Sunday, August 14, 2011

በቅዱሳን ደም መጠየቅ እንዴት ያስፈራል?


በእግዚአብሔር አርአያና አምሳል የተፈጠረን የሰው ልጅ ነፍስ ማጥፋት ታላቅ ክፋት፣ ታላቅ በደል ነው፡፡ ይህንንም ጌታችን ‹‹እናንተ ግብዞች ጸፎችና ፈሪሳውያን የነቢያትን መቃብር ስለምትሠሩ፣ የጻድቃንንም መቃብር ስለምታስጌጡና ‹በአባቶቻችን ዘመን ኖረን በሆነስ በነቢያት ደም ባልተባበርናቸውም ነበር ስለምትሉ ወዮላችሁ፡፡ እንግዲያስ የነቢያት ገዳዮች ልጆች እንደሆናችሁ በራሳችሁ ላይ ትመሰክራላችሁ፡፡ እናንተ ደግሞ የአባቶቻችሁን መስፈሪያ ሙሉ ፤እናንተ እባቦች የእፉኝት ልጆች፣ ከገሃነም ፍርድ እንዴት ታመልጣላችሁ? ስለዚህ እነሆ ነቢያትንና ጥበበኞችን ፃፎችንም ወደ እናንተ እልካለሁ፤ ከእነርሱም ትገድላላችሁ፤ ትሰቅሉማላችሁ፤ ከእነርሱም በምኩራባችሁ ትገርፋላችሁ፤ ከከተማም ወደ ከተማ ታሳድዳላችሁ፤ ከጻድቁ ከአቤል ደም ጀምሮ በቤተ መቅደስና በመሰዊያው መካከል እስከ ገደላችሁት እስከ በራክዩ ልጅ እስከ ዘካርያስ ደም ድረስ በምድር ላይ የፈሰሰው የጻድቅ ደም ሁሉ ይደርስባችሁ ዘንድ፡፡›› በማለቱ እንረዳለን፡፡ (ማቴ 23፥29-36)

በቅዱሳን ደም መጠየቅ እንዴት ያስፈራል? ጌታችን ‹‹ወዮላችሁ››፣‹‹እናንተ እባቦች፣ የእፋኝት ልጆች››፣ ‹‹ከገሃነም ፍርድ እንዴት ታመልጣላችሁ?›› ‹‹በምድር ላይ የፈሰሰው የጻድቅ ደም ሁሉ ይደርስባችሁ ዘንድ›› በማለቱ የበደሉን ታላቅነት ፤ የቅጣቱንም አስከፊነት አመልክቷል፡፡ ወንድሙን ከገደለው ቃየል ሳይማር በነፍሰ ገዳይነት የተገኘው ላሜሕ ‹‹እኔ ጎልማሳውን ለቁስሌ ብላቴናውንም ለመወጋቴ ገድዬዋለሁና ቃየልን ሰባት እጥፍ ይበቀሉታል፤ ላሜሕን ግን ሰባ ሰባት እጥፍ›› ብሏል፡፡ (ዘፍ 4፥24)

‹እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ››

No comments:

Post a Comment