Sunday, February 5, 2023

በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ሻሸመኔ እስራትና ውክቢያው ቀጥሏል። ሀገረ ስብከቱን በወራሪ ለመመዝበርና ሰብሮሮ ለመቆጣጠረር እየተሞከረ ነው።


+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ብርሃኑ ወልደ ዮሐንስ የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ለኢኦተቤ በስልክ እንደገለጹት ፣ ዛሬ ጥር 26 ቀን 2015 ዓ.ም ጠዋትወደ ምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት የጸጥታ አካላት በመምጣት የሀገረ ስብከቱን  ሠራተኞችን ከሥራ በማስወጣት ሀገረ ስብከቱን ግቢ  ከሠራተኞች ነጻ እንዳደረገው ገልጸዋል።
ፖሊስ በአርሲ ነገሌ አራት የደብር አስተዳዳሪዎችን ሕገ ወጡን ቡድን ተቀበሉ በማለት ሲያስገድድ ከቅዱስ ሲኖዶስ ጎን ነን በማለታቸው አራት አስተዳዳሪዎች ታስረዋል ብለዋል።
በመንበረ ጵጵስናው አብያተክርስቲያናት በታጠቁ ኃይሎች በፓትሮል በመዞር ምእመናኑን በማስፈራራት ላይ ናቸው ያሉት ዋና ሥራ አስኪያጁ 
ትናንት ምሽት በጸጥታ ኃይሎች የታፈኑት የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ዋና ፀሐፊ ሊቀ ልሳናት ቀሲስ ወንድወሰን ጥላሁንና የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው መምህር ሰሎሞን ዘገየ ከእስር ከተለቀቁ በኋላ ከበላይ ታዘን ነው በማለት በዛሬው ዕለት በድጋሚ  መታሠራቸውን እርሳቸውም ክትትል እየተደረገባቸው እንደሆነና የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ጽሕፈት ቤት ሠራተኞች በመንግሥት የጸጥታ አካላት ወደ ጽሕፈት ቤቱ እንዳይገቡ መከልከላቸውን አስታውቀዋል።
ሁነቱን ለዘረፋ ሊጠቀምበት ያሰፈሰፈ ኃይል አለ የዞኑ መንግሥት ከበላይ የመጣ ትዕዛዝ ነው በሚል በሃይማኖታችን ሊያስገድደን አይገባም ብለዋል። ትላንት አብረናቸው ሥንሰራ የነበሩ የፀጥታ አካላት እናዝናለን ግን ከበላይ ታዘን ነው በማለት ምንም ማድረግ እንደማይችሉ እየገለጹልን ነው ያሉት ሥራ አስኪያጁ በሕገ ወጥነትና በዘረፋ ምእመናንን ማገልገል እንዴት ይቻላል? ሲሉ ጠይቀዋል። እኔም የአካባቢው ተወላጅና በኦሮምኛ ቋንቋ አገልግሎት የምሰጥ ነኝ ጉዳዩ ቤተክርስቲያንን ለሌላ ሃይማኖት መጠቀሚያ ለማድረግ የተሴረ ሴራ ነው ብለዋል። ሁሉም ወረዳዎች ሕገወጡን ሢመት አውግዘው በቅዱስ ሲኖዶሱ ሥር መሆናቸውን ገልጸዋል።
በሻሸመኔ በሕገ ወጡ ሲኖዶስ የተሾመው ግለሰብ የወንጌላውያን አማኝ የሆነችው ዘጸአት አፖስትሊክ ቸርች የኪራይ ስምምነት አለኝ ስትል መግለጫ ያወጣችበት ግለሰብ መሆኑ ይታወሳል።
ሥራ አስኪያጁ የሰጡትን መግለጫ ከቆይታ በኋላ በዩቲዩብ ገጻችን ማግኘት ይቻላል።
EOTC TV
++

No comments:

Post a Comment