Tuesday, April 3, 2012

"ሰላማዊ ሰልፉ ላይ የተሳተፉት በሙሉ፥ ቤተክርስቲያንን የማይወክሉ ፖለቲከኞች ናቸው" አቡነ ፋኑኤል


ጆሮ አይሰማው ጉድ የለም!
ሰሞኑን በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ስለ ዋልድባ ገዳማችን ይዞታ እና ከፊታችን የተደቀነውን አደጋ በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን የኢትዮጵያን ዜና ጨምሮ ስንሰማው ቆይተናል፥ የሚገርመው ግን የኢትዮጵያ ዜና ዘገባ እና በሌላው ዓለም የሚዘገበው ዘገባ በጣም የተለያየ መሆኑ ብዙዎችን ዜጎች ይልቁንም ኦርቶዶክሳዊያኑን ግራ ሳያጋባ የቀረ አይመስለንም። 

ነገሩ እንዲህ ነው ባለፈው ጥቂት ሳምንት በፊት የቤተክርስቲያኑ ልጆች በአንድነት ተሰባስበው መልስ ባያገኙም ባይሰጥም ግንዛቤን ለማስጨበጥ ይረዳል ብለው እንደማንኛውም የሀገሪቱ ዜግነታቸው፣ እንደ ሃይማኖተኛነታቸው ድምጻቸውን ለማሰማት 1200 በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን  በዋሽንግተን ዲሲ ላይ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ፊት ለፊት ታላቅ ትዕይንተ ሕዝብ አድርገው እንደነበረ ለሁላችንም የተሰወረ አይደለም፥ በዚህ ሕዝባዊ ትዕይንት ላይ ከመላው ዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው ከሚከገኙ ቤተክርስቲያናት ወጣቶች፣ የሰንበት /ቤት መዘምራን፣ አረጋዊያን አባቶች እና እናቶች እንዲሁም ሕጻናት በዚሁ ሕዝባዊ ትዕይንት ላይ ተሳትፎ አድርገው እንደነበረ በተለያዩ የዜና መሰራጫዎች ተገንዝበናል፥ ከዚህ በተጨማሪ በጣም ጥቂት ከሚባሉት አብያተ ክርስቲያናት ካሕናት ተገኝተው ነበር እና ነገሩን ለማጣራት የዚህ ዝግጅት ክፍል በተለያየ መልኩ ሙከራ ስናደርግ ቆይተናል በሃገራችን ኢትዮጵያ ያለው ቤተክህነት ምንም ተስፋ የምጣልበት እንዳልሆነ በዘገባቸው ተረድተናል፤ በስደት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ካህናት አባቶች በተለይ ህይወታቸውን በምንኵስና የሚኖሩ የዋልድባን ጉዳይ ከማናቸውም የህብረተሰቡ ክፍል በተለየ ይቆረቆሩለታል የሚል በተለያዩ የህብረተቡ ክፍሎች ታስቦ ነበር፥ ነገር ግን ሊሆን ያልቻለበት ምክንያት ለሁላችንም እንቆቅልሽ ሆኖ ሰንብቷል። ለሁሉ በላይ ግን ትልቅ የህዝብ ተቃውሞ ያስነሳል ብለን የገመትነውን ለማጣራት በተለያዩ መንገዶች ሞክረን፣ ሁሉም መንገዶች ተመሳሳይ ናቸው፥ ነገሩ እንዲህ ነው። 
በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው ተሹመው የተመደቡት አቡነ ፋኑኤል በተለያየ ጊዜ ትልቅ ተቃውሞ ሲደርስባቸው ቆይቷል ተቃውሞውም እንደቀጠለ ነው፥ አሁን ባገኘነው መረጃ መሰረት ብፁዕነታቸው በዋሽንግተን ዲሲ ኢትዮጵያ ኤምባሲ ሰላማዊ ሰልፍ በተደረገበት ወቅት፣ የብዙዎች ክርስቲያኖች፣ ሀገር ወዳድ ማኅበረሰብ፣ የሀገር ሀብት እና ቅርስ መውደም እና መጥፋት የሚጨንቃቸው በሙሉ የብጹዕነታቸውን መምጣት እና የሰላማዊ ሰልፉ ተካፋይ እንደሚሆኑ ጠብቆ ነበር። ነገር ግን ብጹዕነታቸው ለሃገር፣ ለሃይማኖት፣ ለወገን እና ለቅርሶቻችን መጥፋት ተጨንቀው ድምጻቸውን ሊያሰሙ ከመጡት ኢትዮጵያውያን ጋር መሰለፍ ቀርቶ፣ በዚያው ዋሽንግተን ዲሲ ለሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ደብዳቤ ጽፈው "ሰላማዊ ሰልፉ ላይ የተሳተፉት በሙሉ፥ ቤተክርስቲያንን የማይወክሉ ፖለቲከኞች ናቸው" ብለው ለኢትዮጵያ ኤምባሲ ደብዳቤ ጽፈው ማስገባታቸውን ስንሰማ "ጆሮ የማይሰማው ጉድ የለም!" ብለን  ብዙ ሙከራዎችን ለማድረግ ችለናል፣ ይልቁንም ደብዳቤውን ለማግኘት የዝግጅት ክፍላችን ሙከራዎችን እያደረገ ይገኛል፤ እንደደረሰን እናቀርበዋለን።


