Friday, May 24, 2013

የ‹‹አጥማቂው› መምህር ግርማ ስራ በቤተክርስቲያን ስርዓት እይታ



(አንድ አድርገን ግንቦት 16 2005 ዓ.ም)፡- መምህር ግርማ የማጥመቅ ስራቸውን ከጀመሩ ዓመታት ማስቆጠራቸው  ይታወቃል ፤ በየሄዱበት ብዙ ተከታይ ከማፍራታቸው በተጨማሪም ብዙ ነቃፊ ፤ ትምህርታቸውም ይሁን የማጥመቅ ስርአታቸው ከቤተክርስቲያን ውጪ ነው የሚሉ ሰዎች አልታጡም ፤ ‹‹አጥማቂው›› በተለይ በቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ሲያካሂዱት የነበረው ተግባር 17 ክፍል ያለው ፊልም ወደ ሲዲ በመለወጥ ለህዝበ ክርስቲያኑ ለገበያ አቅርበዋል፡፡ ምዕመኑ ቤተክርስቲያን ሄዶ ከማስቀደስ ይልቅ የእሳቸውን ሲዲ ከፍቶ ቤቱ ቁጭ ብሎ ‹‹ይገርማል›› እያለ የሚያይበት ጊዜም ነበር ፤ ከሀገር ውጪ ያሉ አብያተክርስቲያናት ‹‹አጥማቂውን›› አምጡልን በማለት የቤተክርስቲያኖቻቸው አስተዳዳሪዎች ያስጨነቁበት ጊዜም ነበር ፤ በአሁኑ ሰዓት በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ በብዙ ምዕመናን ቤት የ‹አጥማቂው›› ፊልሞች ይገኛሉ፡፡ ከቀናት በፊት የቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ካገዳቸው በኋላ ቤተክህነቱ እንዲህ በማለት ድጋፉን ገልጾላቸዋል ‹‹መምህር ግርማ ወንድሙ በደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ በሕገ ወጥ መንገድ የሚፈጽሙት ሕገ ወጥ የማጥመቅ ሥርዐትና የወንጌል አገልግሎት መኾኑን እየገለጽን የእምነታችን ተከታይ ሕዝበ ክርስቲያኑ ከዚህ እግድ ጋራ በተያያዘ የጸጥታ ችግር እንዳይገጥመው የሰበካ ጉባኤ /ቤት ጥብቅ ክትትል በማድረግ ውሳኔውን ተግባራዊ እንዲያደርግ እያሳሰብን የሚመለከታቸው የመንግሥት የጸጥታ አካላትም የቤተ ክርስቲያኒቱን ውሳኔ ተግባራዊ በማድረግ ረገድ አስፈላጊው ትብብር እንዲያደርጉልን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡››
 
ይህ በእንዲህ እያለ የ‹አጥማቂው›› የሲዲ ስራዎች በቤተክርስቲያ እይታ ምን ይመስላሉ ? እውን ትምህርታቸውም ሆነ የአጥምቆት ስርዓታቸው የቤተክርስቲያን ስርዓትን የተከተለ ነውን? ምዕመኑ ለምን አላስፈላጊ ንትርክ ውስጥ በ‹‹አጥማቂው›› አማካኝነት ሊገባ ቻለ? ‹‹መምህር›› ግርማስ ማን ናቸው ? እና በ‹‹አጥማቂው›› ዙሪያ የሚነሱ ጉዳዮችን ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ባሉበት ግንቦት 20 2005 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ በአራት ኪሎ ግቢ ገብርኤል አዳራሽ በምዕመናን ታላቅ መልስ የመስጠት ጉባኤ ተዘጋጅቷል፡፡ በ‹‹አጥማቂው›› ግራ ለገባችሁ ፤ ግራ ለተጋባችሁ ፤ ግራም ያጋባችሁ ሁላችሁም በጉባኤው ላይ ተጋብዛችኋል፡፡

42 comments:

  1. We have been hearing from church scholars and bishops aproving the authenticity of Memhir Girma's healing and teachings. He has been disclosing to us how the 'debteras', may be you are calling some of them 'liquawnt' here, kill people, take some one else's wealth using the devil; such 'liquawnts' are servants of the devil, not God. At any rate, if possible, please upload the program.

