Monday, September 30, 2013

‹‹የበደልናትን ቤተክርስቲያንን እንክሳለን ፤ ይዘን የወጣነውን ህዝብ መልሰን እናመጣለን ፤ ላጠፋነው ጥፋትም ቤተክርስቲያኒቱ ይቅርታ ታድርግልን›› ተሀድሶያውያን


ከእንቁ መጽሄት እንዳገኝነው
(አንድ አድርገን መስከረም 20 2006 ዓ.ም)፡- ጉዳያቸው በቅዱስ ሲኖዶስ ተይዞ በመታየት ላይ የሚገኝው የበጋሻው ደሳለኝ እና የያሬድ አደመን ጉዳይ በእርቅ መንገድ መፍትሄ እንዲፈለግለት በመንቀሳቀስ ላይ የምትገኝው ዘማሪት ፋንቱ ወልዴ መሆኗን ከቤተክህነት አካባቢ ያገኝነው መረጃ ያመለክታል፡፡  መረጃው እንደሚያመለክተው በጋሻውና ያሬድ አደመ ‹‹የበደልናትን ቤተክርስቲያንን እንክሳለን ፤ ይዘን የወጣነውን ህዝብ መልሰን እናመጣለን ፤ ላጠፋነው ጥፋትም ቤተክርስቲያኒቱ ይቅርታ ታድርግልን›› ማለታቸውና እርቁን መፈለጋቸው ታውቋል፡፡

Friday, September 27, 2013

የእግዚአብሔርን ተዓምር ተመልከቱ



(አንድ አድርገን መስከረም 17 2006 ዓ.ም)፡- ቦታው ሶርያ ሀገር ነው፡፡ የቤተክርስቲያኑ ስም saydania ይባላል:: ቤተክርስቲያኒቱ እንደተለመደው የዘወትር ፀሎት ለህዝቡ ፤ ለዓለምም እያደረሰች ባለችበት ሰዓት አንድ ሰው ወደ አንድ መነኩሴ እማሆይ Marina Almaloof ቀርቦ ‹‹ስለት ለመስጠት ነበር እባክዎን ይሄን ብር ሳጥን ውስጥ ያስገቡልኝ›› ይላቸዋል  በእጅ የያዘውን 160. የሆነውን ሻማ ‹‹ይሄን ደግሞ በስዕለ ማርያም ፌት ያብሩልኝ እኔ በጣም ሰለምቸኩል ነው›› ይልና በፍጥነት ከቤተመቅደሱ ይወጣል ፡፡ መነኩሴዋም ክብሪት በማንሳት ‹‹አቤቱ የሰራዊት ጌታ የዚህን ሰው ስለቱን ተቀበለው›› እያሉ ክብሪቱን ጫሩ ፤ ሻማው ጫፍ አቀረቡት ሻማው ሳይቃጠል ክብሪቱ ተቃጥሎ አለቀ ፤ በድጋሚ ሞከሩ ሞከሩ ሻማው ባለመቃጠሉ እየተገረሙ ከወደ ቤተክርስቲያኒቱ ደጃፍ ጩህት ተሰማ መነኩሴዋም ወደ ጩህት ቦታው በፍጥነት ወጡ ፤ ከታች ከበስተመጨረሻ ደረጃው ላይ አንድ ሰው ወድቆ የሞተ ሰው ተመለከቱ፡፡‹‹ ይሄ አሁን ስለት የሰጠኝ ሰውየ አይደለምን?›› በማለት የተፈጠረውን ሁኔታ ለማስረዳት ስልክ ለአካባቢው ፖሊስ ደወሉ ፤ ፖሊስም በፍጥነት ቦታው ላይ በመገኝት ነገሩን አጣራ ፤ ሁኔታውን ሁሉ ከመነኩሴይቱ በመጠየቅ ተረዳ ፤ ልጁ ቤተመቅደስ ይዞ ገብቶ እንዲለኮስ የፈለገውን ሻማ ፖሊስ ተቀብሎ ሲመረምረው በውስጡ ዳይናሜት TNT የተባለ አደገኛ ተቀጣጣይ ፈንጆች የተሞላ ሁኖ አገኝው፡፡ ይህን ያደረገውን ሰው የሚያውቅ አልተገኝም ፤ ሰውየው በልብ ድካም ነው የሞተው ተባለ ፤ ወላዲተ አምላክ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ህዝቧንም ቤተክርስቲያኑንም በዚህ ተዓምር ታደገች ልመናዋ ምልጃዋ በእኛ ላይ  ይሁን አሜን! 

