Saturday, March 30, 2013

ታሪክን የኋሊት “ዴር ሡልጣን በእጃችን እስካልተመለሰ ድረስ ኢየሩሳሌምን አልሳለምም” አቡነ ሺኖዳ


(አንድ አድርገን መጋቢት 23 2005 ዓ.ም)፡- ትላንት ለዛሬ ታሪክ ነው ፤ ዛሬ የተጻፈውም እውነት ለነገው ትውልድ ታሪክ ሆኖ ይቀመጥለታል ፤ የዛሬ ታሪክን የኋሊት ፅሁፋችን  ከአስራ አራት ዓመት በፊት በወርሐ ሐምሌ 1991 ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ገብርኤል በኢየሩሳሌም በነበሩበት ወቅት  ከ‹‹ጦቢያ መጽሔት›› ጋር ያደረጉት ቃለ መጠይቅ ይሆናል ፡፡
  •   አቡነ ሺኖዳ ‹‹ዴር ሡልጣን በእጃችን እስካልተመለሰና የፍልስጤም መንግሥት ተመስርቶ እየሩሳሌምን እስካልገዛ ድረስ  ኢየሩሳሌምን አልሳለምም›› ብለው በይፋ በጋዜጣ ላይ ጽፈዋል፡፡
  •   ግብጽ በመንግሥት ደረጃ ጉዳዩን ይዛ ሽንጧን ገትራ በዲፕሎማሲያዊ መስመር ከፍተኛ ትግል ስታካሂድ ኢትዮጵያ ግን በመንግሥት ደረጃ በጉዳዩ ላይ ጣልቃ ገብታ ባለመከራከሯ በእጃችን ገብቶ የነበረውን ፍትህ እንድናጣ ሆኗል፡፡
  •  የግብፅ መንግሥትና የግብፅ ቤተ ክርስቲያን በዴር ሡልጣን ጉዳይ እንቅልፍ የላቸውም፡፡ ግብጾች በጉዳዩ ክርክር ያደርጉ የነበረው ‹‹የአገር መሬት ነው የተወሰደው ፤ ሁኔታው የክብር ጉዳይ ነው›› ብለው ነበር፡፡
  •   ዴር ሡልጣን የኢትዮጵያ ሕዝብ ርስት ነው፡፡ ይህንን በአገር ውስጥም በውጭ ያሉትም ኢትዮጵያውያን ማወቅ ይገባቸዋል፡፡
  •  የእስራኤል መንግሥትም እንደ ግብፅ መንግሥት ሁሉ በጉዳዩ ላይ ክርክር ሆነ ውይይት እንዲደረግበት የሚፈልገው በመንግሥት ደረጃ እንጂ በቤተ ክርስቲያን ብቻ ተወስኖ እንዲቀር አይደለም፡፡
  •   የጎሳ በሽታው ከዚሁ ከአገር ቤት እንደ ተስቦ ወደ ኢሩሳሌም የተዛመተ ነው ማለት ይቻላል፡

Friday, March 29, 2013

ቅርሶቹ የት አሉ ?




  • ቅርሶቹን እና የደረሰብኝን ጉዳት በተመለከተም ማስረጃዎች በእጄ የሚገኙ በመሆኑ እያዘጋጀሁት ባለሁት መጽሐፍ ላይ ይፋ አደርገዋለሁ፡፡”  ቀሲስ ምትኩ

(አንድ አድርገን መጋቢት 20 2005 ዓ.ም)፡- መርጡ ለማርያም ገዳም የሚገኙት ቅርሶች ከዚህ በፊትም በገዳሙ ሰበካ ጉባኤ እና በሕዝቡ ዘንድ መነጋገሪያ አርዕስ እንደነበር ይታወቃል ፡፡ አንዳንድ የአካባቢው ነዋሪዎች መኖራቸውን ሲጠራጠሩ የገዳሙ ሰበካ ጉባኤ ደግሞ መኖራቸውን ምንም ሳይሆኑ መቀመጣቸውን ሲናገር ነበር፡፡ አሁን ግን አንድ አባት ቦታውን እና የቅርሶቹን ሁኔታ በአግባቡ አውቃለሁ አብዛኞቹ ቅርሶች ሸሽተዋል ወይም ጠፍተዋል በማለት ማስረጃ እንዳላቸውና ጥያቄውን ለሚመለከታቸው አካላት ቢቀርብም መልስ ስላልተሰጣቸው ያለመኖራቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ እጄ ላይ ስለሚገኝ በመጽሐፍ መልክ በማሳተም ለሕዝብ ይፋ አደርጋለሁ ብለዋል፡፡ ከሳምንት በፊት እኝህን አባት ቆንጆ መጽሔት አነጋግሯቸው ነበር፡፡

Wednesday, March 27, 2013

የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት የመብት ጥያቄ በተሃድሶ መናፍቃን አጀንዳ ተጠለፈ

  • የደቀመዛሙርቱ አካዳሚክ፣ አስተዳደራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ ወደ ግለሰቦች ኃላፊነት ማስነሳት በሚል ቅድመ ሁኔታ ተቀይሯል፡፡
  • “ተቃውሞውን አስተባብረሃል” በሚል ታስሮ የነበረው ደቀመዝሙር ከእስር ትናንት ተፈትቷል፡፡
  • የተሃድሶ ኑፋቄ አራማጅ የሆኑ ተማሪዎች ተቃውሞውን ኦርቶዶክሳውያንን ከኮሌጆ ቁልፍ ቦታ በማስወገድ በመናፍቃን ለመተካት በኅቡዕ እየተንቀሳቀሱ ነው፡፡

(አንድ አድርገን መጋቢት 19 2005 ዓ.ም)፡- የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት በኮሌጁ ስላለው የአስተዳደር ጉድለት ፣ የትምህርት ጥራት ማነስና የምግብ አቅርቦት ጥራት መጓደል ተቃውሟቸውን በትምህርት ማቆምና የረሃብ አድማ በማድረግ እየገለጹ ነው፡፡ በርካታ መገፋት ቤተክህነቱ  እያደረሰባቸው የሚገኙት የነገረ መለኮት ምሩቃንና ደቀ መዛሙርት ያቀረቡት ተቃውሞ የቤተክህነቱን አስተዳደረዊና መንፈሳዊ ድቀት ርቀት እንደ ማሳያ ተደርጎ ተወስዶአል፡፡