    ReplyDelete
  2. Minew Memhirin Bete Kirstian besetechachew maereg metrat amemachihu? Melake Menkirat Memhir Girma. Ayzoachihu atifru...

    ReplyDelete
  3. "ምዕመኑ ቤተክርስቲያን ሄዶ ከማስቀደስ ይልቅ የእሳቸውን ሲዲ ከፍቶ ቤቱ ቁጭ ብሎ ‹‹ይገርማል›› እያለ የሚያይበት ጊዜም ነበር" is biased to me. Memhir has been teaching us to participate in 'Kidasie' and beyond that by repenting to take the holly communion. For those of us living abroad, he was teaching that we abandon our hatred and go to church to worship only, not for other cases. He has been teaching us in a very nice way and I believe he has made lots of people to repent and partake in the holly communion.

    ReplyDelete
  4. አሁን ትክክለኛ ጎበዝ የኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ክርስቲያን የምትባሉት ልክ እንደ ቀጠሮአቹሁ ግንቦት 20 ወይም አሁን የትኛውም ጊዜ : አለን የምትሉትን ሁሉ እውነታ በግልፅ ብቅ ብላቹሁ እንደ መምህር ግርማ ሳትፈሩ ራሳቹሁን በግልፅ እንደ አባቶቻችን ተቃወሙ እንጂ በጓዳ ሆናቹህ ህዝቡን ግራ አታጋቡ : መቼም እውነት ከልቡ ያለች መች ይፈራል : ስለዚህ እውነቱን አውጡት እንጠብቃለን: አሁን ጎበዝ ልትባሉ ነው

    ReplyDelete
  5. egziabher lebona yestachu yehenen tehuf letafachu

    ReplyDelete
  6. ጥፋቱ ምንድን ነው: ንገሩኝ ልወቀው !!!
    እንህ አባት የሚዋጉት ያለው ሰይጣንን አይደለምን :
    እንህ አባት በእግር ብረት እስረው በአለንጋ ገርፈው የሰይጣን ማደሪያ የሆነውን ስጋ ጐዱን:
    እንህ አባት በጥንቆላ ሳይሆን የክ/እየሱስን ስም በመጥራት እና የቤ/ክ መጽሐፍትን በመጠቀም አይደለም እንዴ ሰይጣንን የሚያሳድዱ ያሉት:
    ቤተ ክርቲያንን የበደሉስ፤ ገዳም አፍራሾች፣ ጵጵስና በገንዘብ ገዥዎች (ስማቸውን ለጊዜው ልተወውና)፣ ምስላቸውን አስቀራጺዎች፣ ፎቷቸውን በመቅደሱ ውስጥ ሰቃዮች፣ ዘረኞች ፣ ሙሰኞች፣ አመንዝራዎች ...

    ReplyDelete
    Replies
    1. U r right mikegna hizb chiristina chiristos yastemaren fikir new mikegninet alneberm Egziabiher mastwalun yistachu Abatachin memhir Girma Edmewon yarzmew Amen.

      Delete
    2. God bless you....

      Delete
  7. Shame on you Andadirgen!. It has been long time since he starts the service. And He has lot of followers. where have been yet? Who is beneficial for this? Yerasachinin gemena new eyagaletachihu yalachihut. sintu menafik yehene yihichin agatami tetekimo sintun askobililotal. ere mastewal yinuren ebakachihu.

