Wednesday, March 21, 2012

ወጣቶቹ እና ርብርቡ


ተጨማሪ ፎቶዎች



(የአንድ ሰው አስተያየት)
እናንተ የተዋህዶ የቁርጥ ቀን ልጆች...ፎቶአችሁን በፍቅርና በስስት ሀዘን በሰበረው ልቤ...እንባን በተሞሉ አይኖቼ ደግሜ ደጋግሜ ቅድምም አሁንም ቆይቼም ደግሞ እንደ አዲስ አያቸዋለሁ:: የሆነብን ሁሉ ልብን የሚያደማ ቢሆንም ግን ደግሞ ያደረጋችሁት ጊዜ የማይሽረውና ትውልድ የማይዘነጋው በመልከሙ ተጋድሎአችሁ ኮራሁ  ለካስ ቤተ ክርስቲያን ልጆችዋ ተወልደው አልቀሩም...ለካስ አድገውላታል....ለካስ እንደ ቀደሙት አበው ስለ እርስዋ ዛሬም ለእሳት የተዘጋጁ ልጆች አሉዋት!!!...ብዬ...ኩራቴና ትምክህቴ ትክክል ሆኖ አገኜሁትና....ልቤና አይኔ በሲቃ አብረው አነቡ...ፍቅራችሁ ማረከኝ....በሩቅም ሁኜ ናፈቅሁዋችሁ...ኩራታችን...መጽናኛወቻችን ናችሁና ኑሩሉን...እናንተም የኔ እኔም የእናንተ በመሆኔ...በወገኔ ምንኛ...ኮራሁ!!!....ግን ደግሞ ቀናሁባችሁ...አምላክ ከክፉ ይጠብቃችሁ...ተባረኩ...ሌላማ ምን ይባላል...?...!!!...ተመስገን...!!!


ቤተ ክርስቲያን የወላድ መካን አለመሆኗን ያረጋገጥንበት ወንድሞችና እህቶች በሁሉ የስራ ሁኔታና ደረጃ ያሉ ማህበረ ምዕመናን ወምዕመናት በእውነት ያኮራል፡፡ ስለዚህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ መጠራታችሁንና መመረጣችሁን ታጸኑ ዘንድ ከፊት ይልቅ ትጉ፤ እነዚህን ብታደርጉ ከቶ አትሰናከሉምና። እንዲሁ ወደ ዘላለሙ ወደ ጌታችንና መድኃኒታችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ መንግሥት መግባት በሙላት ይሰጣችኋልና። ስለዚህ እነዚህን ነገሮች ምንም ብታውቁ በእናንተም ዘንድ ባለ እውነት ምንም ብትጸኑ፥ ስለ እነዚህ ዘወትር እንዳሳስባችሁ ቸል አልልም። ሁልጊዜም በዚህ ማደሪያ ሳለሁ  በማሳሰቤ ላነቃችሁ የሚገባኝ ይመስለኛል። 2ጴጥ.110-13


የገዳማውያኑ አባቶች ምስጋና 
‹‹
ለቦታው ተቆርቋሪ ከሆነው ወገን የቀረ ሰው የለም፡፡ የዩኒቨርስቲ ተማሪው፣ የከተማው ወጣት፣ የሰንበት /ቤት ተማሪዎች፣ ፖሊሱ፣ መከላከያው በአጠቃላይ ሕዝበ ክርስቲያኑ እዚሁ ነው ያለው፡፡ በተለይ ወጣቱ ለቦታው ታላቅ ባለውለታ ነው፡፡ ሃይላንዳቸውን ብቻ ይዘው ተራራውን ወጥተው ከዚህ መድረሳቸው ብቻ ለእኛ አለኝታ ነው፡፡ እግዚአብሔር ሐሳባቸውን ያስፈጽምላቸው፡፡ ውለታቸው በሰው ተነግሮ የሚያልቅ አይደለም፡፡ ቦታውን ታድገውታል፡፡››


