እውን አቡነ ፋኑኤል ሕዝብን ለመንፈሳዊ አባትነት ሊመሩ ነው የመጡት ወይስ የመንግስትን አጀንዳዎች ሊያስፈጽሙ ነው የመጡት? መልሱን እርሳቸው ሊመልሱት ይችላሉ፥ ከዚህ በኃላም ለሕዝብ ያላቸውን ንቀት እና ጥላቻ በግልጽ አሳይተዋል ለቤተክርስቲያኒቱም መፍረስ እና ታሪክ፣ ሃይማኖት  ትውፊት መጥፋት ከመቼውም ጊዜ በላይ ተጠያቂነታቸውን የሚያመለክት ይመስለናል። በዚያ ቀን ዋሽንግተን ዲሲ ላይ የተደረገው ሰላማዊ ሰልፍ እርግጥ ነው ጥቂት የፖለቲካ ሰዎች ነበሩበት ብንልም፣ ፖለቲከኞችም እኮ ቢሆኑ ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን መዘንጋት የለብንም፥ እንደ ሃገር ዜጋ ብሎች እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይነታቸው ተቃውሞዋቸውን ማሰማት ተገቢ ነው ይጠበቅባቸዋልም፣ ነገር ግን እዳር ቁጭ ብሎ የበይ ተመልካች መሆን እና ወይም አብዛኛውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አማኝ ይልቁንም ከዚያው ከደብረ ምሕረት ቤተክርስቲያን የመጡትን ካህን እና ምዕመን ልክ እንደ ፖለቲከኛ መፈረጅ በእምነቱ የግፍም ግፍ የበደልም በደል ነው፥ እውን አቡነ ፋኑኤል ማንን ለመበደል ብለው ይሆን እንዲህ ያለ ትልቅ ክህደት በሕዝበ ክርስቲያኑ ላይ ሊፈጽሙ የበቁት ? ማንንስ ሊጠቅሙ ነው? እውነቱን ቀስ ብለን እንደርስበታለን ብለን እናምናለን፤ እርግጥ ነው ልሳናቸው በሆነው "አባ ሰላማ" በተሰኘው የጡመራ መድረክ የተናገሩት ነገሩን እውነት ለመሆኑ ግልጽ ማስረጃ ሊሆን ይችላል ስለ ዋልድባ ገዳም የተጻፈው በአባ ሰላማ ብሎግ ይጫኑት እዚህ   ይህ ብሎግ በተለያየ ጊዜ፣ ስለቤተክርስቲያን መጥፋት እና ስርዓት፣ ትውፊት፣ ቀኖና የሚሉትን ነገሮች ግድ እንደሌላቸው በግልጽ ሲናገሩ እና ሲጽፉ የሚታይ ጉዳይ ነው ታዲያ ዛሬ ከአባ ፋኑኤል ጋር ሆነው የዋልድባን አበረንታንት ገዳም መጥፋት እና መፍረስ እያዩ ሲሳለቁ ማየት የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች እንጂ በዓላማም በግብርም አንድ እንደሆኑ በግልጽ ያስቀመጡት ጉዳይ ነው።