    ReplyDelete
  8. እናንተ እንደጠቆማችሁት የችግሩ ተጠቂ የአዲስ አበባ ምእመን ብቻ አይደለም:: የዓምደ ሃይማኖት ልጆችን አሁንም ዐምድ ያድርግልን እና እናንተ ደግሞ ሪፖርታዥ ነገር ብትሰሩበት ምንኛ ድንቅ ነበር? በዚህ ዘመን ሰንበት ት/ቤቶችን ያዘጋጀልን አምላክ ይክበር ይመስገን::

    ReplyDelete
    Replies
    1. በየ ሰንበት ት/ት ቤት ውስጥ የተሰገሰጋቹ የመናፍቃን ጥርቅም ሁሉ የተያዛቹ ቀን መዋረዳችሁ አይቀርም ነበርና መምህር ግርማን ለማጥፋት ስትሉ የራሳችሁን መጥፊያ እያነፈነፋችሁ መሆኑን ብትገነዘቡት ይበጃችሁ ነበር:: አሁን ግን ህዝበ ክርስትያኑ ማን ምን እንደሆነ ለይቶ ያወቀበት ዘመን ስለሆነ መንፈሳዊ ያልሆና መልእክታችሁን የሚቀበላችሁ አታገኙም... ታፍራላቹ::
      እናንተም "አንድ አድርገኖች " shame on you... የናንተን ብሎግ የማነበው ከዚህ ቀደም ስለ አለቃ አያሌው እና ስለ መምህር ተስፋዬ ሽዋዬ ስላቀረባችሁ ብቻ ነው....
      ለዚህ ለደሃ ህዝብ ትንሽ እንኹአን አታዝኑም????... ህዝቡ ስፍር ቁጥር ከሌለው የበሽታ አይነት ለምን ተፈወሰ ብሎ መታገል እውነትም ማን ከዲያቢሎስ ወገን እንድቆመ በግልጽ ያየንበት ወቅት ነውና እግዚአብሄርን እናመሰግናለን::
      ደግሞ አቅርቡት

      Delete
    2. Shame on you Andadirgen

      Delete
  9. betam tasazinalachihu!....maninetachihu ahun taweke....Melake Menkirat Memihir Girma Wondimu talak abat nachew!...endenante ayinet kehadiwoch bebezubet midir EGZEABHER ende CHERINETU yeseten talak,yetebareku Abat NACHEW!

    ReplyDelete
  10. igeziabeher aseteway libona yeseten.

    ReplyDelete
  11. እናንተ በቦታው ትልቅነትም ትንሽነት ሁሉ ላላቹሁ በመጠንሰስም፣ በቅናትም፣ በእገዳውም፣ በማወቅም ባለማወቅም ሁሉ ለተባበራቹሁ ሁሉ። ኢትዮጽያዊ ዳግማዊ ሐዋሪያ መምህር ግርማ በእውነት በፍቅር ያገለገሉት እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን ነው ። እኔ ለእናንተም የምለምናቹሁ የማሳስባቹሁ እንድታውቁት የማሳስባቹሁ የምለምንላቹሁ ስለ ድፍረታቹሁ፣ ስለ ክፋታቹሁ ፣ስለ በደላቹሁ ፣ስለ ሚስጥራዊ ተንኮላቹሁ ኢትዮጽያዊ ዳግማዊ ሐዋሪያ መምህር ግርማ በእውነት የገለገሉት እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ይቅር ይበላቹሁ ፣ በእውነት እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ይማራቹሁ !!..... በእውነት በእውነት ! አሜን!

    የመምህር ግርማ የፀሎታቸው በረከት ለእኛም ይድረሰን!

    ReplyDelete
    Replies
    1. Wey ethiopia! men aynet zemen new? ewnetegna yebetekrstian lijoch meslachehugn neber. Memher Girma yeserut tefat kale begelt zerzerachehu masawekna memenan enditebeku madreg sigeba kemeret tenesto ayn yaweta yewshet sem matfat enkuan endenante menfesawi negn lemil website kerto alemawi kehonu andand weshetamna websitoch enkuan altebekem neber. YASAZENAL.

