Thursday, July 21, 2016

ስለ አባ ሚካኤል ገ/ማርያም የፅኑዋኑን ምዕመናን እንባ እና በሀዘን የተሰበረ ልብ ሂዱና አድምጡ




ከአላባ እና ከምባታ አካባቢ ምዕመናን የተሰማ የመጨረሻ ቃል….

 የጵጵስና ማዕረግ አስመራጭ ኮሚቴው ከቅዱስ ሲኖዶስ የተቀበለው ከባድ ሃላፊነት በመመልከት ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አባቶች ሊሆኑ ይችላሉ ያላቸውን መነኮሳትና ቆሞሳት በመቀበል ባስቀመጠው መመዘኛ መሰረትማለት ምንኵስናቸውና ገዳማዊ ሕይወታቸው አጠራጣሪና በቂ ማስረጃ የሌላቸው፤  በትውልድ አገራቸው በሥርዓተ ተክሊል ያገቡና ጋብቻቸውን ያፈረሱ፤  ጋለሞታዎች፤  ባለትዳሮችን የሚያማግጡ፤  ከተለያዩ ሴቶች የወለዱ፤  በአብነቱም በዘመናዊውም ትምህርት  የተጭበረበረ ማስረጃ የያዙ፤  ከተለያዩ አብያተ-ክርስቲያናት በምዝበራቸው የተባረሩ ጵጵስናውንም የዚኹ ሽፋን አድርገው ሀብት ለማድለብ የሚቋምጡ፤  በጠንቋይነትና አስጠንቋይነት፤ በመተተኛነት ለነፍስ መጥፋት ምክንያት የኾኑ፤  በእምነታቸው ጉልሕና ተጨባጭ ሕፀፅና ነቀፌታ ያለባቸው፤ ለፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ መናፍቃንም በኅቡእ የሚሠሩና ሽፋን የሚሰጡ፤  እጩዎችን በወንፊት ነፍቶ ብዙዎችን በመቁረጥ እዚህ ደረጃ ላይ 31 ያላቸውን በማስቀረቱ ሳናመሰግን አናልፍም፡፡ ነገር ግን እኛ በደንብ የምናውቃቸው ለዓመታት ምዕመኑን ሲያስለቅሱ የነበሩ አባ ሚካኤል ገ/ማርያም በዚህ መስፈርት ተመዝነው እዚህ ደረጃ መድረሳቸው አግራሞትን ፈጥሮብናል፡፡

Sunday, July 17, 2016

አባ ሚካኤል ገ/ማሪያም ፡ እንኳን ለጵጵስና ላሉበት ምንኩስና የሚያበቃ ሥነ-ምግባርና የመምራት አቅም የላቸውም


ቀን፡-  08/11/08 .
 ለኢ/////////ቤት
አዲስ አበባ

ጉዳዩ፦ ቆሞስ መላከ ጽዮን አባ ሚካኤል /ማሪያምን ይመለከታል
በስም ተጠቃሹ አባት የከምባታ ጠምባሮና ሀላባ /ስብከት /ቤት ሥራ አስኪያጅ ሲሆኑ በአሁን ሰዓት ለጵጵስና ማዕረግ መታጨታቸውን በመገናኛ ብዙሓን ተገልፆ ሰምተናል። ዳሩ ግን እኒህ አባት እንኳን ለጵጵስና ላሉበት ምንኩስና የሚያበቃ ሥነ-ምግባርና የመምራት አቅም ያላቸው አባት ሳይሆኑ ለምዕመናን መሰናከያ ከመሆናቸውም ባሻገር የቤተክርስቲያንን ህልውና ደፍረው የሚያስደፍሩ ናቸው። ለዚህም መገለጫ ከሚሆኑት ጥቂቶቹን ብንጠቅስ፦
1) ኮረዳዎችን ከዱራሜ ከተማ ወደ አዲስ አበባ ከተማ በመውሰድ ቤት ተከራይተው በቅምጥነት የሚያኖሩና ለሥራ ወደሄዱበት ሁሉ ይዘው በመዘዋወራቸው አገር ጉድ ያላቸው ናቸው።

2)የሥነ-ምግባር ጉድለት ያለባቸውን መንገደኛ የሆኑ መነኮሳትን በየአድባራቱ እያሰማሩ ቤተመቅደሶችን ያስመዘበሩ ናቸው። ለአብነት ብንጠቅስ፦

የራሳቸው ሰዎችን ፊርማ ለአስመራጭ ኮሚቴው ያቀረቡ ፡ አባ ሚካኤል ገብረማርያም

(አንድ አድርገን ሐምሌ 10 2008 ዓ.ም) እስከ አሁን ድረስ በተለያዩ መንገዶች የተጠቆሙ እና አስመራጭ ኮሚቴው እንደተቀበላቸው ከተገለጹት ቆሞሳትና መነኮሳት ስም ዝርዝር ውስጥ  አባ ሚካኤል ገብረማርያም ይገኙበታል፡፡
የከምባታ እና ሀላባ አካባቢ ሕዝብ ደግፎኛል በሚል አሰባሰብኩ ያሉትን የራሳቸው ሰዎችን ፊርማ ለአስመራጭ ኮሚቴው ያቀረቡት አባ ሚካኤል ገብረማርያም የከምባታ አላባ /ስብከት ስራ አስኪያጅ በዱራሜ ከተማ የሚገኘውን የጥምቀት በዓል ማክበሪያ ቦታን ከመናፍቃን ጋር በመሆን ያላቸውን የፖለቲካ ተቀባይነት ለማሳደግ ሲሉ አሳልፈው በመስጠጥ የሚታወቁ ፤ የቤተክርስቲያንን እርስት አሳልፈን አንሰጥም ያሉ የቤተ ክርስቲያናችን ተቆርቋሪዎችን አባቶቻችንን  ሽብርተኞች እያሉ የሚያሸማቅቁ ፤ በአውደ ምህረት እንዳያስተምሩ የታገዱትን የተሀድሶ ሰባኪያንን እርሳቸው በሚያስተዳድሩበት ሀገረ ስብከት እንደፈለጉ እንዲፈነጩበት በመፍቀድ(ለምሳሌ እነ በጋሻው በዱራሜ ተክለሃይማኖት ያደረጉት) አይሆንም የሚሉትን የቤተክርስቲያን ልጆች ደግሞ የተለያዩ ፖለቲካዊ አቅማቸውን በመጠቀም በማሸማቀቅ እና ባስ ሲልም በዛቻ እና በማስፈራሪያ እየታገዙ እጅግ ጥቂት አማንያን ያሉበትን አካባቢ እያወኩ የሚገኙ ሰው ናቸው፡፡