የነዛ የዓለምን ትርኪ ምርኪ ትተው ለክርስቶስ ሕይወታቸውን ሰጥተው ረሃብን ጥሙን ታግሰው፣ ግርማ ሌሊቱን ታግሰው፣ ጤዛ ልሰው ሌት ተቀን እየጸዩ ሰውንና እግዚአብሔርን የሚያስታርቁ ገዳማውያን ባዕታቸው ተነካ ተደፈረ ብሎ ድምጹን ለማሰማት የወጣን ሕዝብ "ላም ባልዋለችበት፥ ኩበት ለቀማ" እንዲሉ ያለሃጢያቱ እና ያለግብሩ በሰጡት ስም ሳያንስ የሕዝብ ወገንተኝተታቸውን ባለማሳየታቸው ሳያንስ እንዲህ ዓይነት ስም በመስጠታቸው የአባቶቻችን አምላክ ይፋረደን እያልን እንሰናበታለን።
ቸር ወሬ ያሰማን

የተዋህዶ ቤተሰብ ከመላው አለም የተወሰደ

15 comments:

  1. ተዋቸው ዋጋቸውን እግዚብሔር ይከፍላቸዋል:: እንደዚህ እንደቀለድኩ የምኖር መስሏቸው ነው::

    ሰው ፊትን ያያል እግዚአብሔር ግን ልብንና ኩላሊትን ይመረምራል!!!

    ReplyDelete
  2. በስመ አብ፤ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አባ ሠላማ የአቡነ ፋኑኤል ነው እንዴ? የሚፅፏቸው በሙሉ እኮ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አስተምህሮዎች አይደሉም፡፡ እንጃ አይመስለኝም እንዲያ ከሆነ ግን ፕሮቴስታንት ጳጳስም ሊኖረን ነው፡፡ እኔ ይህን አላምንም ጭራሽ ፕሮቴስታንት ጳጳስ ቤተክርስቲያናችን ዉስጥ! ይኼ እንኳን አይደረግም፡፡

    ReplyDelete
  3. ለሰዎች በጣም ይገርመን ይሆናል እግዚአብሄር ግን የማያውቀው ነገር የለምና በትግእስትና በጸሎት እንጠብቃለን!!!

    ReplyDelete
  4. huluneme ngr lbalbitu mtwu yeshalale.

    ReplyDelete
  5. peace to all of u.I did no twant to write among our orthodox tewahdo members
    botI have to say something why we christians fght among ourselvesdo we belive onright faith?Ido not think so but I see about power and money I have read books histy is reapting zera yakob killed many clegys experts and bund our churches.the same thing u reapt his job at this time the problem u make it u bring it if u blieve tewahodo love brothers and sisters as ur self and love ur enemy too pray for orthodox tewahdo church don't bad name to ur fathers,brothers and sisters. let me ask u qustion when Jesus christ was on this earth they gave him bad name was he? ofcour not it is the same thing in our age pleas do not deastroy our chrch be childern of god May God bless u.