      Delete
  12. tenakayu gerema ke'ahun behala ye'amlelakeh hezeb yemeyatalelebet gize abeka. geta lemeta kerbalena yeseu ewenet ewoku ke'hasetegn agelegay tetebeku. geta yaseben

    ReplyDelete
  13. Ene Milewu minewu minewu MAhibere Kidusan eskahun tiru tiru neger lebetechrstianachn eyaderegachihu ahun ehenin bemin aynet menetsir endayachihut alawukim EMEBRHAN EWUNETUN TASAYACHIHU TIGILETILACHIHU MIN ELALEWU. Eski lelawu kerto bezih tsihufachihu erasu hulum sewu comment misetewu egnih agelgay ewunetegna ena tikikilegna mehonachewun newu. ARE TEWU TEWU TEWU NEGEROCHIN ATINU EBAKACHIHU. ENEM BIHON ANDUA YE MAHIBERE KIDUSAN ABAL NEGN!!!Gin ene ehe lik newu biye alaminim. And tiyake alegn lenante TSEBEL YETETEMEKE HULU YIDINAL ENDE?? Yenante amelekaket hulum sewu ayidinim newu bicha lela hateta wust algegbam SILE EMEBETE NEWU YEMILACHIHU EGNIH SEWU MINIM HATYAT YELEBACHEWUM !!! ASTEWULU ASTEWULU ASTEWULU!!!!!!

    ReplyDelete
    Replies
    1. Mastewal eko sisetachew new. Enem ye Mahabere Kidusan abal negn. They are keeping so quiet and it's very interesting how everyting is going. Lenegeru endezih menfes kidusn kemesadeb zim maletu 100% yishalal. Memhir endehone ewnetegna Tsega Menfes Qidus yalachew sew nachew. Ayineteq engidih!!! Midre tenkolegna debtera hula endih yetenchachaw eko awde negestu siletenekabet new. Enesu yatemedutil fenji Memhir akeshefut!!! Ye Diabilosin sira endih gilitlit adirgew silastemaru new kifatu? Engidih diabilos ena tebabariwochu min tihonu? Shih debdabe bitisifu tsegachew ayineteq!!!

      Delete
  14. እናንተ በቦታው ትልቅነት፣ ትንሽነት ፣በተቃውሞ ሁሉ ለተሰለፋችሁ:-
    የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ባለሟል መምህር ግርማ ወንድሙ ካሉን ብዙ የኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ድንቅዬ ልጅ አንዱ ሲሆኑ ። በመምህር ግርማ ወንድሙ እና ሌሎችም በእውነት በቆሙ አባቶቻችን ቀልድ የለም !! ለማንም ሰው ፊት አንሰጥም !! እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ይረዳናል የጌታን ማዳን በመረጣቸው በመምህር ግርማ በኩል እንመሰክራለን። እውነቱን እግዚአብሔር ገልፆልናል :: የሐሰት ፍርድ የሚፈልጉትንና የተራቡትን ግራ የተጋባ ፍርድን የሚያሳዩንን አየን ተረዳናቸው…….. ። ትልቅ ብለን ያሰብናችሁ: ቀድማቹሁ ከታች እስከ ላይ በቦታው የተቀመጣቹሁ ግን በቅናትና በተንኮል የምትመላለሱ የምትደክሙ አውቀናቹሀል በናንተ አፈርን ።የደግና የቀና አባቾችን እናቶችን ወንድም እህቶችን ስም ክብር አትበክሉብን::
    በኢትዮጽያዊ ኦርቶዶክስ ተዋህዶነታችን ሁሌ እንኮራለን እናድጋለን ። ለእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አሰራር የጠመሙትን ግን ግብራቹሁ ይለያቹሀል , መደበቅም አትችሉም ጌታ ገልጦታልና ። አሁንም በተለመደ ድለላቹሁ አትረብሹን አምልኮታችንን አትረብሹን ። በእውነት ልቦና ሳትታመኑ ጥቅስና ሕግ መጥቀሳቹሁ አይዋጥልንም አይገባንም ። ስለዚህ ራሳችሁን መጀመሪያ መርምሩ ።
    1ኛ/ ራሳቹሁን በመጠየቅ 2ኛ/ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ እናንተን እንዲመረምር በማረግ
    እግዚአብሔር እውነቱን ይግለጥልን ። በእውነት ቆመው የፀደቁባትን የአባቶቻችን እና እናቶቻችን ያቆሙትን የኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ(እና ሁሉንም ኦርቶዶክስ ተዋህዶ) እግዚአብሔር ይጠብቅልን!!
    በእውነት ለቆሙትና ለመምህር ግርማ እግዚአብሔር ፀጋውን ያብዛላቸው!! አሜን! እኛንም ይባርከን! አሜን!

