Tuesday, December 31, 2013

ሊያዩት የሚገባ የቴሌቬዥን መርሐግብር ፡ ጥር 25 2006 ዓ.ም

    • ሙሉ መርሀ ግብሩን ጥር 25 2006 ዓ.ም በአኮቴት የቴሌቪዥን መርሐ ግብር ላይ የሚተላለፍ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን
     
  • አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወይን ተክለው ለ12 ዓመታት በቦታው በመቀመጥ ሲጸልዩበት የነበሩበትና በርካታ ተዓምራትን ያከናወኑበት ቦታ ያዩበታል፡፡
  • ጻድቁ አቡነ ህጻኑ ሞአ የተወለዱበትና እንደ በሬ ተጠምደው በማረስ ገድላቸውን የፈጸሙበት ታላቅ ስፍራን ይመለከቱበታል፡፡
  • የቦታውን የቀደመ ታሪኩን ያውቁበታል ፤ ዛሬን ያዩበታል ፤ ነገን ያሳስብዎታል፡፡


(አንድ አድርገን ታህሳሥ 23 2006 ዓ.ም)፡- አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከኢትዮጵያውያን አበው መካከል በእግዚአብሔር ቸርነት ተነሥተው ከሐዋርያ ማዕረግ  የደረሱ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያንን ተስፋ ያደሱ ታላቅ አባት ሲሆኑ በሃያ ዓመት ዕድሜያቸው ጨለማ የሰለጠነባትን ክፍል ብርሃን እንድትሆን ‹‹አዲስ ሐዋርያ አድርጌ ሾሜሃለሁ›› ሲል ያከበራቸውና ለሾማቸው ‹‹ተክለ ሃይማኖት›› ብሎ ስም ለሠየማቸው ለፈጣሪያቸው ሕይወታቸውን  አሳልፈው ከሰጡበት ጊዜ ጀምሮ ያለ ጽልሁት ያለ ሐኬት በርዳታ በማስተማር በሰማዕትነት ፤ በድንግልና ፤ በምንኩስና ፤ በተባሕትዎና በልዩ ልዩ ተጋድሎ ሰማንያ ዘመን ሃይማኖቸውን ጠብቀው ፤ ፈጣሪያቸውን አገልግለው ፤ ገድላቸውን ካጠናቀቁ በኋላ በመቶ ዘመን ዕድሜያቸው በደብረ ሊባኖስ ገዳም አርፈዋል፡፡  

Monday, December 30, 2013

ፓትርያርኩ ስለ እምነታቸው የከፈሉት ዋጋ



(አንድ አድርገን ታህሣሥ 21 2006 ዓ.ም)፡- ኢትዮጵያ ብዙ መከራዎችን አሳልፋለች ፤ ብዙዎቹ መከራዎች ከውጭ ወራሪዎች ቢደረሱም ከውስጥ ሀይሎችም ከደረሰው ጥቃት ያልተናነሰ መከራ በቤተክርስትያንና በሀገር  ላይ ብዙ መከራ ደርሷል ፤ ይህች ቤተክርስቲያን ከዘመነ አክሱም ጀምሮ አሁን እስካለንበት የኢህአዴግ ዘመን ድረስ ብዙ መንግስታትን አሳልፋለች ፤ ፈሪሀ እግዚአብሔር ያላቸው ነገስታት ለቤተክርስትያን እና ለህዝበ ክርስትያን በርካታ መልካም ተግባሮችን አከናውነው ወደማይቀረው አለም አልፈዋል ፤ ስማቸውም በየዘመኑ በመልካም እየተጠራ ትውልድም የሚዘክራቸው እስከ አሁን ድረስ አሉ ፤ ሌሎች ደግሞ የምትጠፋ መስሏቸው ጦር መዘውባታል ፤ በዘመናቸው ቤተክርስትያኒቷን ለማፍረስ ድንጋይ  አንስተውባታል ፤ አሳት ለኩሰውባታል ፤ ጦር መዘውባታል ፤ እርሷ ግን የመጣውን መከራ ተቋቁማ እጃቸውን ያነሱባትን ወደ ኋላ ትታ አሁን እኛ ትውልድ ላይ ደርሳለች፡፡

