Tuesday, October 25, 2011

አነጋጋሪው እና አደናጋሪው የመጋቢ ሐዲስነት ጉዳይ…


  • መጋቢ ሐዲስ ለመባል ምን ያስፈልጋል ? 
  • ቤተክርስትያን ለምን አይነት መምህራን መጋቢ ሐዲስ የሚል የመአረግ ስም ትሰጣለች ?
  • መጋቢ ሐዲስ የሚል መአረግ ለተሰጠው አገልጋይ ከእሱ ምን ይጠበቃል ? 
የሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 8
18 ሲሞንም በሐዋርያት እጅ መጫን መንፈስ ቅዱስ እንዲሰጥ ባየ ጊዜ፥ ገንዘብ አመጣላቸውና።
19 እጄን የምጭንበት ሁሉ መንፈስ ቅዱስን ይቀበል ዘንድ ለእኔ ደግሞ ይህን ሥልጣን ስጡኝ አለ።
2ጴጥሮስ ግን እንዲህ አለውየእግዚአብሔርን ስጦታ በገንዘብ እንድታገኝ አስበሃልና ብርህ ከአንተ ጋር ይጥፋ
21  ልብህ በእግዚአብሔር ፊት የቀና አይደለምና ከዚህ ነገር ዕድል ወይም ፈንታ የለህም።
22 እንግዲህ ስለዚህ ክፋትህ ንሰሐ ግባ፥ ምናልባትም የልብህን አሳብ ይቅር ይልህ እንደ ሆነ ወደ እግዚአብሔር ለምን፤ 
23 በመራራ መርዝና በዓመፅ እስራት እንዳለህ አይሃለሁና።
                                                                                                  የሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 8 ፤18-23

አሁንም ባለንበት ዘመን እግዚአብሔር የሚገለገልበትን ነገር በገንዘብ ለማግኝት የሚጥሩ ፤ በገንዘብ ኃይል ቅስናውን፤ ድቁናውን፤ መጋቢ ሐዲስ ፤  ከፍተኛ ሐላፊነትን ፤ የደብር አስተዳዳሪነት ፤ሌሎች የቤተክርስትያናችንን የአገልጋይ ስሞችን  ማእረጉን ያገኙ ሰዎች አሉ ፡፡ የዛሬ ዓመት በዚህ ሰዓት ብዙ መነኮሳት ጵጵስናን ለመሾም ከ300,000-500,000 የኢትዮጵያ ብር በጉቦ መልክ ፤ በእጅ መንሻ መልክ ማቅረባቸው የዛሬ ዓመት ትውስታችን ነው፡፡ለእነዚህ ሰዎች የእኛ መልእክት ከላይ የሐዋርያት ላይ ‹‹የእግዚአብሔርን ስጦታ በገንዘብ እንድታገኝ አስበሃልና ብርህ ከአንተ ጋር ይጥፋ››  ካለው የጴጥሮስ መልዕክት የሚለይ አይደለም፡፡ የእግዚአብሔር ቁጣ መጥታ ከምታነዳቸው በንስሃ ህይወታቸውን ይመለከቱ ዘንድ  የዘወትር መልዕክታችን ነው፡፡


READ IN PDF click here


Click Read more to continue 



2 comments:

  1. ar befterachu wushet aytekmachum

    ReplyDelete
  2. Sirachihuna Hasabachihu hulu QINATINA MIKEGNINET Yetemolabeti newu. Kezihi Wetitachihu Melikam Negeri Lemaseb Mokirru.

    ReplyDelete