ደቀ መዛሙርቱ በኮሌጅ ቆይታቸው ጥራቱ የተጓደለ ምግብ ፣ ፍታሃዊ ያልሆነ የውጤት ምዘና ሥርዓት ፣ የአስተማሪዎች ንቀትና ስድብ ፣ በተሃድሶ መናፍቃን ቡድን ቅሰጣና በአስተማሪዎች የአቅም ማነስ ይማረራሉ፡፡ ከኮሌጅ ተመርቀው ሲወጡ የሚከፈላቸው ደመወዝ ለዕለት ኑሮ አለመብቃትና በጥቂት መናፍቃን ምክንያት በምእመናን ዘንድ ለደቀ መዛሙርቱ ያለው አመለካከት የተዛባ መሆኑ ቤተክርስቲያን ከምሩቃኑ ልታገኝ የሚገባትን አገልግሎት እንዳታገኝ እያደረጋት ነው፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ያቀረቡት የመብትና የአስተዳደራዊ ለውጥ ጥያቄ ሁሉንም የኮሌጁ ደቀ መዛሙርት ባሳተፈ መልኩ እያቀረቡ ሲሆን ተቃውሞውን ከሚመሩት የደቀ መዛሙርት ተወካዮች (ካውንስል  አመራር አባላት መካከል የተሃድሶ ኑፋቄ አራማጆች መሆናቸው ማስረጃ የቀረበባቸው) አጋጣሚውን ተጠቅመው የኮሌጁን አስተዳደር ቁልፍ መዋቅር ኦርቶዶክሳውያንን በማስነሳት አዝማቾቻቸው በሆኑት ሁለት መምህራን ለመተካት እንቅስቃሴ ላይ መሆናቸው ተመልክቶአል፡፡

Tuesday, March 26, 2013

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ስራቸውን ጀምረዋል

  • “እስከ አሁን ለሰራችሁት ስራ ቤተክርስቲን ታመሰግናለች ፤ ቤተክርስቲያን አገልጋይ ትፈልጋለች ፤ ወደፊትም በዚሁ ቀጥሉ” ማኅበረ ቅዱሳን ራት ግብዣ ካደረገላቸው በኋላ የተናገሩት 
  •   የአንድ ቡድንን የእራት ግብዣ ፓትርያርኩ አልተቀበሉትም፡፡
  •  “ይህን ጉዳይ አላውቀውም ይቆይ” ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ እነዲፈርሙ ለቀረበላቸው ሰነድ የሰጡት መልስ

(አንድ አድርገን መጋቢት 18 2005 ዓ.ም)፡- ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ከተመረጡ በኋላ  ለመጀመሪያ ጊዜ ከዚህ በፊት ባሉ አባቶች ያልተለመደ ቃለ መጠይቅ ከአሜሪካ ድምጽ የአማርኛው ፕሮግራም ጋር አድርገው ነበር ፡፡ ፓትርያርኩን ጋዜጠኛ አዲሱ አበበ ለጠየቃቸው በርካታ ጥያቄዎች ከአንድ አባት የሚጠበቅ ጥሩ መልስ መስጠታቸውን ብዙዎች የሚስማሙበት ነጥብ ሆኗል ፡፡ በርካቶች እንደ ‹‹አንደበታቸው ያድርግላቸው ሃሳባቸው እግዚአብሔር ያሳካላቸው›› በማለት መልካም ምኞታቸውን ሲገልጹ ፤ ጥቂቶች ደግሞ ‹‹ትልቁ ነገር ቃለ መጠይቅ ለማድረግ ፍቃደኛ መሆናቸው ፤ ከማንኛውም ፍትሀትና ስጋት ያለመሸበባቸው ነው›› በማለት አስተያየታቸውን የሰጡም አልጠፉም ፤ አንድ አንዶች “እጅግ የመርህ ሰው መሆናቸውን ያመላከተ ቃለ መጠይቅ ነበር” ብለዋል ፡፡ በተጨማሪም በባለፈው አስተዳደር የቤተክርስቲያኒቱ አስተዳደራዊ መዋቅሮች በጎጥና በቋንቋ የሚግባቡ ሰዎች የተወረረ ቢሆንም ጥበባዊ እና መንፈሳዊ በሆነ አካሄድ ተጠቅመው ቤተክርስቲያኒቱ የሁሉ መሆኗን የሚያሳይ ከጎጥ ፤ ከብሄር ፤ ከቋንቋ እና መሰል ቤተክርስቲያኒቱን የማይወክሏትን ነጥቦች ወደ ኋላ በማድረግ ዘመናዊ ስልጡን አስተዳደር ይዘረጋሉ ብለው የሚያምኑ  ሰዎች አልጠፉም፡፡

ወቅታዊ ምላሽ “ለኤልያሳውያን” መርሃ ግብር





(አንድ አድርገን መጋቢት 17 2005 ዓ.ም)፡- አዲሱን የኤልያሳውያን አስተምህሮ በማስመልከት  መጋቢት 25 አውቶቡስ ተራ አካባቢ የሚገኝው በተለምዶ አዲሱ ሚካኤል ቤተክርስቲያን በመምህር ምህረት አብ አማካኝነት ምዕመኑን የማንቃት እና ከዚህ አይነት አስተምህሮ ራሱን እንዲጠብቅ የሚያስችል ትምህርት ለመስጠት ታቅዷል ፤ በተጨማሪም ነብዩ ኤልያስን የሚመለከት የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ምን እንደሆነ በአባቶች ይቀርባል ፡፡ እርስዎም በመርሀ ግብሩ ላይ እንዲገኙ ተጋብዘዋል፡፡

ከዚህ በታች የምታት ፎቶ ኤልያሳውያን አራት ኪሎ በሚገኝው መሰብሰቢያ አዳራሻቸው አርቲስት ጀማነሽ ፕሮግራም ስትመራ ነው…. የሚለብሱት ልብስ ፤ ከጀርባ ያለውን መስቀል ፤ የእምነታቸውን መጠሪያ ያስተውሉት፡፡

Sunday, March 24, 2013

የፓትርያርኩ አስመራጭ ከምርጫ በፊትና ከምርጫ በኋላ… … . ምን ይላሉ ?

