ዜና

    ከተለያዩ ድረ-ገጾች ስለ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርሰትያን የተጻፉ ጽሁፎች የሚወጣበት ገጽ ነው ፤ በተጨማሪም እንደ ደጀ ሰላም ያሉ ኢትዮጵያ ውስጥ የማይከፈቱ ገጾችን በቀላሉ በቀጥታ የሚያወጡትን ጽሁፎች ለማንበብ ይህን የዜና ገጽ ይጠቀሙ 





    • __________________________________________________________


    የተሀድሳውያን ጉባኤ በዱባይ
    ታላቅ የተሀድሳውያን ጉባኤ በዱባይ ሊደረግ ዝግጅቱ ተጠናቋል:: ታዲያ የዚህ ጉባኤ ተብዬ ዲስኩር ምን ያወሩ ይሆን? መቼም ዛሬም አባ ዮናስ የወለደው በምንፍቅና እየኮተኮተ ያሳደገው ልጁ በጋሻው አሮጊቷ ሳራ ወልዳናለች ካላቸው አጋሮቹ ጋር ማለትም ምርትነሽ ትዝታው እና ሌሎችም በአንድነት ምንፍቅናን ለማስፋፋት ከሀገር ቤት አልፎ በተለያዩ ሀገራት በመሔድ ምንፍቅናን ለማስፋፋት በመንቀሳቀስ ላይ ናቸው::

    አባቱን የማያከብር የሰማይ አባቱን አያከብርም ይህ ደግሞ በጋሻው በአደባባይ አባቶችን የእንጨት ላይ ሽበት ብሎ የሚሰድብ ሰባኪ ወይም ዲያቆን ቤተክርስትያን አልወለደችም::  አባ ዮናስ ግን ወልዷል ልጀቹን ደግሞ አሁን በጉባኤ ቤርያ ላይ ምንፍቅናን ሲደሰኩሩ ምንፍቅናን ሊዘምሩ ይሆን? የመዝሙር ዳንኪራ ሊያሳዩን ወንጌልን በምንፍቅና ለመበረዝ በመንቀሳቀስ ላይ ናቸው::

     ከነዚህ የበግ ለምድ ከለበሱ አውሬዎች ይሰውረን አሜን


    ከተዋሕዶ የቁርጥ ቀን ልጆች

    ይህ  መልዕክት ደርሶን ነበር

    በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አንድ አምላክ በሚሆን አሜን
    ውድ አንድ አድርገን፣
    እንደምን ሰንብታችኃል፣ እኛ የኢ/ኦ/ተ/ ልጆች በኢትዮጵያ እና በመላው ዓለም የምንገኝ ይህንን ደብዳቤ ስለ ወቅቱ የቤተ ክርስቲያናችን ጉዳዮችን አስመልክተን ለቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ልከናል እናንተም ይህንን ከዚህ መልዕክት በማድረስ እንድተባበሩን በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን፡
    አክባሪያችሁ የተዋሕዶ የቁርጥ ቀን ልጆች

    እኛም ይህው ለእናንተ ለአንባቢያን በዚህ መልክ አቅርበናል በpdf ያንብቡ To Read in Pdf

    _______________________________________________________________________


     3 ክርስትያኖችን በድንጋይ ገደሉ

    ደሴ አሬራ እየተባለ በሚታወቅ አካባቢ በሚገኘው የደብረ ሣህል ቅዱስ ዐማኑኤል ፀበል ተፀብለው ወደ መኖሪያ ቤታቸው እየተመለሱ በነበሩ ወጣቶች ላይ፣ ጳጉሜን 3 ቀን 2003 ዓ.ም ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ላይ በአካባቢው ያሉ አክራሪ ሙስሊሞች አስበው እና አልመው ሲጠብቋቸው በነበሩ ክስርትያኖች ላይ የድንጋይ ናዳ በማውረድ ጥቃት አድርሰውባቸው ወዲያው አንድ ሰው የገደሉ ሲሆን ፤ ሌሎች ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸው ደሴ ሪፈራል ሆስፒታል ከገቡት ብዙ ክርስትያኖች ውስጥ አንዲት ሴት እና አንድ ወንድ በህክምና ላይ እያሉ የደረሰባቸው ጉዳት ከፍተኛ በመሆኑ ህይወታቸው ሊያልፍ ችሏል፡፡በአሁኑ ሰዓት የተለያዩ አካላቸውን በጥቃቱ የተጎዱ ክርስትያኖች በሆስፒታሉ ይገኛሉ፡፡የመጀመሪያው ሟች ከፍተኛ ጉዳት ልቡ ላይ ደርሶበት ነው፡፡

    በአካባቢው የነበሩ የአይን ምስክሮች ጠይቀን እንደተረዳነው ጉዳቱ የደረሰባቸው በጠመጠሙ አክራሪ ሙስሊሞች መሆኑን የተረዳን ሲሆን ደጀሰላም ላይ የተዘገበው ግን ‹‹አንዳንድ ምንጮች ለጥቃቱ በሰኔ ወር የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የእገዳ ውሳኔ ያስተላለፈባቸው “መምህር ግርማ” የተባሉትን አጥማቂ ተከታዮች ››እንደሚጠረጠሩ ብለው የዘገቡት የተሳሳተ እና የተዛባ መረጃ ስለሆነ እንዲስተካከል ስንል እንጠይቃለን፡፡ ይህን መረጃ ቦታው ድረስ ሄደው ወይንም ጉዳቱ ደርሶባቸው በሆስፒታል ያሉትን ሰዎች አናግሮ እና አጣርቶ መዘገብ ያለበለዚያ ደግሞ ጉዳዩ እስኪጣራ እና ጉዳት ያደረሱት ሰዎች እስኪለዩ ድረስ በይሆናል የተሳሳተ መረጃ ለክርስትያኑ ማድረስ ተገቢ አለመሆኑን በዚህ አጋጣሚ ለመግለፅ እንወዳለን፡፡
    ________________________________________________________________________

    ሀሰት አንናገር እውነትን አንደብቅም
    ‹‹እግዚሐብሔር ቤተክርስትያንን ይጠብቅ››