    ReplyDelete
  6. ለመላ፡ኢትዮጵያውያን፤
    "አስተበቍዐክሙ፡አኃዊነ፡ከመ፡ትትቀነይዋ፡ለእንተ፡ትውህበት፡ለቅዱሳን፡ሃይማኖት።"፡(ይሁ.፡፩፥፫)፡ወንድሞቻችን፥ለቅዱሳን፡አባቶቻችን፡የተሰጠችውን፡ሃይማኖት፡ተግባር፡አድርጋችኹ፡እንደትይዟት።የኛ፥የራሳችን፥ውርሳችን፥ቅርሳችን፡ብላችኹ፡እንድትጠብቋት፡ዐደራ፡እላችዃለኹ።
    በሃይማኖት፡የማይገኝ፡ነገር፡የለም።አገራችኹ፡ኢትዮጵያ፡ለዚህ፡እንግዳ፡አይደለችም።ከዓለም፡አህጉር፡በፊት፡እግዚአብሔርን፡የሚያውቁ፥እግዚብሔርም፡የሚያውቃቸው፥አገር፡ከነሀብቷ፡ከነክብሯ፥ሃይማኖት፡ከነሥርዐቷ፥ቋንቋ፡ከነፊደሉ፡ከነሥነ፡ጽሕፈቱ፥አስተዳደር፡ከነሕጉ፡ከነመብቱ፡አሟልቶ፡የሰጣቸው፡አባቶች፡ነበሯችኹ።በመሐልየ፡ሰሎሞን፡፯፥፲፬፥"ትርንጎዎች፡መዓዛቸውን፡ሰጡ፤በርሻችን፡የፍራፍሬ፡ዐይነቶች፡ዅሉ፡አሉ።ዐዲሱ፡ካሮጌው፡ጋራ፡አለ"፡እንዳለው፡በመንፈሳዊው፥በሥጋዊውም፡ብሉይ፡ከሐዲስ፡የተሟላላት፡አገር፡ነበረቻችኹ።ዛሬ፡ግን፡ዅሉም፡እየታጣ፡ነው።ኢትዮጵያ፡የገነት፡ጎረቤት፡እንደ፡መኾኗ፡(ዘፍጥረት፥፪፥፲፫)፡በገነት፡ያለ፡ሀብት፡ዅሉ፡በኢትዮጵያ፡አለ።ግን፡የሚወረሰው፡በሃይማኖት፡ስለ፡ኾነ፥ሃይማኖት፡ከሌለ፡ዅሉም፡የለም።ስለዚህ፥ዅሉን፡ዐጥቶ፡ከመቸገር፥ዅሉን፡ላለማጣት፡ሃይማኖተን፡ማግኘት።ነባሪቱን፡ሃይማኖታችኹን፡አጥብቃችኹ፡ያዙ፤ዅሉም፡የናንተ፡ይኾናል።እምቢ፡ብትሉ፥ፍርድ፡ይጠብቃችዃል።ወደ፡እግዚአብሔር፡ተመለሱ፤ይመለስላችዃል።ወደ፡እግዚአብሔር፡ቅረቡ፤ርሱም፡ወደናንተ፡ይቀርባል።ይህን፡ዐደራ፡በፍቅር፡እንድትቀበሉኝ፡በእግዚአብሔር፡ስም፡እማፀናችዃለኹ።