  • ነፃ መሆናችንን የሚያረጋግጠው እግዚአብሔርና ሕሊናችን ነው፡፡ በሙሉ ህሊናዬ በመተማመን የምናገረው አንዳች የሚፀፅተኝ ነገር አለማድረጌ ነው፡
  • ማኅበረ ቅዱሳን አቡነ ጳውሎስ ሹመት ከቀኖና ውጪ ነው በማለት ተቃውሞ አያውቅም፡
  • ማኅበረ ቅዱሳን ለምርጫው አመራር ላክ ተብሎ ቢነገረው እንኳ እኔን ይልከኝ እንደነበር በእርግጠኘነት መናገር እችላለሁ፡
  • መንግሥት ጣልቃ አልገባም ፤ “የማይተማመኑ ባልንጀሮች በየወንዙ ይማማላሉ” ይባላል፡፡ ከአሁን በኋላ ይህን ጥያቄ እንድትጠይቀኝ አልፈልግም፡፡(ከምርጫ በፊት
  • ጫናዎች አልነበሩም ማለት አልችልም…(ከምርጫ በኋላ
  • ሕጉ ተጣሰ ከተባለም ሕጉን የጣሰው አስመራጭ ኮሚቴው ሳይሆን መርሀ ግብሩ እንዲጸድቅ ያደረገው ሲኖዶሱ ነው፡
  • እኛ አቡነ ማትያስ ኢትዮጰያዊ ዜጋ መሆናቸውን ደብዳቤም በለው ምንም እስከተመለከትን ድረስ አምነንበታል፡፡
(አንድ አድርን መጋቢት 16 2005 ዓ.ም)፡- ከሳምንታት በፊት ስድስተኛ ፓትርያርክ አድርጎ አቡነ ማትያስን በመምረጥ የተጠናቀቀው የምርጫ ሂደት ውስጥ ሲኖዶሱ ምርጫውን እንዲያከናውኑ አስመራጭ ኮሚቴ አድርጎ ከሾማቸው ሰዎች ውስጥ ባያብል ሙላቴ አንዱ ነው፡፡ ባያብል ከአስመራ ዩኒቨርሲቲ በአካውንቲንግ የመጀመሪያ ድግሪ እና በማኔጅመንት ኢንፎርሜሽን ሲስተም ሌላ ድግሪ እንዳለው የትምህርት ፕሮፋይሉ ይናገራል፡፡ በአሁኑ ሰዓት በኮንስትራክሽን ባንክ የመምሪያ ኃላፊ እና በማኅበረ ቅዱሳን ስራ አመራር ደረጃ እየሰራ ይገኛል፡፡

Thursday, March 21, 2013

አራት ኪሎ የመሸገው የኤልያሳውያን ቡድን አስተምህሮ



·   “ኦርቶዶክስ ተዋህዶ” ብሎ ከመሰየም ይልቅ “ካቶሊክ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን” ብሎ መሰየም አስር እጥፍ የተሻለ ነው፡፡
·   የ “ተዋህዶ” ልጆች ሁሉ ልብሳችንን ጸአዳ ፤ የልብሳችንን ዘርፍ  ፤ የአንገታችንን ማህተብ የቀስተ ደመና ማህተብ ሊሆኑ ይገባል፡፡
·    አንዲቱ ዕለት ሰንበት ቅዳሜ መሆኗን ፤ እሁድ ግን ዕለተ ሰንበት አለመሆንዋን ምስጢር አዋቂው ቀናኢ ነብይ ኤልያስ ለአባቶቻችን አረጋግጦ ነግሯቸዋል፡፡
·  ኤልያሳውያን ማኅበረ ቅዱሳንን እንዲህ ነው ይላሉ “የኢትዮጵያ ቅዱሳን ያዘኑበት የአመጸኞች ስብስብ ፤ ምን ያህል ያጌጠ ሽፋን እንደተከናነበ በውስጡ ግን ምን እንደሚካሄድ ግልጽ ነው ፤ ይህ ካለ እኔ ለቤተክርስቲያን ማንም የለም እያለ ከመናፍቃን ፤ ከጳጳሳት ጋር ሽር ጉድ የሚል……”

(አንድ አድርገን መጋቢት 13 2005 ዓ.ም)፡- የዚህ የአራት ኪሎው ቡድን አካሄድ ከአመት በፊት ብናውቅም በጊዜው ስለ እነርሱ ያሉንን መረጃዎች ብናወጣ ለእነሱ ማታወቂያ መስራት ይሆናል ብለን በማሰብ እስከ አሁን አዘግይተነዋል፡፡ አሁን ግን በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት ለማግኝት ያስችላቸው ዘንድ በኢግዚቢሽን አዳራሽ መርሀ ግብር ለማዘጋጀት እየሰሩ ስለሆነ ስለ ቡድኑ ያለንን መረጃ ደረጃ በደረጃ ለማውጠት ግድ ሆኖብናል፡፡

አራት ኪሎ የመሸገው የኤልያሳውያን ቡድን ምን አይነት ፍልስፍና እና አስተምህሮ እንደሚከተል ሰዎች እንዲያውቁት ለማድረግ ያስችል ዘንድ “በዘመናችን ከብሔረ ህያዋን የወረደ ቅዱስ ኤልያስ የገለጠው ስውር ረቂቅ ምስጢራት” በሚል አርዕስት የተጻፈ እና ለአባሎቻቸው በሀርድ ኮፒ እና በሶፍት ኮፒ የተሰራጨውን ባለ ዘጠኝ ገጽ ወረቀት አለፍ አለፍ ብለን መሰረታዊውን የቡድኑን አስተምህሮ እና አካሄድ ከጽሁፉ ላይ ቀጥታ በመውሰድ ጥቂት ለመዳሰስ እንሞክራለን፡፡ (በፒዲኤፍ ለማንበብ ) 

Wednesday, March 20, 2013

የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች ኮሌጁን በመቃወም ለፓትርያርኩ ደብዳቤ ጻፉ



-    አሥር ችግር ናቸው ያሏቸውን ጥያቄዎች አቅርበዋል
   (Reporter March 20 ):- አራት ኪሎ የሚገኘው የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች ኮሌጁ እያደረሰባቸው ያለውን ችግር በመዘርዘርና በመቃወም፣ 15 ቀናት በፊት በዓለ ሲመታቸውን ለፈጸሙት ስድስተኛው ፓትርያርክ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ደብዳቤ ጻፉ፡፡
ደብዳቤያቸውን ለቋሚ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት፣ ለጠቅላይ ቤተ ክህነት፣ ለኮሌጁ፣ ለሰብዓዊ መብት ኮሚሽን፣ ለፌዴራል ፖሊስ፣ ለአዲስ አበባ ወጣቶች ቢሮና ለአራዳ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ግልባጭ ያደረጉት ተማሪዎቹ፣ በኮሌጁ ውስጥ ከዕለት ወደ ዕለት እየተባባሰ መጥቷል ያሉትን አስተዳደራዊና የመማር ማስተማር ሒደት ችግሮች አስታውቀዋል፡፡

Tuesday, March 19, 2013

መናፍቃን “ሁዳዴ ጾምን ከኦርቶዶክስ ጋር አብረን እንፁም” እያሉ ነው


  • ይህን አቋም በኢቢኤስ የቴሌቪዥን ፕሮግራም ለ8 ወራት ያህል አውርደናል አውጥተናል፡፡
  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ታሪካዊ ቤተክርስቲያን ነች ረዥም ዓመት በወንጌል አገልግሎት በወንጌል የቆየች ቤተክርስቲያን ነች፡፡ ከዚች ቤተክርስቲያን ጋር ቀን ወስኖ መጾም በረከቶችን ያመጣል ፤ በአንድነት በኅብረት ሲጸለይ ሲጾም እግዚአብሔር ዘንበል ይላል፡፡
  • ይህንን ስንል የቤተክርስቲያኗ የተለመደ ስርዓት አለ ፤ ቤተክርስቲያኗ የኛ ናት ፤ አካላችን ናት በማለት ማክበራችንንና ማስተዋላችንን ለማሳየት ነው፡፡
  • እኛ የራሳችን የሆነ ማንነታችንን የሚያሳይ  ጤነኛ የባህል እጦት አለብን፡፡