    ReplyDelete
    Replies
    1. I agree my brother. I don't expect from this guys. I repeat ጥቅስና ሕግ መጥቀሳቹሁ አይዋጥልንም I agree

      Delete
    2. Ewnet new. This article doesn't prove a single point. Yasazinale.

      Delete
  15. IT is really sad to hear this kind of thing from Andadregen. This guy fights devil. Not the church. Ether way I got healed. God saved me through this man. I learn about the bible and became orthodox from Muslim. I missed his preching. Thank you Jesus.

    ReplyDelete
  16. The Angry Ethiopian/ቆሽቱ የበገነውMay 30, 2013 at 7:18 AM

    I didn't trust this guy from the beginning. When I reject him, I was told I am not Orthodox and I don't believe in miracles.
    The fact is I am Orthodox Tewahido and it is in my blood because I can not be nothing else. watching some kind of pentae style role play infront of me shouldn't make me Orthodox or strengthen my faith. In my view, he is part of the 'ማርያም ነኝ' - 'ኤልያስ መትዋል' series of cults that has been creating some noises in Ethiopia under the nose of the leaders of the church and the woyane regime. That says a lot about who is leading the country and the church.
    ሁሉም ማኖ የሚያስነካ ሆኖ ነው ያገኘነው
    http://www.youtube.com/watch?v=JBG9MWaCfOo (ተመልከቱ የትግሬዎችን ዕቃ ዕቃ ጨዋታ)

    ReplyDelete
    Replies
    1. Koshtih dibin endale tiqerataleh enji ye Memhir Tsega endehone Kelay Kesemay new. Ayineteq engidih!!! Shih debdabe bitsaf. You seem to have more of a political passion than that of spiritual. So I say this is not a place for your rotten blogs. Memhirin kemesadebih befit esti for the last 28 years bematmeq, for the last 35 years bemastemar yasalefutin gize research adirgeh mermirew. Mastewalih simeles eko you will regret of bundling such a great father with the everyday cult we notice like you mentioned. Libona yistih.

      Delete
    2. ከዲያብሎስ ጋር ቆሽትህ ገና ይነዳል ። ቅናትና ምቀኝነትህን አስወግደህ ፣ንስሀ ገብተህ ፣የጌታን ባለማል ማንቋሸሽክን ትተህ በእውነት ካልተገዛህ ያገሬ ልጅ መብገን አይደለም ገና ትንቦለቦላለህ ። ምክንያቱም ግብረ ዲያብሎስ እየሆንክ ነው አንተና መሰሎችህ።ለእግዚአብሔር ርዳታ ማስተዋል ከቻልክ ጌታ ለድህነት እየጠየቀን ነው ። ግን እባክህን ጠመህ አትገኝ።
      መምህር ግርማ በእግዚአብሔር ሀይል ዛሬም ነገም ያገለግላሉ።

      Delete
    3. ቤ/ን የኦሮሞ የአማራ የትግሬ የጉራጌ...... ሳትሆን የሁሉም ናት.... በቃ የሁሉም:: የህንን እንኳን የመንፈስ ቅዱስ ድንጋጌ በአግባቡ ሳትረዳ እኚህን የሚያክሉ ታላቅ አባት ለመተቸት መነሳትህ በጣም ትገማለህ::