Tuesday, December 24, 2013

በኩክ የለሽ ገዳም ሁከት የፈጠረው የኤልያሳውያን ተከታይ በገንዘብ ተቀጣ



(አንድ አድርገን ታህሣሥ 16 2006 .)- አቶ አበበ ነጋሽ የሚባል ሰው በደብረ ብርሃን በምትገኝው ኩክ የለሽ ገዳም ውስጥ ትውልድ አልቋል› ፤ ‹8ተኛው ሺ ደርሷል› ፤ ‹ትውልድ ሊቀጠፍ ነው› ፤ ‹ኤልያስ ወደ ምድር ወርዷል› ብሎ ሲሰብክ ተይዞ ‹የሌላ ሃይማኖት ተከታይ ሆኖ ሳለ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ገዳም ስብከት በማከናወንና የሃይማኖት ተከታዮች ውስጥ ሁከት በማነሳሳት›› እና ተያያዥ ክሶች ቀርበውበት ደብረ ብርሃን ፍርድ ቤት መቅረቡን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ይህ ሰው በወቅቱ ሃይማኖታዊ ስነሥርዓቱ እንዲታወክ እና ረብሻ እንዲፈጠር አድርጎ ነበር፡፡ ከቦታው በደረሰን መረጃ መሰረት አቶ አበበ ነጋሽ ላይ የተመሰረተው ክስ የተመለከተው ፍርድ ቤት ጥፋተኝነቱን በማረጋገጥ ባሳለፍነው ሳምንት በእስር የቆየባቸውን 40 ቀናት ከግምት ውስጥ በማስገባት የአንድ ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ፈርዶበታል፡፡
“የማህበረ ስላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ” ማህበር አባላት አሁንም ድረስ ከፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሕጋዊነቱን የሚያረጋግጥና በመንግስት ዘንድ እውቅና ያለው የእምነት ተቋም ሳይሆን ስሙን ከመሬት በማንሳት በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተክርስቲያናት እና ገዳማት ላይ አስተምህሯቸውን ለመጫን እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ በአሁኑ ሰዓት በባለፉት ሦስት ዓመታት በሰሩት ስራ ባፈሯቸው ጭፍራዎቻቸው አማካኝነት ጊዜን እየጠበቁ በየቦታው ሁከት እያስነሱ ይገኛሉ፡፡ ቤተክርስቲያኒቱ እነዚህ ሰዎች በተለያዩ ቦታዎች ላይ እያደረሱት ያለውን ጉዳት ከግምት ውስጥ በማስገባት በሕጋዊ መንገድ የምትጠይቅበት ምዕመኑንም ከውዥንብር የምትታደግበት ጊዜ እስኪመጣ ድረስ ሁሉም በያለበት እነዚህን ሰዎች ሊቃወማቸውና ከተቻለም እንደ ደብረ ብርሃን ወጣቶች ከነሥራቸው ወደ ፍርድ አደባባይ ሊያቀርባቸው ይገባል እንላለን፡፡

እግዚአብሔር ቤተክርስቲያንን ይጠብቅልን

Monday, December 23, 2013

በይቅርታ የሚታለፍ ተሐድሷዊነት ወይም ምንፍቅና ይኖር ይሆን?




ከሚካኤል ጎርባቾቭ

  • በነገረ ድኅነት፣ በነገረ ማርያምና በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ላይ ሲነገሩ የነበሩትን የሰውዬውን ስህተት ችላ በማለት በይቅርታ ለማለፍ ብቻ ከተሞከረ ሃይማኖታዊ ለዘብተኛነት ከአባቶቻችን እየተማርን መሆኑ መዘንጋት የለበትም
  • የኢትዮጵያ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ ሃይማኖታዊ ስህተት ተገኝቶበት በይቅርታ የታለፈ አንድም ሰው የለም

(አንድ አድርገን ታህሣሥ 15 ፣ ታህሳስ 06 2006 .ም)፡-  ይሄ ሰው በቤተ ክርስቲያን መድረክ ላይ እንዳሻው እንዲሆንና ብሎም በማወቅም ይሁን ባለማወቅ አንዳንድ ምዕመናን እንዲከተሉት ዕድልን ያገኘበት ሁለት ወሳኝ አጋጣሚዎች ነበሩት፡፡ የሰውዬው ታሪክም ከዚህ የሚጀምር ይሆናል፡፡ የመጀመሪያው ምርጫ 97 ተከትሎ ቅንጅት በብዙኋኑ ሕዝብ ዘንድ ተዓማኒነት ማግኘቱና ሕዝቡም ገዢውን ፓርቲ ኢህአዴግን /መንግሥትን/ ተቋዋሚ በመሆኑ ወቅታዊውን ሀገራዊ ትኩሳት ተገን በማድረግ የቤተ ክርስቲያኒቱ ልጆችም እንደ ዜጋ የድጋፉና የተቃውሞው አካል መሆናቸውን ሰውዬው በመረዳቱ የአብዛኛውን ሕዝብ ስሜት የተከተለ የመንግሥት ተቃውሞን ማሰማቱ ነው፡፡