Sunday, September 22, 2013

“ይህ መስቀል የቤተክርስቲያኒቱ የክብር መገለጫ ነው” መጋቢ ሃዲስ ፍሰሃ


  • ለህዝብ የሚታየው ፓትሪያርኩ በተገኙበት ነው
  • በየእለቱ 3ሺህ ሰው በላይ ቦታውን እየጎበኘ ነው
(አዲስ አድማስ ቅዳሜ መስከረም 11 2006 ዓ.ም)፡- በአቃቂ ቃሊቲ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስትያን ከሰማይ ወረደ የተባለው መስቀል ፓትርያርኩ በተገኙበት ለህዝብ እንዲታይ መግቢያ መንገድ እስኪሰራ ድረስ የተራዘመ ሲሆን፣ በመስቀሉ ላይ የሳይንስ ምርመራ እንደማይፈቀድ ተገለፀ፡፡ ከሶስት ሳምንት በፊት በፍንዳታ ድምፅና በብርሃናማ ቀስተደመና ከሰማይ ወረደ የተባለው መስቀል፣ በሚቀጥለው ሳምንት መስከረም 19 ቀን ለህዝብ ይታያል ተብሎ የነበረ ቢሆንም፣ ፓትርያርኩ የሚገኙበት ስነስርዓት ለማዘጋጀት ጊዜው እንደተራዘመ የቤተክርስቲያኗ አስተዳዳሪዎች ተናግረዋል፡፡ መስቀሉ ለህዝብ የሚታየው ቅዱስ ፓትሪያርክ አቡነ ማቲያስ በተገኙበት ስነስርዓት መሆን አለበት መባሉን አስተዳዳሪዎች ጠቅሰው፤ መንገዱ ጭቃ ስለሆነ ጠፈፍ ብሎ ለመኪና እስኪስተካከል ድረስ ቀኑ መራዘሙን ገልፀዋል፡፡ ቀኑ ገና እንዳልተወሰነና ለፓትሪያርኩ ጋር ውይይት እየተደረገበት ነው ያሉት የቤተክርስቲያኒቱ አስተዳዳሪዎች፤ ስነስርዓቱን ህዳር 11 ቀን ለማካሄድ እንደታሰበ ጠቁመዋል፡፡

‹‹ማኅበረ ቅዱሳን አክራሪ ሆኖ የገደለው ሰው የለም›› ዲ/ን ዳንኤል ክብረት

 ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከዕንቁ  መጽሔት መስከረም 2006 ዓ.ም እትም ጋር ቆይታ አድርጎ ነበር ‹‹አንድ አድርገን›› ፍሬውን ከላይ ዝርዝሩን ከታች አድርጋ እንዲህ አቅባላችኋለች


·   ኢትዮጵያ ውስጥ ጠንካራ አመኔታ ያለው የዕምነት ተቋም የለም፤ ጠንካራ እምነቶች ግን አሉ፡፡
· ማኅበረ ቅዱሳን እስከ አሁን ድረስ አክራሪ ሆኖ ያመጣው ነውጥ፣ ያስነሳው ነገር፣ የደበደበው፣ የገደለው ሰው፣ ያቃጠለው ቤተ እምነት የለም፡፡
·  ማኅበረ ቅዱሳንን አክራሪ ለማሰኘት የሚያበቃ ምንም፣ አንድም መከራከሪያ ሊያመጡ አይችሉም፡፡ ከሳቸውም በፊት የነበሩት ሌሎች ሰዎች እንደ እርሳቸው ብለዋል፡፡
·         ማኅበረ ቅዱሳንን በተመለከተ የሚሰነዘሩ ሐሳቦች ምንጫቸው መታየት አለበት፡፡  ‹‹ቂጣም ከኾነ ይጠፋል፤ ሽልም ከኾነ ይገፋል›› እንደሚባለው በተያዘው ሐቅ መቀጠል ነው
·    ማኅበሩ አንድ የሚጎድለው ነገር ቢኖር ማስረዳት ነው፡፡ መልስ መስጠት እንጂ ቀድሞ የማስረዳት ነገር ውስጥ ብርቱ አይደለም፡፡
·        ‹‹ይህች ቤተ ክርስቲያን ተጠብቃ፣ ሥርዐቷን ይዛ ወደሚቀጥለው ትውልድና ዘመን መሻገር አለባት›› የሚሉትን አካላት ነው አሁን ‹‹አክራሪ›› ማለትና ዝም ማሰኘት ነው የሚፈለገው
·        በቤተ ክርስቲያኒቱ ታሪክ አክራሪነትን ሊያበቅል የሚችል መሬት አይገኝም፡፡
·        የምንመሠርታቸው ተቋማት ለምን እንደ ሐበሻ መድኃኒት ድብቅ እንደሚኾኑ ይገርመኛል
  •    ‹‹ መቻቻል›› የሚለውን አልቀበለውም…. ቻለው ተብለህ የምትኖረው ኑሮ ማለት ነው፡፡
  •    እኔ በኢትዮጵያዊነቴ የሙስሊም ወገኔን በዓል ገዝቼዋለኹ፡፡ ሙስሊሙም የእኔን በዓል ገዝቶታል፡፡ እርሱም በእኔ እምነት እድናለኹ፤ እኔም በእርሱ እምነት እድናለኹ፤ አላልንም እንጂ በባህላችን አንዳችን የሌላችንን በዓል ገንዘብ አድርገነዋል፡፡
  •    ለምን ሚዲያው ይለየናል? እኛ ያልተያየነውን ለምን የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የሚለያየን እላለኹ፡ በሕግ ደረጃ ብሔራዊ በዓል ነው ተብሎ ከተደነገገ በኋላ በሚዲያ በኩል ልዩነቱ ለምን ይመጣል?
  •    ኢትዮጵያውያን ከሥር ሆነን ያዳበርነው ከወደላይ ትልቅ ችግር ይፈጠርበታል፡፡
  •    መልካሙ ገድልም ደግሞ ከሦስት አካላት ጋራ የሚደረግ ነው፡፡ አንደኛ፡- ከራስ ጠባይዕ ጋራ፣ ሁለተኛ፡- ከሰይጣን ጋራ፣ ሦስተኛ፡- ከተለያዩ አካላት ማለትም ሃይማኖትኽን፣ ቤተ ክርስቲያንህን ወይም እምነትህን ለማፍረስ ከተነሡ ወገኖች ጋራ፣ ከመናፍቃን፣ ከከሐድያን፣ ከአላውያንና ከሌሎች አካላት ጋራ የምታደርገው ተጋድሎ ነው፡፡
  •  ‹‹ቀኝኽን ለሚመታኽ ግራኽን ስጥ›› የሚል ክርስትናን የምንከተል በመኾናችን እስከአሁን አባቶቻችን ሞተዋል እንጂ አልገደሉም፡፡