(አንድ አድርገን መጋቢት 11 2005 ዓ.ም)፡- ቀድሞ ከአስርና ከሃያ ዓመታት በፊት ቤተ ክርስቲያኒቱን በቅርቡ የማያውቋት ወገኖች ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ፍጹም ከወንጌል ያፈነገጠች ፤ ባህላዊ ነገር የሚበዛባት ፤ ከወንጌል ጋር ግንኙነት የሌላት አድርገው ይሰብኩ ነበር ፡፡ ይህ አካሄድ እንደማያዘልቃቸው የተረዱት ወገኖች ቀስ በቀስ በመንሸራተት ቤተክርስቲያን ያስቀመጠችውን ስርዓት በመውሰድ ሲጠቀሙ እየተስተዋሉ ይገኛሉ ፡፡ ማንም ባይጠይቃቸውም ከበሮውን ፤ ጽናጽሉን ፤ መቋሚያውን ፤ እና መሰል መገልገያዎችን ወደ አዳራሾቻቸው ካስኮበለሉ ቆይተዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ቤተ ክርስቲያኒቱ ለአገልጋዮቿ የምትሰጠውን የማዕረግ ስም መጠቀም ከጀመሩም ሰንበትበት ብለዋል፡፡ መጋቢ ሐዲስ ፤ መጋቢ ብሉይ እና መሰል ማዕረጋት በቤታቸው ይገኛሉ ፡፡ ቤተክርስቲያን ለመዘምራን ፤ ከቀሳውስት ፤ ለዲያቆናት እና ለመነኮሳት ለይታ ያስቀመጠቻቸውን አልባሳትን ከንዋየ ቅዱሳት መደብሮቻችን መግዛት ጀምረዋል ፡፡ የቅዱስ ያሬድን ዜማ ቤተ ክርስቲያን ባስተማረቻቸው ሰዎች አማካኝነት አባሎቻቸውን በማስተማር ፍጹም አይን ያወጣ ዝርፊያ በማድረግ እንደ ተሐድሶያውያን መዝሙር መሳይ ዘፈኖቻቸውን መስራት ጀምረዋል ፤ ምንም የግጥምም ሆነ የዜማ ለውጥ ያልተደረገባቸው መዝሙሮቻችን የአዳራሾቻቸው ማሞቂያዎች ከሆኑ ቆይተዋል ፤ ለመጀመሪያ ጊዜ በበገና የታጀበ መዝሙር ለገበያ አቅርበዋል ፤ ስብከቶቻቸው ላይም ስለማያውቁት ቅዱስ ያሬድ በማንሳት ሰማያዊ ጸጋን ከአምላክ መቀበሉን እየሰበኩ ይገኛሉ ፤   .. ታዲያ እኝህ ሰዎች ምን ቀራቸው ?

Saturday, March 16, 2013

“ነብዩ ኤልያስ በአራት ኪሎ” አዲስ ሃይማኖት ?



  • ኤልያስ ብቻውን አይመጣም ፤ አብሮት ሄኖክም ይመጣል ::
  • “የኢትዮጵያ ትንሳኤ ሊያረጋግጥ ኃያል ባለስልጣን ቅዱስ ኤልያስ ከብሔረ ሕያዋን መጥቷል”  አርቲስት ጀማነሽ ሰለሞን ለሚዲያዎች የበተነችው መልዕክት
  • ሐሳዊ መሲሕ የሚነግሠው ፤ ኄኖክና ኤልያስም የሚገለጡት ‹በተቀደሰችው ከተማ” በኢየሩሳሌም ነው፡፡ በኢየሩሳሌምም ሐሳዊ መሲህ ገና አልነገሰም፡፡
  • በ2012 የተደረሰ አንድ ጥናት ባለፉት 3 ዓመታት በአሜሪካ ውስጥ 132 ሰዎች መሲሕ ነን ብለው ተነስተው ወደ 4.5 ሚሊየን የሚደርስ ሕዝብ አስከትለዋል፡፡


(አንድ አድርን መጋቢት 7 2005 ዓ.ም)፡- አንድ አድርገን  ኤልያሳውያን የዛሬ አመት በመሀል አዲስ አበባ አራት ኪሎ ላይ ሲያቆጠቁጡ በነበረበት ጊዜ ከተማ ውስጥ ሰዎችን ለመሳብ የበተኑትን ወረቀት ብሎጋችን ላይ በመለጠፍ በጊዜው ሰዎች ከእዚህ አይነት እንቅስቃሴ ራሳቸውን እንዲጠብቁ መልዕክት አስተላልፋ ነበር፡፡ ማኅበረ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ የጽዋ ማኅበር ስብስባቸውን የጀመሩት ጥቂት ሰዎች ዛሬ ቁጥራቸው እየጨመረ ይገኛል ፡፡ በቅርቡ እጅጉን ብዙ ሰው ለመሳብ ይረዳቸው ዘንድ በአዲስ አበባ ኢግዚቢሽን ማዕከል ትልቅ የሚባል ፕሮግራም እንዳዘጋጁና የኢትዮጵያንም ትንሳኤ እንደሚያበስሩ እየገለጹ ይገኛሉ፡፡ ተሀድሶያውያን ከውስጥም ከውጭም ያሉ ሰዎች ላይ መረባቸውን ጥለው አንዴ በአውደ ምህረት ፤ አንዴ በአዳራሽ ፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ በስታዲየም እየጠሩ ሰዉን ውዥንብር ውስጥና ጥርጣሬ ውስጥ መክተታቸው ይታወሳል፡፡ የአሁኖቹ “ተዋሕዶ” ነን ባዮች ኤልያሳውያን ደግሞ ከእዚህ ለየት ያለ አካሄድ አላቸው ፡፡ ኤልያሳውንን በቅርብ ሆነን እንደተመለከትነው ስለ ትምህርተ ሃይማኖቱ ጠለቅ ያለ እውቀት አለው ብለው የሚያስቡት ሰዎች ላይ ፤ ሚስጥራትን የሚያውቁ ፤ የመንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች እና ረዥም ጊዜ በአገልግሎት የቆዩት ሰዎችና ታዋቂ አርቲስቶች አባሎቻቸው ሆነው ተመልክተናል፡፡ ሳምንት በፊት ይህን በሚመለከት ያቀረብነው ጽሁፍ ከሀገር ውስጥም ይሁን ከሀገር ውጪ ያሉ ሰዎች እንቅስቃሴው አዲስ ነገር እንደሆነባቸውና እጅጉንም መገረማቸውን ገልጸውልናል ፡፡ምእመኑን እንደ ተሀድሶያውያን ለማስኮብለል እና ሌላ ውዥንብር ፤ ሌላ መከፋፈል ፤ ሌላ የህብረት ማጣት ውስጥ ለመክተት የተዘጋጁ ቡድኖች ከአዲስ አበባ አልፈው ወደ ክልል ከተሞች ፤ ከኢትዮጵያ አልፈው በአውሮፓ እና በአሜሪካ ሊንቀሳቀሱ ስለሚችሉ ምእመኑ መረጃውን አውቆ ራሱን ፤ ቤተሰቡንና ቤተክርስቲያንን ከእንዲህ አይነት እንቅስቃሴ አስቀድሞ በመንቃት ይጠብቅ ዘንድ መልዕክታችን ነው፡፡
የአርቲስት ጀማነሽ ሰለሞንን የሚሼሪያን ቆይታ ካወጣን በኋላ ይህን እንቅስቃሴ በሚመለከት አዲስ ጉዳይ መጽሔት ዲያቆን ዳንኤል ክብረትን ምላሽ እንዲሰጥበት በመጠየቅ አንድ ጽሁፍን ይዛ  ወጥታለች፡፡  ዲ/ን ዳንኤል የተነሱ ጥያቄዎች ተንተርሶ  ጥቂት ጉዳዮችን ይዳስሳል፡፡ “ነብዩ ኤልያስ ወደ ኢትዮጵያ መጥቷል የሚለው” ጉዳይን በመፈተሸ ሃይማኖታዊ ትንታኔ ሰጥቶበታል፡፡“ተዋህዶ” ነን ባዮች አስተምህሮዋቸውን በሚመለከት አዲስ ጉዳይ ላይ የወጣውን እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡

Friday, March 15, 2013

13 አክራሪዎች ከ27 መሳሪያ ጋር ተያዙ




(አንድ አድርገን መጋቢት 6 2005 ዓ.ም)፡-በተለያዩ ሃይማኖቶች ውስጥ ወይም በአንድ ሃይማኖት ውስጥ የሚገኙትን የተለያዩ  የእምነት ቡድኖች እንዲህ ናቸው ብሎ ለመሰየም የሚያስችል ገላጭና ተስማሚ ቃል ወይም ስያሜ መምረጥ ሁልጊዜም ቢሆን አስቸጋሪ ሥራ ነው፡፡ ቃሎቹ ገላጭ ናቸው ሲባል አልፎ አልፎ አንድ ላይ ፈራጅ ሆነውም ይገኛሉ፡፡ ሁሉንም በአንድ አጠቃሎ መጥራት አደገኛ ነው ፤ የግበጹ ሼክ ሻኪር አል ሰይድ ከወደ አሜሪካ ባወጀው ጅሀድ ውስጥ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉት ሙስሞች እንዲነሱ  የተጠቀመበት ቃል አለ፡፡ “ ቤትህ ውስጥም ብትሆን ፤ከልጅህ ጋር ብትጫወት ፤ ቴሌቪዥን እያየህ ቢሆን ሙስሊም በመሆንህ ብቻ አሸባሪ ነህ ይሉሀል” ብሏል፡፡ መንግስት ሙስሊም የሆነውን ሁላ አሸባሪ በማለት ያሳድሀል” በማለት የወሃቢያ ፕሮፖጋንዳን ዘዴ ሰውን ለመቀስቀሻነት ሲጠቀም ተስተውሏል፡፡ ከዚህ ቃል ጋር ብዙ ተዛማጅነት ያላቸው ቃሎች ሰዎች በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ሲጠቀሙበት ይስተዋላል ፡፡ መሰረታውያን (Fundamentalist).. “ነውጠኞች” በውጊያ የሚያምኑ (Militant) ፤ ጽንፈኖች ወይም ጠርዘኞች (Extremists) ፤ ስር ነቀሎች (Radicals) ፤ አክራሪዎች (fanatics) ፤ የሃይማኖት ጦረኞች (Jihadist ) ፤ የእስላማዊ  መንግስት አቀንቃኞች እስላማዊያን (Islamist) በመባል ይታወቃሉ፡፡  አክራሪ የሚለው መጠሪያ የተመረጠው ቡድን ለእምነቱ ፍጹም ቆርጦ የተነሳ ፤ እምነቱን ለድርድር የማያቀርቡ የሆኑ ነጥቦችን ብቻ መርጦ የሚያቀርብ በመሆኑ ነው፡፡ የአክራሪነት የመጨረሻው ግብ የሃይማኖቱን የበላይነት የሚያረጋግጥ ሃይማኖታዊ መንግስት Theocratic Government መመስረት ነው፡፡ ኢስላማዊያን የሚባለው አክራሪ ቡድንም ግቡ ይሄ ነው፡፡ የተለያየ ስም አንግተው ቢንቀሳቀሱም መዳረሻቸው ግን አንድና አንደ ብቻ ነው፡፡