Saturday, December 21, 2013

ቤተ ክርስቲያን ካሽ ሬጅስተር ልትጠቀም ነው

  • ምእመናን ለሚከፍሉትና ለሚሰጡት ገንዘብ ደረሰኝ የመጠየቅ ልማድ ሊኖራቸው ይገባል
  • ድብቅሙዳየምጽዋትማስቀመጥ፣በዣንጥላናበምንጣፍገንዘብመለመንይከለከላል

(አዲስ አድማስ ታኅሣሥ 12 2006 ዓ.ም)፡-  በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማት፣ አድባራትና አብያተ ክርስቲያናት የካሽ ሬጅስተር ማሽንን ለገቢ መሰብሰቢያነት ለመጠቀም  ቅድመ ዝግጅት እያደረጉ እንደሆነ ተገለጸ፡፡  

ዘመኑን ያልዋጀውንና ጥራት  የጎደለውን፣ ለሙስናና ብክነት የተጋለጠውን የቤተ ክርስቲያኒቱን የፋይናንስ አሠራርና ቁጥጥር ችግር፤ ግልጽነት፣ ወጥነት፣ ተቀባይነትና ተጠያቂነት ባለው የፋይናንስ አያያዝ ሥርዐት ለመቅረፍና ለማድረቅ ያስችላል፤ በሚል በቀረበው የሀገረ ስብከቱ የሒሳብ አያያዝ ፖሊሲና ዝርዝር የአፈጻጸም መመሪያ ረቂቅ ላይ እንደተጠቀሰው÷ በማንኛውም መንገድ የተሰበሰበ ገንዘብ፣ ሕጋዊ የገቢ መሰብሰቢያ ደረሰኝ ወዲያውኑ ሊቆረጥለት የሚገባ ሲኾን ይህም በዋናነት በካሽ ሬጅስትር ማሽን እንደሚከናወን ተመልክቷል፡፡

ፖለቲካና ሃይማኖተኝነት የሚያቃርናቸው ነገር አለን?

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
                                            amsalugkidan@gmail.com 
(አንድ አድርገን ታህሳስ 13 2006 ዓ.ም)፡-ፖለቲካ የሚለው ቃል የባዕድ ቃል ነው እምነተ-አሥተዳደር ማለት ነው፡፡ ከባዕድ ከመምጣቱም ቃሉንና ተግባሩን በመልካም ጎኑ ቀምሰን ሳናጣጥመው ወዲያውኑ ምሬቱን ስላሳየን ለቃሉና ለተግባሩ መልካም ስሜት የለንም፡፡ አንድ አባባልም ፈጥረንለት ከሥነ-ቃሎቻችን ቀላቅለንለታል ‹‹ፖለቲካንና ኮረንቲን በሩቁ ነው›› የሚል፡፡ በእርግጥ ግን ፖለቲካን ርቆ መራቅ ይቻላል? ለዚህ ቃልና ለተግባሩ ባለን ጥሩ ያልሆነ አመለካከት የተነሣ ፖለቲካ ያለውን የሀገርንና የሕዝብን እጣ ፈንታ የመወሰንን ያህል ግዙፍ አቅምና ሚና ዘንግተን ፖለቲካንና ፖለቲከኛነትን ጭንቅላታችን ውስጥ የጭራቅ ምስል ሥለን በመፍራት በመጥላትና በመሸሽ በዜግነታችን ለሀገራችን ልናበረክተው የሚገባንን ተግባርና አገልግሎት እንዳናበረክትና ሀገሪቱም በፖለቲካ ምክንያት ከሚከሰቱ ትብትብ ችግሮች እንዳትወጣ አድርጓታል፡፡

       