Monday, September 16, 2013

ድንቅ ስራውን መስክሩ





(መስከረም 4 2005 ዓ.ም አዲስ አድማስ ጋዜጣ)፡- በአቃቂ ቃሊቲ፣ በቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ፣ ባለፈው ነሐሴ 23 ቀን በቀስተ ደመና፣ በመብረቅና በነጐድጓድ ታጅቦ ከሠማይ እንደወረደ የተነገረለት መስቀል፣ በጳጳሳት የተጐበኘ ሲሆን፣ ከሁለት ሳምንት በኋላ ለህዝብ እይታ እንደሚቀርብ ተገለፀ፡፡ 

መስቀሉን ከወደቀበት ለማንሳት የሞከረ ወጣት ተስፈንጥሮ በወደቀበት ለ4 ቀን ራሱን እንደሳተ የሚናገሩ የቤተክርስትያኑ አገልጋይ፣ ከምሽቱ 9 ሰዓት ከፍንዳታ ጋር አካባቢው በብርሃን ተሞልቶ ስናይ የእሳት ቃጠሎ መስሎን ነበር ብለዋል፡፡ እያንፀባረቀ በሃይለኛ ግለት ያቃጥል ነበር የተባለው መስቀል፤ በማህበረ ቅዱሳን መሪዎችና በጳጳሳት የተጐበኘ ሲሆን የኢየሱስን ስቅለት የሚያሳይ ወርቃማ ቅርጽ ያለው ነው፡፡ ወደ አቃቂ ከተማ ከሚያስገባው ዋና የአስፓልት መንገድ በስተግራ በ10 ኪሎ ሜትር ርቀት ገላን ጉራ በሚባለው ስፍራ የዛሬ 5 አመት የተቋቋመው የገብርኤል ቤተክርስቲያን ውስጥ ነሐሴ 23 ቀን የክርስቶስ ሰምራ በአለ ንግስ እየተከበረ እያለ ከሌሊቱ 9 ሰዓት የተከሰተው ግርግር ነው የዚህ ሁሉ መነሻ፡፡ ከባድ የፍንዳታ ድምጽ የሰሙ እና የቀስተ ደመና ቀለማትን የተላበሰ ብርሃን የተመለከቱ ነገሩን ከዝናባማው የአየሩ ሁኔታ ጋር በማያያዝ ብዙም ትኩረት አልሰጡትም ነበር የሚሉት የቤ/ክርስትያኑ መጋቢ፤ በነጎድጓድና በኢትዮጵያ ባንዲራ ቀለማት የታጀበ መስቀል ከሠማይ ሲወርድ አይቻለሁ ብለዋል፡፡