      Delete
  17. በቅናተኞች እና በምቀኞች ፣እራሳቸውን ደብቀው በቅናት በሚቃጠሉ ሰዎች ምኞኦትና ወሬ ህብረት እሩጫና ድካማችሁ ፣የእግዚአብሔር ክንድ ሊነቀንቁት አይችልም።ትደክማላችሁ ግን መጨረሻችሁ በቅናታችሁ ትረበሻላችሁ ። ጌታ የወደደውን መምህር ግርማንና ሌሎችም አባቶች እና እናቶች የእግዚአብሔር ሀይል ለዘላለም ከነሱጋር ትኖራለች ። እናንተ ሐሰትን ከልባቹህ እያፈለቃችሁ ። እግዚአብሔር በተግባር ይቅር ብሎ ያከበረውን የወደደውን ትከሳላቹሁ። ። ራሳችሁን መርምሩ አንተ በምላስህ ፣በወሬ ፣በክስ የምትፈጥን (እናንተ የምትፈጥኑ) ።እድሜልክህን እያንጎራጎርክ ግዜህን አትጨርስ። አስተውል ለምቀኞች ሀይል ሆነህ በተግባር መቆምህን ተመልከት። እግዚአብሔር ይቅር ይበለን/ ይበልህ::

    እግዚአብሔር ፀጋውን አብዝቶ በእውነት ለቆሙ ለመምህር ግርማ እና አባቶቻችን እናቶቻችን ወንድሞቻችን እህቶቻችን ይስጥልኝ/ ይስጥልን!!! እኛንም ይባርከን! አሜን!

    ReplyDelete
    Replies
    1. Keshtih Deben,You don't make sense at all. Memhir Girma uses God's and the Saints name as well as their images to heal. How is that comparable to cults??? Woye Gude!

      Delete
  18. God bless Memher Girma Wondimu...... Shame on http://andadirgen.blogspot.com/

    ReplyDelete
  19. Amlakin "Kindihin Etef" yemilew keto manew??? Memhir eko be Amlak yetemeretu ye Egziabher baria nachew!!! Tsega Menfes Qidus besachew adro dinq sirawun bisera eneho diabilos behailegnaw kenekenew. Aydelem yihenin lelam bitadergu Egziabiherin Kindihin etef yemilew aynorim. Berasachihu lay tiliq zendo eyetemetemachihu new. Meches bezih hulu yemiyalf moged andadirgenoch maninetachihu taye. Kesachew yiliq yetefetenachihut enante timeslalachihu. Ato Michael endehone "Asa Gorguari Zendo Yawetal" newuna negeru filu temezo gudu gehad honobetal. Min yibejew?!!!!

    ReplyDelete
  20. the true will not be barried and will come out soon with

    God will

    ReplyDelete
  21. ለመምህር ግርማ እግዚአብሔር ፀጋውን ያብዛላቸው!! አሜን! እኛንም ይባርከን! አሜን!
    I don't expect from this guys. I repeat ጥቅስና ሕግ መጥቀሳቹሁ አይዋጥልንም I agree

    ReplyDelete
  22. እናንተ በቦታው ትልቅነት፣ ትንሽነት ፣በተቃውሞ ሁሉ ለተሰለፋችሁ:-
    የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ባለሟል መምህር ግርማ ወንድሙ ካሉን ብዙ የኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ድንቅዬ ልጅ አንዱ ሲሆኑ ። በመምህር ግርማ ወንድሙ እና ሌሎችም በእውነት በቆሙ አባቶቻችን ቀልድ የለም !! ለማንም ሰው ፊት አንሰጥም !! እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ይረዳናል የጌታን ማዳን በመረጣቸው በመምህር ግርማ በኩል እንመሰክራለን። እውነቱን እግዚአብሔር ገልፆልናል :: የሐሰት ፍርድ የሚፈልጉትንና የተራቡትን ግራ የተጋባ ፍርድን የሚያሳዩንን አየን ተረዳናቸው…….. ። ትልቅ ብለን ያሰብናችሁ: ቀድማቹሁ ከታች እስከ ላይ በቦታው የተቀመጣቹሁ ግን በቅናትና በተንኮል የምትመላለሱ የምትደክሙ አውቀናቹሀል በናንተ አፈርን ።የደግና የቀና አባቾችን እናቶችን ወንድም እህቶችን ስም ክብር አትበክሉብን::
    በኢትዮጽያዊ ኦርቶዶክስ ተዋህዶነታችን ሁሌ እንኮራለን እናድጋለን ። ለእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አሰራር የጠመሙትን ግን ግብራቹሁ ይለያቹሀል , መደበቅም አትችሉም ጌታ ገልጦታልና ። አሁንም በተለመደ ድለላቹሁ አትረብሹን አምልኮታችንን አትረብሹን ። በእውነት ልቦና ሳትታመኑ ጥቅስና ሕግ መጥቀሳቹሁ አይዋጥልንም አይገባንም ። ስለዚህ ራሳችሁን መጀመሪያ መርምሩ ።
    1ኛ/ ራሳቹሁን በመጠየቅ 2ኛ/ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ እናንተን እንዲመረምር በማረግ
    እግዚአብሔር እውነቱን ይግለጥልን ። በእውነት ቆመው የፀደቁባትን የአባቶቻችን እና እናቶቻችን ያቆሙትን የኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ(እና ሁሉንም ኦርቶዶክስ ተዋህዶ) እግዚአብሔር ይጠብቅልን!!
    በእውነት ለቆሙትና ለመምህር ግርማ እግዚአብሔር ፀጋውን ያብዛላቸው!! አሜን! እኛንም ይባርከን! አሜን!