Monday, December 16, 2013

በጠወለገው የዘመናችን የሃይማኖት አባቶች ምግባር ፊት ፡- የአራቱ አባቶች ገድል


ከብርሀኑ ደቦጭ

(የቀድሞ የአዲስ ነገር ጋዜጣ ቋሚ ጸሐፊ እና የታሪክ ምሁር)
  • የሞራል ስብዕናቸው ምሣሌነት የሚያንሰው የዘመናችን የሃይማኖት አባቶችም ስለ ሃይማኖቱ መሪዎች የሚያደክመውን ብቻ በመስማት የተዳከመውን ምዕመናንን ዘወር ብለው ትላንትን እንዲመለከቱ በር የሚከፍት ነው፡፡
  • በግዕዝ የተጻፉትን  በአማርኛ እንድናገኛቸው በማድረጉ ባሻገር ራሳቸው ገድላት ያላቸውን ዋጋ እንድናስብና እንድንነጋገር አድርጎናል፡፡
  • ዲ/ን ዳንኤል ገድላቱን እንድናገኛቸው ያደረገ ብቻ ሳይሆን ከተለያዩ ምንጮች ባሰባሰባቸው መረጃዎች አማካኝነት የምናውቃቸውን አካባቢዎች ፤ በምናውቃቸው ማሳያዎችና ፤ በታወቁ ማመሳከሪያዎች ወደ ተጨባጭ ዕውቀት ለመቀየር ያደረገው ጥረት ጥሩ ነው፡፡
  • በሸዋ እና በትግራይ የነበረውን ግንኙነትና  ቅርበት ብዙ የሚያስታውስና  አሁን በተወሰኑ የሁለቱ አካባቢ ሰዎች  ነን የሚሉ ቀንደኞች የሚቀነቀነውን ልክ የለሽ ሽኩቻ ለመታዘብ ዕድል የሚሰጥ ነው፡፡
  • አቀራረቡ በዘመኑ የታሪክ ጥናት ያለብንን ክፍተት ለመሙላት የታሪክን የፊሎሎጂ ስነ ዘርፍ ጥናቶች የመተጋገዝን ጥቅም ልብ እንድንል ያደርገናል፡፡
  • በቤተክርስቲያን አካባቢ በሚፈጠሩ ችግሮች ዙሪያ አዘውትሮ ሃሳቡን ሲያካፍለን የቆየበት የእሱም ሆነ  ሌሎች ልፋት ብዙም ለውጥ ያመጣ ስላልሆነ የነዚህን ሰዎች ታሪክ በገድላቸው አማካኝነት  በመዘከር ፤ የሚጠብቀውን የሞራል ስነ-ልክ በማሳያ ያመላከተ ነው
  • የፕ/ር ጌታቸው ኃይሌን ጨምሮ በግርጌ ማስታወሻ የሚያነሳቸውና የሚከተላቸው ሙግቶች  ፤ ክርክሮችና ማስረገጫዎች ዲ/ን ዳንኤል  የነ ፕ/ር ታደሰ ታምራትን  ፈለግ ለመከተል የሚሻ መሆኑን ያመለክታሉ፡፡
  • ዲ/ን ዳንኤል ገድላቱን የተጻፉበት ምክንያት ከሃይማኖት አይን በዘለለ አለማየቱ ሌሎች ምክንያተ ጽሕፈቶችን ለመቃኝት ጥረት አላደረገም ፤ ስለዚህም ከተጠቀሱት አባቶች ታሪክ የዘለለ ፋይዳ ሲፈልግ አናይም፡፡
  • በየገድላቱ እንደ ተዓምራት የሚቆጥሩትን አማኞች እንዳለ ሊወስዱት ይችላሉ፡፡ በአንጻሩ ሌሎች ደግሞ መጽሐፉን የማንበብ ፍላጎታቸውን ሊፈታተን ይችላል፡፡
(አንድ አድርገን ታህሳስ 08 2006 ዓ.ም)፡- ዲ/ን ዳንኤል ከጋዜጦች ፤ መጽሔቶችና ድረ-ገጾች ያሰባሰባቸውን ጽሁፍ ያሳተመባቸውን መጻፍት ጨምሮ  በርካታ ስራዎችን  (በአብዛኛው በሃይማኖት ላይ  ያተኮሩ) ለህዝብ አቅቧል፡፡ በዚህም ምክንያት ይህንን ሁሉ በምን ጊዜ ሰርቶት  ነው የሚሉና የሚደነቁ አሉ፡፡ ከጋዜጣና መጽሔት ያሰባሰባቸውን  እየደጋገመ ማሳተሙ  ደስታ ባይሰጠኝም ፤ እኔም በዚህ ምክንያት  ከሚገረሙት መካል ነኝ ፡፡ በእርግጥ ከጋዜጣ እና መጽሔት  ወስዶ በማሳተሙ ተቆራርጦ  የወጣውን በአንድ ቦታ  እንዲገኝ የማድረግ  ፋይዳውን አልዘነጋሁም ፡፡ ለማንኛውም አዲሱን የዲ/ን ዳንኤል መጽሐፍን የጽሐፊው ልፋት ከመቼውም በበለጠ መሆኑንና  የሥራውም ዋጋ  የዛኑ ያህል  ከፍ ያለ እንደሆነ ለማስተዋል ችያለሁ፡፡ የዛሬው አጠቃላይ አስተያየቴ  በዚሁ መጽሀፍ ዙሪያ ይሆናል፡፡