Wednesday, March 13, 2013

“ፕሮፌሰር መስፍን የድብትርናን ሹመት የሚሰጡ በሆኑና በተቀበልኳቸው ደስታውን አልችለውም” ዲ/ን ዳንኤል ክብረት


  •   የኢትዮጵያ ታሪክ ከሸፈ ሊባል አይቻልም ፤ የኢትዮጵያ ታሪክ እኮ የተጻፈው ብቻ አይደለም ፤ ያልተጻፈ ብዙ ታሪክ አለ፡፡
  •  ፕሮፌሰር መርዕድ ሲሞቱ ፤ ፕሮፌሰር ታደሰ አልጋ ላይ ሲውሉ ጠብቆ የእነሱ ስራ ላይ ሂስ ማቅረብ ተገቢ አይደለም፡፡
  • ደርግ እኮ ከወደቀ 21 ዓመታት ተቆጥሯል፡፡ ታዲያ ለምን ከደርግ ውድቀት በኋላ መጽሀፉን ሳያሳትሙት ቆዩ? ስለ ኢትዮጵያ ታሪክ በምልአት ዛሬ ልትናገር አትችልም ፤ የኢትዮጵያን ታሪክ በአንድ ሰው እድሜ አትጨርሰውም፡፡
  •  የኢትዮጵያ ሕዝብ ተረድቼዋለሁ የማትለው ልዩ ሕዝብ ነው፡፡ አንድን ጉዳይ በቃ ጨርሷል ስትል ብድግ የሚል ፤ ተኝቷል ስትለው የሚነሳ ነው ፤ ከ1997 ዓ.ም በፊት የነበረውን 97 ላይ ለምንድነው ብድግ ያለው? ለሚለው እንኳን ተንትኖ የሚነግርህ የለም::
  •   መስፍን በቁጣ ስሜት ለኔ መልስ በማለት የጻፉት ጽሁፍ ምላሽ ያልሰጠሁት ለእሳቸው አክብሮት ስላለኝ ነው፡፡
(አንድ አድርገን መጋቢት 5 2005 ዓ.ም)፡- በዚህ ሰሞን የብዙዎች መነጋገሪያ ከሆነው ጉዳይ ውስጥ የዲ/ን ዳንኤልና የፕሮፌሰር መስፍን ጉዳይ መሆኑ ይታወቃል ፡፡ ፕሮፌሰሩ በ83 እድሜ ዘመናቸው በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ያዩትንና ያስተዋሉትን  በመጽሀፍ መልክ ለንባብ አብቅተዋል ፡፡ ዲ/ን ዳንኤልም ፕሮፌሰሩ የጻፉት መጽሀፍን በራሱ እይታ ተችቷል ፡፡ ይህ ጽሁፍ መጻፉ ፤ ለሂስ መቅረቡና ሰዎች የራሳቸው አስተያየት መስጠታቸው ተገቢ ቢሆንም ጥቂት አስተያየት ሰጪዎችና ሂስ አቅራቢዎች “ዲያቆን” የሚለውን ማዕረግ ከየት እንደተገኝ ፤ ለዲ/ን ዳንኤል ማን እንደሰጠው ያላስተዋሉ የፕሮፌሰሩን ወይም የዲ/ን ዳንኤልን ሃሳብ ከመሞገት ይልቅ ወደ ሰዎቹ ማዕረግ እና ስብዕና ላይ ያተኮረ አስተያየት ሲሰጡ ተስተውሏል ፡፡ ፕሮፌሰር መስፍንም የፕሮፌሰርነትን መአረግ ከመሬት ወድቆ እንዳላገኙት ሁሉ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንም የዲያቆንነት ማዕረግ ዝም ብሎ አይሰጥም ፡፡ ትንሽ ቢመስል ዋጋ ተከፍሎበታል ፡፡ ቤተክርስቲያን ለአንድ አገልጋይ የምትሰጠውን ማዕረግ አንቋሾ ፤ አውርዶ ፤ እንደማይገባው አድርጎ አስተያየት መስጠት “ባለቤቱን(ማዕረግ ሰጪውን)  ካልናቁ ….” ነው የሚሆነው፡፡ አንድ ሰው ስለ ዲ/ን ዳንኤል በሰጠው አስተያየት ላይ የፈለገው ማለት ይችላል ፤ ማዕረጉን ግን ከፍ ዝቅ ማድረግ ተገቢ ነው ብለን አናምንም ፡፡ ለማንኛውም የዲ/ን ዳንኤል አስተያየትን በአንባቢያ ጥያቄ መሰረት ከላይፍ መጽሄት ላይ በመውሰድ  እንዲህ አቅርበነዋል፡፡

Tuesday, March 12, 2013

ታሪክን የኋሊት “አቡነ ማትያስ ለቅዱስ ሲኖዶስ ያቀረቡት አቤቱታ”

  • ብዙ መከራ ውስጥ ተዘፍቃ የምትገኝው በአሜሪካ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሀገረ ስብከት ሲኖዶሳዊ ፍትሕ ርትዕን ትጠብቃለች፡፡
  • የእግዚአብሔር ባለ አደራ መሆን ቀላል ስላይደለ እያንዳንዳችን በእግዚአብሔር ፤ በታሪክና በሃይማኖት በምንመራቸው ምዕመናን ዘንድ በኃላፊነት እንጠየቃለን፡፡ ጌታ ቅዱስ ጴጥሮስን “ለዐይኬ አባግዕ” በማለት እየደጋገመ አደራ ያለው ምግብናውን በቀላሉ እንዳያየውና ቸልተኛ ሆኖ አደራውን እንዳይዘነጋ ነው፡፡
  •   ፓትርያርኩ በተቃራኒ መንገድ በመጓዝ ምን አይነት ጥቅምና የኅሊና ደስታ እንደሚሰጣቸው በፍጹም ሊገባን አልቻለም፡፡
  •  ቆቡ እንደው አንድ ጊዜ ከተሰቀለ በኋላ በቀላሉ የሚወርድ ወይም የሚሻሻል አይደለም፡፡ “ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ” (የጳጳሳትን ሹመትን በተመለከት ለቅዱስ ሲኖዶስ ያሳሰቡት)
  •  በስመ ሲኖዶስ  የሚጠቀሙት ባለስልጣኖች ሲኖዶሱን ባያሰድቡ መልካም ነው፡፡
  •  አንድ ወታደር በቂ የሆነ ትጥቅና ስንቅ ሳይሰጠው የጀነራልነት ማዕረግ ብቻ አሸክመው ወደ ጦር ሜዳ ቢልኩት ከጠላት ጋር ተፋልሞ የአገር ዳር ድንበር ማስከበር አይችልም፡፡ (ዝኒ ከማሁ) መንፈሳዊ ወታደርም ከዚህ የተለየ አይለም፡፡
(አንድ አድርገን መጋቢት 3 2005 ዓ.ም)፡-  በአሁኑ ሰዓት ስድስተኛ ፓትርያርክ አድርጋ ቤተክርስቲያን የሾመቻቸው አባት ከአመታት በፊት የሰሜን አሜሪካ ሊቀ ጳጳስ ሆነው ማገልገላቸው ይታወቃል፡፡ በወቅቱ በርካታ አስተዳደራዊ ግድፈቶችን ተመልክተው ማለፍ ያልቻሉት አቡነ ማትያት ለቅዱስ ሲኖዶስ የሚደርስ 20 ገጽ ደብዳቤዎችን ከበርካታ አባሪ ማስረጃ ደብዳቤዎች ጋር ለወቅቱ የቅዱስ ሲኖዶሱ ዋና ጸሀፊ ለብጹዕ አቡነ ኒቆዲሞስ ጥቅምት 12 1992 ዓ.ም አድርገው ልከው ነበር፡፡ ይህ የተላከው ሰነድ ቅዱስ ሲኖዶስ ተነጋግሮበት ውሳኔ እንዲሰጥበት መሆኑን አቡነ ማትያስ ይገልጻሉ ፡፡ ነገር ግን ከቅዱስ ሲኖዶስ ጽህፈት ቤት ያገኙት መልስ ቢኖር “አልደረሰንም” የሚል ነበር፡፡ ይህ በሴራ ለቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ እንዳይቀርብ የተደረገው ደብዳቤ የግል ጋዜጦች እንዲያወጡትን በፓትርያርኩ እና በዙሪያቸው ያሉ ሰዎች  እያደረጉ ያለውን ነገር ህዝቡ እንዲያውቅ ለማድረግ በአስቸኳይ የፖስታ አገልግሎት በወቅቱ ህትመት ላይ ለነበረው “ኢትኦጵ” መጽሄት ዋና አዘጋጅ ለአቶ ተስፋዬ ተገኝ ከተላከው ሰነድ እና በጊዜው ለህትመት ከበቃው ጋዜጣ ላይ መለስ ብለን አቡነ ማትያስ ምን አይነት ስሞታዎችንና ቅሬታዎችን ለሲኖዶስ እንዳቀረቡ ለማየት እንሞክራለን፡፡