    አለቃ፡ዐያሌው፡ታምሩ

    ReplyDelete
  7. “ያለ መከራ ጸጋ ያለድካም ዋጋ አይገኝም” እንደተባለ ይሄ ሁሉ መሆኑ ለቤተክርስቲያን ታላቅ ሰማያዊ ዋጋ ሊያሰጣት ነዉና ክርስቲያኖች ሁሉ አይዟችሁ:: እነዚህ ጌታ አክብሮ በወንበሩ ቢያስቀምጣቸው ራሳቸውን ለውርደትና ለንቀት ያዘጋጁ ሁሉ ዋጋቸው ከጌታ ዘንድ ይሰጣቸዋል ደግሞም አይዘገይም ለነርሱ ዝምታው አለመኖር መስላቸዋል እንጂ::
    እኛ ግን እንደ ክርስቲያንነታችን በጾምና በጸሎት ዘወትር ማሳሰብን ችላ ልንል አይገባንም፡፡ እንኳን ዛሬና በዘመነ ሐዋርት እንኳ በውስጥ ያሉ የሀሰተኛ ወንድሞች ፈተና የነበረ ነው፡፡
    ከዚያም በላይ ነገሥታቱ በሰይፍና በስለት ሲያሰቃዩዋቸው እንደነበረ እሙን ነው፡፡ አባቶቻችን ግን በደምና ባጥንታቸው ሃይማኖታችንን ጠብቀው ለኛ አድርሰዉናል እኛም በነሱ ፈለግ ልንጓዝ ይገባናል ገና ደምን እስከማፍሰስ ድረስ አልደረሳችሁም ተብሏልና፡፡
    የቤተክርስቲን ራስ የሆነው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በውኑ ዝም ማለቱ ለምን ይሆን ብለን ራሳችንን ጠይቀን እናውቃለንን; እኛስ ምን ያህል በጎ ስዎቸ ነን? ለሃይማኖታችን ቀናኢነታችን ከልብ ነው ወይስ ለታይታ ብቻ?
    በእስራኤል ታሪክ አስራ አንዱን ነገድ አንዱ የብንያም ነገድ በጦርነት በተደጋጋሚ ድል ቢነሳቸውና ቢያሳፍራቸው ወደ እግዚአብሔር ቢጮሁ ያገኙት መልስ “መሸነፋችሁ ስለብንያም ነገድ ጽድቅ ሳይሆን በነገደ ብንያም የተሰራውን በደል የሚሰሩ በናንተ መካከል ስላሉ ነው እነሱ እስኪያልቁ ትሸነፋላችሁ አሁንም አልቀዋልና ወደ ሰልፉ ውጡ ድል ታደርጋላችሁ” የሚል እንደሆን እናውቃለን ስለዚህ እንባችን ከልባችን ተጋድሏችንም በመንፈስ በመቃጠልና በፍቅር ሊሆን ይገባል እላለሁ፡፡ ያን ጊዜ እግዚአብሔር ምህረት ዐይኖቹን ወደኛ ቁጣ ፊቱ ደግሞ በቤቱ ላይ ጦር ባወጁ መናፍቃን ላይ ያደርጋል ካልሆነ ግን ጥፋቱ ለሁላችንም ይሆንና ደስታው ለሳጥናኤል ብቻ ይሆናል::
    የቅዱሳን አምላክ እንደ እና የልቦና ክፋት ሳይሆን እንደ ቸርነቱ ይቅር በለን አሜን::

    ReplyDelete
  8. enanet betkerstian atwekulum betaghch

    ReplyDelete
  9. lemen yigermenal gena bezu neger yadergalu eko. Abune Fanueal is like begashaw lehayimanot yeminoru sew eko ayidelum. ewunet elalew egna zim benlem esachew hulem endetewaredu new ...mikniyatum sew ke hilina wekesa ayidenem easachewum agul kemayiwetubet elk wusti gebetew hulem yemayamenubetn dergit yifetsimalu genam sifetsimu yinoralu, gen mata mata kehilinachew gar sitagelu yaderalu. silezih hilinachew awardachewalech already.Niko metew new.

    ReplyDelete
  10. No worry at all times since We do not expect milk from Scorpions Like Abune Fanuel and his decedants . . .

    ReplyDelete
  11. Please read this article. I found it very interesting. http://www.ecadforum.com/Amharic/archives/2471

    ReplyDelete
  12. I have no idea why in all corner of us they need just only opposition or against the current adminstration... why ourselves wants to be the the judge?
    are we ignoring those who keep quit? do the writers, speakers ( yezemenu) thought they are the best....or can represent to all orthodox? pls let's analyz before we fight otherwise it might be the worst for some of us or all of us.
    Let's pray

    ReplyDelete