Thursday, September 12, 2013

‹‹ኢትዮጵያን የሚያሰጋት የክርስቲያን አክራሪነት ነው›› ኡስታዝ ሀሰን ታጁ


  • የእንቅስቃሴው ሌላ አደጋ በሚስጢር እየተመራ መሆኑ ነው፡፡

(አንድ  አድርገን መስከረም 03 2006 ዓ.ም) ፡- ኡስታዝ ሀሰን ታጁ የእስልምና ሃይኖትን በተመለከተ በርካታ መጻህፍቶችን በትርጉም አሳትሟል ፤ በአሁኑ ሰዓት በእስር ላይ የሚገኙት በእነርሱ አጠራር ‹‹መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ›› ሃሳቡ ሲጀመር ፤ አሀዱ ተብሎ ነገር ሲጠቀለል ከፊት ከነበሩት 20 ተመራጭ ሰዎች ውስጥ ኡስታዝ ሀሰን ታጁ አንዱ ነው ፡፡ ‹‹‹አሁን የሙስሊሞች ጉዳይ ላለበት ደረጃ የፊት መስመር ቀያሹ ሰው አንዱ ኡስታዝ ሀሰን ነው›› በማለት ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁት ሰዎች ይናገራሉ ፤ የጀመሩት ‹‹ትግል›› መነሻው ሃይማኖታዊ ቢሆንም በሂደት እያደር ፖለቲካው ይዘት እንደተላበሰ በቃለ መጠይቁ ላይ ገልጿል፡ በዚህ ንቅናቄ መሰረትም መንግሥትን የመጣል ፍላጎት ያላቸው ዲያስፖራዎች እንደበረከቱ ሁኔታውን ወደ ሌላ ምዕራፍ ለማሸጋገር በታሳሪዎች ስም በአውሮጳ እና በመካከለኛው ምስራቅ በርካታ ብር በስማቸው እየተሰበሰበ እንደሆነ ገልጿል ፡፡ ኡስታዝ ሀሰን ታጁ በእርሱ አባልነት የተጀመረውን እቅስቃሴ እንዲህ ብሎ ገልጾታል፡፡

‹‹.. ወጣቱን ፤ የታሰሩትን የኮሚቴ አባላት ወንድሞቼንና እንቅስቃሴውን አውቀዋለሁ ብዬ አምናለሁ ፡፡ ብዙ ሰው ነገሩን መርምሮ እና ጥቅምና ጉዳቱን ለይቶ ሳይሆን በስሜት ነው የሚሄደው፡፡ ስሜት ጥሩ ነገር ሆኖ ግራና ቀኙን ማየት ግን ያስፈልጋል ፡፡ ስሜት ቁጭት እልህ የሚባሉት ነገሮች አስተሳሰብህን ከሸፈኑት እንደ አደንዛዥ እጽ ናቸው፡፡  ያሰክሩሃል ፤ የእንቅስቃሴው ሌላ አደጋ በሚስጢር እየተመራ መሆኑ ነው፡፡ ሚስጢራዊው እንቅስቃሴ መሀል ላይ ተጠልፎ ወደ አልተፈለገ አቅጣጫ ሊያመራ ይችላል፡፡ ›› በማለት ያለበትን ሁኔታ እና የወደፊቱን አስቀምጧል፡፡ እኛም ‹‹ከባለቤቱ በላይ ያወቀ ቡዳ ነው›› ብለናል፡፡

Friday, September 6, 2013

ሟችም ከመሞቱ በፊት ይህን ሲል ነበር




 

(አንድ አድርገን ጳግሜ 1 2005 ዓ.ም)፡- ሰሞኑን የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ባዘጋጁትና ‹‹አገር አቀፍ የሰላም እሴት ማጎልበቻ ጉባኤ›› ከነሀሴ 21 እስከ 24 2005 ዓ.ም በአፍሪካ ሕብረት መሰብሰቢያ አዳራሽ ማዘጋጀታቸው ይታወቃል፡፡ በዚህም ጉባኤ ከተለያዩ የእምነት ተቋማት እና ከፍተኛ የሚባሉ የመንግሥት ባለስልጣናት ተገኝተውበታል፡፡ በጉባኤው መክፈቻ ስነስርዓት ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የቀጥታ ሽፋን ማግኝት ችሎ ነበር ፤ በጉባኤው ላይ የተጋበዙት እንግዶችና ከሃይማኖታዊ ሁኔታዎች ጋር ቀጥተኛ ተያያዥነት ያላቸው ጉባኤተኞች ከአምስት ያላነሰ ጥናቶች ላይ እንደሚወያዩ መርሀ ግብሩን ከሚመሩት ሰዎች ምልከታ ተሰጥቶ ነበር፡፡ በመጀመሪያ ንግግር እንዲያደርጉ የተፈቀደላቸው ሁለት አባቶች ውስጥ አንዱ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያት ነበሩ፡፡ እርሳቸውም በትምህርተ መስቀል ካማተቡ በኋላ ያዘጋጇትን ሶስት ወረቀት ለታዳሚው በንባብ አቅርበዋል፡፡