    ReplyDelete
  23. minew 'yere selasie'agelglot sijemiru satnegrun.beigziabher sira atidesetum.

    ReplyDelete
  24. ሰብሳቢዎች ወዴት ሄዳቹሁ ? 2 ወር ሊሆናቹህ ነው 2 ወር ሙሉ ሰፊ አዳራሽ አጣቹሁ? ለምን ሰፋፊ አዳራሽ እኮ አሉን ::ለምን እነሱን አትጠቀሙም:: አዳራሽም እኮ አያስፈልጋቹሁም በሰበካ ጉባኤ መድረክ ላይ ማስተላለፍ ትችላላቹሁ? እውነታቹሁን ለመስማት በጣም ናፈቀን?
    እውነት የያዘ እኮ እውነቱን በግልፅ ለመናገር በሰአት ይፋጠናል :: የናንተ ተኛ እኮ ለነገሩ ውሸትን የያዘ በእውነት ሲጠየቅ ያልሆነ ምክንያት እየሰጠ ግዜ እያራዘመ ማረሳሳት የባህሪው ነው:: ዲያብሎስም እንዲህ እኮ ነው በእውነት ቦታ ሲጠየቅ ድራሹም አይገኝም:: ግን በለመደው መድረክ ግን የሱን እውነት ብሎ የፈበረከውን አሳምሮ ሲነዛ ጊዜ ይፈጃል ትውልድ ግራ ያጋባል:: ስለዚህ መልስ እንጠብቃለን

    ReplyDelete
  25. በየ ቤተ አብያተ ክርስትያናት ውስጥ የተሰገሰጋቹ የደብተራና(አስማተኛና) የመናፍቃን ጥርቅም ሁሉ የተያዛቹ ቀን መዋረዳችሁ አይቀርም ነበርና መምህር ግርማን ለማጥፋት ስትሉ የራሳችሁን መጥፊያ እያነፈነፋችሁ መሆኑን ብትገነዘቡት ይበጃችሁ ነበር:: አሁን ግን ህዝበ ክርስትያኑ ማን ምን እንደሆነ ለይቶ ያወቀበት ዘመን ስለሆነ መንፈሳዊ ያልሆና መልእክታችሁን የሚቀበላችሁ አታገኙም... ታፍራላቹ::
    እናንተም "አንድ አድርገኖች " shame on you... የናንተን ብሎግ የማነበው ከዚህ ቀደም ስለ አለቃ አያሌው እና ስለ መምህር ተስፋዬ ሽዋዬ ስላቀረባችሁ ብቻ ነው....
    ለዚህ ለደሃ ህዝብ ትንሽ እንኳን አታዝኑም????... ህዝቡ ስፍር ቁጥር ከሌለው የበሽታ አይነት ለምን ተፈወሰ ብሎ መታገል..... እውነትም ማን ከዲያቢሎስ ወገን እንድቆመ በግልጽ ያየንበት ወቅት ነውና እግዚአብሄርን እናመሰግናለን::
    ደግሞ አቅርቡት

    ReplyDelete
  26. እግዚአብሔር ይባርክህ።

    ReplyDelete