Wednesday, December 11, 2013

“ይቅርታ አድርጉልን ?” :- የቤተ ክህነቱ ተቋማዊ ድቀት ምስክሮች ስልተ ነገር


  •  ‹‹በነበረው ሒደት በተለያየ ምክንያት ለበደላችኹን ሁሉ ይቅርታ አድርገንላችኋል ፤ እናንተም ይቅርታ አድርጉ ›› በጋሻው ደሳለኝ ባለፈው እሁድ በሀዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ገዳምምእመናን ያደረገው ንግግር
  • በአንድ  የቅዱስ ሲኖዱስ ምልዐት ጉባኤ ውሳኔ  ሊያበቃ የሚችልን ጉዳይ አንዲትዘማሪት›  እስክትገባ መፍቀድ  ትልቋን ቤተ ክርስቲያንን  አይመጥንም
  • ልጆቹ እኮ ምስጢረ ሥላሴን “ሥላሴ አትበሉእያሉና ምስጢረ ሥጋዌን ”…ክርሰቶስና ዲያብሎስ ቁማር ተጫወቱ…” እያሉ አላግጠው ነበር፡፡
  • የይቅርታው ሒደት ቀኖናዊ ነው የሚለው ተገቢ ቢሆንም የመንፈሳዊ እና አሰተዳደራዊ ቀውሱን ተራራ  እንደማይንደው ጥርጥር የለውም ፡፡ ቀውሱ  ይቅርታ አድርጉልንይጠልቃል ፤ ይረዝማልም ፡፡


  • እንዲህ ያለ ዜና ከሰሞኑን ሰማን፡፡ አንዱ "የበቃ" ከየት መጣ ሳይባል ድንገት ሲያውከው ሲያተራምሰው በከረመው መድረክ ብቅ ብሎ እንዲህ ተናገረ መባሉን ሰማን፡፡ "ለበደላችሁኝ ሁሉ ይቅር ብያችኋለሁ"፡፡ እንደዚህ ያለ "የበቃ" ሰው በ፳፩ኛው ክፍለ ዘመን ያላት አሮጊቷ ሣራ መሆኗም አይደል፡፡ ተበድሎ ይቅር ማለት እንዲህ ነው እንጂi  ታዲያ እንዲህ ያለውን በበር እንጂ ለምን በጓሮ ተሞከረ? ለመሆኑ ከበር በስተቀር ቤተ ክርስቲያን ሌላ መግቢያ አላት? ምነው በጓሮ ተሞከረችሳ! ….......................................................(/ አባይነህ ካሴ).......
 (በጽጌ ማርያም)
(አንድ አድርገን ታህሳስ 02 2006 ዓ.ም)፡- በቅርቡ የበጋሻው  ደሳለኝ እና የያሬድ አደመ ቀኖናዊ ያልሆነ ይቅርታ አድርጉልን ?”እግረ ጉዞ ለብዙዎች የመነጋገሪያ ጉዳይ ሆኗል፡፡የይቅርታ አድርጉልን ?”ሒደትም የመጀመሪያ እንጂ የመጨረሻ እንደማይሆንም በራሳቸውይቅርታ አድርጉልን ?”በሚሉት እና ከቤተ ክርስቲያን አውጥተውእምነ ጽዮንየስደተኞች ማኀበር በሚል በፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ መስመርነት በሐዋሳ ከአደራጆት ቡድናቸው ጋር መከፋፈላቸውም ገላጭ እሆነ ነው፡፡ይህ ቀኖናዊ አግባቦችን  አላሟላም የሚባለው ይቅርታ አድርጉልን ?”እግረ ጉዞ   ያስከተለው መለስተኛ ውዝግብ በልጆቹ ብቻ አልተወሰነም፡፡ደዌው ተዛምቶ እውነተኛ የቤተ ክርስቲያን ልጆችንም አምሶ ነበር፡፡አሁንም ቢሆን ( በመሠረቱ) የጉዳዬን ማዕከላዊ ጭብጥ እና መነሻ አድበስብሶ የሚያልፍ ከመሆን የታደገው ያገኘ አይመስልም፡፡