Monday, March 11, 2013

ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝን አነጋገሩ


  • አቶ ኃ/ማርያም ለለቅዱስነታቸው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ካላት ተሰሚነት አንጻር በኢትዮጵያ እና በኤርትና መካከል ሰላም እንዲሰፍን የበኩሏን አስተዋጽኦ ታበረክት ዘንድ ጠይቀዋል


(አንድ አድርገን መጋቢት 2 2005 ዓ.ም)፡- ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ቤተክርስቲያኒቷ ስድስተኛ ፓትርያርክ አድርጋ ከሾመቻቸው በኋላ ስራቸውን በይፋ ከጀመሩ ዛሬ ስምተኛ ቀናቸው ይዘዋል ፡፡ አቡነ ማትያስ ከብጹአን ሊቃነ ጳጳሳት ጋር በመሆን ባሳለፍነው ሳምንት የኢፌድሪ ፕሬዝዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስን በቢሯቸው ተገኝተው ስለ ወቅቱ የቤተክርስቲያኒቱ ሁኔታ እና ቤተክርስቲያኒቱ ለሀገሪቱ አየሰራቻቸው ያሉትን ማህበራዊ እና መንፈሳዊ ጉዳዮች ላይ ፕሬዝዳንቱን ማነጋገራቸው ይታወቃል፡፡ ቅዱስነታቸው በመቀጠልም የሀገሪቱን ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃ/ማርያም ደሳለኝን በቢሯቸው በመገኝት እንዳነጋገሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡
በንግራቸው ላይ አገሪቱ የያዘችው የልማት ጎዳና ማስቀጠል ይቻል ዘንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርቲያን  የምታካሂደውን ዘርፈ ብዙ  ልማት አጠናክራ እንደምትቀጥል ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡ ቅዱስነታቸው ከውይይቱ በኋላ ለጋዜጠኞች እንደገለጹት ቤተክርስቲያኒቱ ከመንግሥት ጎን በመቆም  በአገሪቱ የሚካሄደውን ልማት  እንዲቀጥል የበኩሏን አስተዋጽ ታደርጋለች ብለዋል፡፡ በመላው ሃገሪቱ የሚገኙ አማኞች ከሌሎች የእምነት ተቋማት ጋር  በመተባበር በልማት ስራዎች እንዲሳተፉ እና ለሀገሪቱም እድገት አሻራቸው እንዲጥሉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡

Sunday, March 10, 2013

“ቤተ ክርስቲያን ከፖለቲካ ተጽእኖ ነጻ ሆና አታውቅም” ዲያቆን ዳንኤል ክብረት





  • መንግሥት ሙስናን ለመቀነስ የባለስልጣናትን ንብረት እንደመዘገበ ሁላ ቤተክርስቲያኒቱ የጳጳሳቱን ንብረት መመዝገብ ይኖርባታል፡፡
  • እስከ አሁን ብዙ ንብረት  በመያዝና በማስቀመጥ ክስ ያልተሰማባቸው አባት አቡነ ጳውሎስ ናቸው፡፡
  • ታምራት ላይኔ ጥገኝነት ለመጠየቅ ተናገረ የተባለውን ነገር እንደ ታሪካዊ ማስረጃ ለመውሰድ በግሌ እቸገራለሁ፡፡ ይህንን ካደረገ ቤተክርስቲያኒቱን ይቅርታ መጠየቅና ለተፈጠረው ቀውስም ሃላፊነት መውሰድ ይኖርበታል፡፡
  • የ6ኛ ፓትርያርክ ምርጫው ከመንፈሳዊነት ወጣ ባለ መልኩ የምረጡኝ አይነት የምርጫ ቅስቀሳዎች ነበሩ፡፡
  • እሳት በተነሳ ቁጥር ቦታህን እየለቀክ ከተሰደድክ ለችግሩ መፍትሄ መስጠት አትችልም፡፡
  • እርቀ ሰላሙ እንዲጀመር መንገድ የጠረጉት አቡነ ማትያስ ናቸው ፤ አቡነ ጳውሎስንና አቡነ መርቆሪዎስን ብቻቸውን ለማገናኝት እቅድ ነበራቸው ፡፡

 (አንድ አድርገን መጋቢት 2 2005 ዓ.ም)፡- ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከወቅቱ የቤተክርስቲያን ጉዳይን በሚመለከት ከላይፍ መጽሄት የመጋቢት ወር እትም ቁጥር 102 ጋር አጭር ቆይታ አድርጎ ነበር ፡፡ ዲያቆን ዳንኤል ቆይታው ይህን ይመስላል…. ያንብቡት

Thursday, March 7, 2013

“ተሀድሶን” ጠርገን ሳናስወጣ “ተዋህዶ” የሚሉ ደግሞ ብቅ ብለዋል


(አንድ አድርገን የካቲት 28 2005 ዓ.ም )፡- ከአመት በፊት በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጀርባ  ኤልያስ ወደ ምድር ወርዷል ትክክለኛ ሰንበት ቅዳሜ እንጂ እሁድ አይደለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አማኞች” መባል አንፈልግም እኛ የኢትዮጵያ ተዋህዶ አማኞች” ነን “ኦርቶዶክስ” የሚለው ስም ተለጥፎብን ነው እንጂ እኛን የሚገልጽ አይደለም ፤  የአሁኗ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ስርዓተ ቤተክርስቲያን አንዳድን ቦታ ላይ ትክክል አይደለችም ስለ አማላጅነትና መሰል ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ጋር የሚጣረስ ሃሳብ ያላቸው ቡድኖች በአሁኑ ሰዓት በመሀል አዲስ አበባ “ማኅበረ ስላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ አሃቲ የሰማይ ጉባኤ ዘቅድስት ቤተክርስቲያን ቅድመ መንበሩ ለእግዚነ ወእመፍጥረት ወላዲተ አምላክ” በሚል ስም ምእመኑን ግራ እያጋቡት ይገኛሉ፡፡

