩቱ የተባለች ወፍ በሚራገፍበት ወቅት በመነኰሳቱ ቆዳ ላይ እያረፈ ሰውነታቸውን ያሳብጣል፤ ዕብጠቱ ከሚፈጥረው ሥቃይ ለመዳን መነኰሳቱ ሰውነታቸውን በምላጭ ስለሚበጡት ተጨማሪ ጉዳት እያስከተለባቸው ነው፡፡ በአካባቢው በብዛት የሚፈላው ምስጥ ሌላው የማኅበረ ደናግሉ ፈተና መኾኑ ሲሆን አረጋውያትና ሕሙማን መነኰሳት የሚረዱባቸውን የአልጋ ቆጦችና የቤት ቋሚዎች እየቦረቦረ በመጣል ለጉዳት እየዳረጋቸው መኾኑ ታውቋል፡፡