Thursday, July 14, 2016

ይህን እጩ ጳጳስ ይመልከቱት

በዝሙት ቅሌት በሴቶችና ሕጻናት ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ የተከሰሱት ‹‹አባ›› እንቁ ሥላሴ ተረፈ ከሴት ጓደኛቸው ጋር


  • ከ20 በላይ የድምጽ ማስረጃዎች በእጃችን ላይ ይገኛል

በስማቸው አብያተ ክርስቲያኒያቱን ያስመዘገቡ እጩ ጳጳሳት


ከጀርመን ምዕመናን የደረሰን
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በመጪው ጥቅምት በሚያካሂደው ርክበ -ካህናት ለመሾም ያሰባቸውን አባቶች ምዕመኑ ሃሳቡን እንዲሰጥበት መወሰኑ የሚያስመሰግነውና ከሃሜት ለመራቅ የሚያስችለው በመሆኑ ተገቢነቱን እንገነዘባለን። የተሰጠንን እድል በመጠቀምም የምዕመንነት ድርሻችንን መወጣት አለብን ብቻ ሳይሆን ይገባናልም።
 
ማንም ኤጲስ ቆጶስነትን ቢፈልግ መልካምን ስራ ይመኛል የሚለው ቃል የታመነ ነው።እንግዲህ ኤጲስ ቆጶስ እንዲህ ሊሆን ይገባዋል።የማይነቀፍ ልከኛ ራሱን የሚገዛ እንደሚገባው የሚመራ እንግዳ ተቀባይ ለማስተማር የሚበቃ ገር የሆነ የማይጨቃጨቅ የማይከራከር ገንዘብ የማይወድ ልጆቹን በጭምትነት ሁሉ እየገዛ የራሱን ቤት በመልካም የሚያስተዳድር ፤ ሰው ግን የራሱን ቤት እንዲያስተዳድር ባያውቅ የእግዚአብሔርን ቤት እንዴት ይጠብቃል? 1ኛ ጢሞ.3፡1-5 ይላል።

Friday, July 8, 2016

አባ ናትናኤል ከጵጵስና ውድድሩ ራሳቸውን በይፋ ካላገለሉ በቀጣይ ሌሎች ማስረጃዎችን ይፋ ለማድረግ እንገደዳለን!


ለምዕመናንና ለሚመለከታችሁ አካላት በሙሉ
አባ ናትናኤል የአየር ጤና ኪዳነምህረት አስተዳዳሪ ሆነው የተሸሙት ታኅሳስ 2005 ነው፡፡ አዋሳ ስላሴ / አስተዳዳሪ ከነበሩበት ከተሃድሶውን ጋር አብረው በፈጠሩት ሁከት፣ ዝርፊያ፣ የሰው ነፍስ ማጥፋት ሙከራ፣ የስነምግባር ችግር ተወንጅለው ከተባረሩ በኋላ ነበር በቀጥታ እኛ ጋር የተመደቡት፡፡ ላለፉት 4 ዓመታት ያው ባህሪያቸው እዚህም ሲያውክ ቆይቶ አሁን ደግሞ ለጵጵስና መታጨታቸው ስለተሰማ የአየር ጤና ምዕመን በየጊዜው ለሀገረስብከቱ ሲያቀርባቸው የነበሩ አቤቱታዎችን፣ ደካማ የአስተዳደር አቅማቸውንና ግልጽ የሙስና ተግባራቸውን የሚያሳዩ ማስረጃዎች ብቻ ቆንጥረን ይፋ ለማድረግ ተገደናል፡፡   ከጵጵስና ውድድሩ ራሳቸውን በይፋ ካላገለሉ ግን በቀጣይ ሌሎች ማስረጃዎችን ይፋ ለማድረግ እንገደዳለን!

Friday, July 1, 2016

ከጵጵስና ሽሽት


ረዣዥሞቹ ወንድማማቾች ተብለው የሚጠሩት አውሳብዮስ አሞንዮስ ዲዮስቆሮስና አውሳሚዮስ በቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት ላይ በብዙ መልኩ ይጠቀሳሉ። "አውሳብዮስ አሞንዮስ ተናግረውታል" የሚል ማስረጃ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ትርጓሜ መጻሕፍት ላይ ማግኘት የተለመደ ነው። እነዚህ ቁመታምና መልከ መልካም የነበሩት ወንድማማቾች ሕይወታቸውን ለቤተ ክርስቲያን የሠጡ የዘመኑን ፍልስፍና ተምረው በሃይማኖት እውቀት የመጠቁ ነበሩ። የእስክንድርያ ትምህርት ቤት ቀደምት ሊቃውንትን መጻሕፍትም እጅግ ያነበቡ ከሊቃውንት ተርታ የሚመደቡ የታሪክና የትርጓሜ መምህራን ነበሩ።