Wednesday, March 22, 2017

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፡ በእንጦጦ ተራራ ላይ ግዙፍ ሆስፒታል ልትገነባ ነው

·         ሆስፒታሉ፣ የሜዲካል እና የነርሲንግ ዩኒቨርስቲን ያካትታል፣
·         ታሪክን ያንጸባርቃል፤ ሥነ ምኅዳርን የሚጠብቅ ቴክኖሎጂ ይጠቀማል፣
·         ለሀገሪቱ የሕክምና ቱሪዝም ፍሰት አስተዋፅኦ ያደርጋል፣
 ሰንደቅ፤ መጋቢት 13 ቀን 2009 .
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን፣ ተዋሕዶ ዲፕሎማቲክ ሜዲካል ሲቲ የተሰኘ ኹለገብ የሕክምና ማዕከል 400 ሚሊዮን ዶላር ወጪ እንደሚገነባ ያስታወቀ ሲኾን፤ የፕሮጀክት ስምምነቱንም፣ ጀንደሪ ሜጋኮርፕ ከተሰኘ ዓለም አቀፍ ድርጅት ጋራ መፈራረሙን ገለጸ። 

Thursday, March 16, 2017

ቅዱስ ሲኖዶስ በቆሼ አካባቢ ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖች 7 ቀን የሚቆይ ጸሎተ-ፍትሐት እንደሚደረግ ገለጸ


·        ሼክ መሃመድ አሊ አላሙዲን እና ቤተሰቦቻቸው 40 ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርገዋል፡፡

(አንድ አድርገን መጋቢት 7/2009 . ) :- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ  ቆሼ በተሰኘው አካባቢ መጋቢት 2 ቀን 2009 . ምሽት 130 በደረሰ አደጋ ህይወታቸውን ላጡ ወገኖች ከመጋት 7/2009 .  ጀምሮ ለሰባት ቀናት የሚቆይ ጸሎተ-ፍትሐት በመላው ገዳማት እና አድባራት እንደሚደረግ ገለጸ፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ በአደጋው ለተጎዱና መጠለያ ላጡ ወገኖች የሚውል 200 ሺህ ብር እርዳታ እንዲሰጥ መወሰኗንም አስታውቋል፡፡የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳይ ጠቅላይ ምክር ቤትና የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት እያንዳንዳቸው ለተጎጂዎች የሚውል 100 ሺህ ብር ድጋፍ አድርገዋል፡፡ የሚድሮክ ኢትዮጵያ እህት ኩባንያዎች እና የሚድሮክ ኢትዮጵያ ሊቀ መንበር ሼክ መሃመድ አሊ አላሙዲን እና ቤተሰቦቻቸው  ለተጎዱ ወገኖች የሚውል 40 ሚሊየን ብር ድጋፍ ሲያደርጉ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በበኩሉኩ የ5 ሚሊየን ብር ድጋፍ ማድረጉን አስታውቋል::

የይሓ ቤተ መቅደስ ጥገና ተደርጎለት ለጎብኚዎች ክፍት ሆነ

ከክርስቶስ ልደት በፊት 800  ዓመተ አለም  እንደተገነባ የሚነገርለት ጥንታዊው የይሓ ቤተ መቅደስ ጥገና ተደርጎለት ዛሬ ለጎብኚዎች  ክፍት ሆነ። ቤተ መቅደሱን መጠገን ያስፈለገው በዕድሜ ብዛት የመሰንጠቅና ሌላም ጉዳት ስለደረሰበት መሆኑን በአክሱም ከተማ ባህልና ቱሪዝም ጽህፈት ቤት የአርኪዮሎጂ ባለሙያ የሆኑት አቶ አላይ  ገብረስላሴ ገልጸዋል።
በትግራይ ክልል ከአደዋ ከተማ 32ኪሎ ሜትር  ርቀት ላይ የሚገኘው  የይሓ ቤተ መቅደስ ጥገናው የተደረገለት ባለፉት   ስምንት ዓመታት በጀርመናዊያን  ባለሙያዎች እንደሆነም አመልክተዋል፡፡ባለሙያው እንዳሉት ቤተ መቅደሱ ጥንታዊ ይዘቱ  ሳይለቅ የተሰነጠቁ  ድንጋዮችን መሙላት፣  የበሰበሱ ድንጋዮችን ደግሞ በሌላ የመተካት ስራው በጥንቃቄ ተከናውኗል፡፡
የቤተ መቅደሱን  የጥገና  ስራ መጠናቀቁን ይፋ በማድረግ  መርቀው ለጎብኚዎች ክፍት ያደረጉት የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር  አቶ ዮናስ ደስታ እና  የትግራይ ክልል  ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ አቶ ዳዊት ሃይሌ ናቸው፡፡
 ምንጭ ፡- http://www.ena.gov.et
--------------------------------------------------------------------------------------------------------------------

ይሓ የጥንታዊ ሥልጣኔ አሻራ 

(ከምሕረተሥላሴ መኰንን)
 ከአክሱም ከተማ በስተሰሜን ምሥራቅ አቅጣጫ 56 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ጥንታዊቷ ይሓ ከተማ ትገኛለች፡፡ የይሓ ከተማ መግቢያ ላይ ከተማዋ የምትታወቅባቸው ሁለት ታላላቅ ሕንጻዎች ይገኛሉ፡፡ አንደኛው ግራት በዓል ግብሪ በሚባለው ቦታ የነበረው ቤተ መንግሥት ነው፡፡ ይህ ሥፍራ አሁን የአርኪዮሎጂ ስፍራ (ሳይት) ሲሆን፣ በተመራማሪዎች ተከልሎ ይታያል፡፡ የጀርመን አርኪዮሎጂካል ኢንስቲትዩት ባለሙያዎች በሚያደርጉት ቁፋሮ ከክርስቶስ ልደት በፊት ወደ 8ኛውና 9ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የሚጠጉ ግኝቶች ይፋ መሆናቸውን ለማወቅ ችለናል፡፡ አንዳንድ ጥናቶች በአካባቢው ቁፋሮ ከተጀመረ ዓመታት ቢቆጠሩም በደርግ ወቅት ተቋርጦ 1985 .. ዳግም መጀመሩን ያሳያሉ፡፡ ኢትዮጵያን ኢንስቲትዩት ኦፍ አርኪዮሎጂና የፈረንሳይ የአርኪዮሎጂ ቡድንን ጨምሮ የብዙ ተመራማሪዎች መዳረሻ ነው፡፡