 እነዚህ ቡድኖች  ታላቁና የሚያስፈራው የእግዚአብሔር ቀን ሳይመጣ ነቢዩን ኤልያስን እልክላችኋለሁ።ትንቢተ ሚልክያስ  45 ኤልያስማ አስቀድሞ ይመጣል ሁሉንም ያቀናናልየማርቆስ ወንጌል 9 12 የሚሉትን የመጽፍ ቅዱስ ቃል መሰረት በማድረግ ነብዩ ኤልያስ ወደ ምድር ጳግሜ 5 2003 . እንደመጣ አብዝተው ይሰብካሉ ፡፡ ቦታው መሃል አራት ኪሎ ሲሆን በርካቶችን በተለያዩ በራሪ ወረቀቶች በመሳብ ላይ ይገኛሉ ፡፡  ቦታው ድረስ ሄደን እንደተመለከትነው አርቲስት ጀማነሽ ሰለሞንን የመሰሉ አርቲስቶች ቆብ ያጠለቁ መነኮሳትና ለማገልገል የሚፋጠኑ ወጣቶች በቦታው ላይ መመልከት ችለናል ፡፡ ተሀድሶያውያንም ሆኑ አሁን ላይ “ተዋሕዶ” ብለው ራሳቸውን ከእኛ ጋር እጅጉን በማመሳሰል የተነሱት ሰዎች መጨረሻቸው መንጋውን ከበረቱ ማስወጣት ነው፡፡ አሁን ላይ “ተዋሕዶ” የሚለውን ትርጉም ከአባቶች እንዳገኝነው በማለት የራሳቸውን ፍልስፍና ምዕመኑን እየጋቱት ይገኛሉ ፤ ጥቂቶች እስከ አሁን ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መባል አልነበረብንም በማለት የጉባኤያቸው ተካፋይ መሆን ጀምረዋል ፡፡ እያየን ያለነው ነገር የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አማኞችን አንገታቸው ላይ የሚያስሩት ክር ትክክል አይደለም ፤ “ከሰማይ የተሰጠው አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ቀለም ክር ነው” በማለት ምዕመኑን የበፊቱን እያስወለቁ አዲሱን የራሳቸውን ክር እያጠለቁለት ይገኛሉ… ይሄ ነገር ዛሬ ዝም ከተባለ ነገ በዝተው የባሰ ቀውስ እንዳያመጡም ስጋት አለን …ለማንኛውም በዚህ አመለካከት  የተጠመቀችው ለምስክርነትም በቃው የምትለው አርቲስት ጀማነሽ ምን እንደምትል ከየካቲት ወር እትም ከሚሺሪያ መጽሄት ጋር ያደረገችው ሙሉ ቃለ መጠይቅ ብሎጋችን ላይ ለጥፈንልዎታል ያንብቡት….

ጥቂት ከቃለ መጠይቁ የተወሰደ
  • ኦርቶዶክስ ሽፋን ነው፡፡ ቅባት ፤ ጸጋ ፤ ዘጠኝ መለኮት እያሉ በግድ አብረው ኦርቶዶክስ በሚል ሰንሰለት ከተዋሕዶ ጋር ጠፍረው አስረው አንድ ላይ ያስቀመጧቸው እምነቶች መሆናቸውን ተረድቻለሁ፡፡
  • ኦርቶዶክስ ማለት ጸጋን ቅባትንም ዘጠኝ መለኮትንም የሚጠቀልል ከሆነ እኔ ኦርቶዶክስ አይደለሁም ፡፡ አልፈልገውም ፤ አልቀበል፤ እኔ ተዋህዶ ብቻ ነኝ፡፡
  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሲባል ቀጥተኛዋ ተዋሕዶ  የሚሉ ስለሚመስለኝ እኔም በዚያ ስም ራሴን ስጠራ ነው የኖርኩትኝ፡፡ በቅዱስ ኤልያስ አዋጅ ላይ ነው ያየሁት ፡፡ የቅዱስ ኤልያስ አዋጅም “እነዚህ እምነቶች የክርስትና እምነት ስላሆኑ ከተዋህዶ ጋር አንድነት ስለሌላቸው የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ሲኖዶሱ ንስጥሮስን እንዳወገዙ ፤ አርዮስን እንዳወገዙ በእምነትም በዶግማም ስለማይመሳሰል አውግዛችሁ ልትለዩ ይገባል” የሚል ታላቅ አዋጅ ነው ያየሁት ፡፡ ይህን ግን ሲኖዶሱ አልተቀበለውም፡፡
  • ከአሁን ወዲያ ደግሞ እውነተኛውን ነገር እስካወቅን ድረስ  አንደ አባቶቻችን “የለም ፤ አይሆንም ፤ አንድ አይደለንም” ብሎ መቆም ደግሞ የኛ ፋንታ ነው፡፡
  • ተዋሕዶ ነን ብላችሁ ልዩነት ስትፈጥሩ ተሃድሶ እንደሚባለው ሊፈረጅ ይችላል የሚል ስጋት የለሽም? (ከጋዜጠኛ የቀረበላት ጥያቄ)
  • ቅባት ጸጋ የሚባሉት እኛን ተዋህዶ በመሆናችን የከሰሱን እና ወንጀለኛ የደረጉን ናቸው ፤ በሙሉ ገዳም ውስጠ ያሉት በዚህ ተይዘዋል ፤ ጥቂት ተዋህዶ አማኞች  በስቃይ የሚኖሩ አሉ፡፡
  • በአሁን ጊዜ ብዙ ሃይማኖቶች አሉ ፤ እውነት ግን ያለው በአንድ መንገድ ብቻ ነው ፤ አሷም ተዋህዶ ናት፡፡
  • ስንት ገዳም ገብቼ የስንት አባቶችን መስቀል ተሳልሜአለሁ ፡፡ ሳስበው ይዘገንነኛል ፡፡ ዋልድባን የሚያህል ቅዱስ ገዳም ነው በእንደዚህ አይነቶች ተሞልቶ ያገኝሁት፡፡ ዋልድባን የሚያህል የቅዱሳን አባቶች መቀመጫ ገዳም “ዘጠኝ መለኮት” የሚሉ መናፍቃን ግማሹን ይዘው እንዳሉበት አላውቅም ነበር፡፡
  • ታላቁ የእግዚአብሔር ቀን ከመምጣቱ በፊት የአባቶችን ልብ ወደ ልጆች የልጆችን ልብ ወደ አባቶች ይመልስ ዘንድ  ቅዱስ ኤልያስን እልክላችኋለሁ” ይላል አሁን ኤልያስ የመጣው ይህን ሊገልጥ ነው፡፡
  • እግዚአብሔር ከዚህ መስመር (ተዋሕዶ) ከሚያስወጣኝ ቢገለኝ እመርጣለሁ፡፡
  • ሶሪያ ትንቢተ ኢሳያስ ላይ እንደሚላት እየወደመች ነው ፤ አሜሪካ እንደምትጠፋ ራዕይ ላይ ተጽፏል
TO READ IN PDF CLICK HERE