 እኛ እንሙት በደጅሽ

ላዩ ታቹ ተናዶ
የቆመውም ተንጋዶ
እሳት በእሳት ሲደራረብ
በነፋሱ ሲርገበገብ
ያንች ልጆች አርበኞቹ
የቁርጥ ቀን ደራሾቹ
ተመሙልሽ ከያሉበት
ጠላትሽን ለመመከት
ተዋሕዶ
ክፉውሽን ከሚያሳየን
ለመከራሽ ከሚያቆየን
እኛ እንሙት በደጅሽ
ያሳደግሽን ልጆችሽ
ቀሲስ ያሬድ ገብረ መድኅን
/
መታሰቢያነቱ በዝቋላ ደብረ ከዋክብት ገዳም እሳት በማጥፋት ተግባር ላይ ለተሰማሩ ወጣቶች/



























18 comments:

  1. እግዚአብሔር ይባርካችሁ በጣም ታኮራላችሁ

    ReplyDelete
  2. አምላክ ያክብርልን

    ReplyDelete
  3. አምላክ ያክብርልን

    ReplyDelete
  4. Egziabhere Yibarkachu!

    ReplyDelete
  5. Thanks for updating us always.

    ReplyDelete
  6. Egziabher Dikamachihun yikuterlachihu

    ReplyDelete
  7. ሀገራችንን እግዚአብሄር ለዘላለም ይባርክ፡፡ እግዚያብሄር ይባርካችሁ

    ReplyDelete
  8. Wud yekurt ken lijoch

    Abet and mehon endet des yilal. Hagerachin yan hulu mekera yalefechiw lijochua and honew yemetawin hulu silemeketut new. Mengist bekuankua ena bezer yekefafele bimeslewim endih yale chigir, hazen, simeta wede andinet yimelesal lenegeru kegize hehuala yemetabin tata silehone gena wustachinim altewahadenim. Yekidusan Amlak bezihch eminetachin ena hagerachin lay and yadirgen.

    ReplyDelete
  9. እግዚአብሔር ይባርካችሁ በጣም ታኮራላችሁ::አቡዬ ለችግራችሁ ይድረሱላችሁ

    ReplyDelete
  10. መሀበር ይድድያ ዘልደታMarch 21, 2012 at 11:04 PM

    እግዚያብሒር ፍጻሚያችውን ያሳምርልን ጉልነታችውን ይባርክ

    ReplyDelete
  11. Egziabher kekfu hulu yitebkachu. ke tsadiku bereket yikfelachu! behayimanot yatsnalin! photowachun bayehuna basebkuwachu kutr befikr bedsta aleksalehu.

    ReplyDelete
    Replies
    1. በመጀመሪያ እግዚአብሔር ክብሩ ይስፋ ይህንን ትልቅ የእምነትና የታሪክ ቦታ ስለጠበቀልን፡፡ በመቀጠል እጅግ በጣም ፈታኝ በሆነው ቦታ ገብተው ለመታደግ የታገሉትን ወጣቶች እድሜ፣ ጤና ፍቅር ይስጥልን፡፡

      Delete
    2. በመጀመሪያ እግዚአብሔር ክብሩ ይስፋ ይህንን ትልቅ የእምነትና የታሪክ ቦታ ስለጠበቀልን፡፡ በመቀጠል እጅግ በጣም ፈታኝ በሆነው ቦታ ገብተው ለመታደግ የታገሉትን ወጣቶች እድሜ፣ ጤና ፍቅር ይስጥልን፡፡

      Delete
  12. Amlake Kidusan wagachihun yikfelachihu YEBETEKIRISTIAN YEKURT KEN LIJOCH.

    ReplyDelete
  13. geta hoy silekidusan bileh yikir belen. igziabher yibarkachihu

    ReplyDelete
  14. melkam sira keminim Yibeltal, bertu

    ReplyDelete
  15. በታም የሚያኮራ ግደል ነው የሰራቸሁት ፃድቁ አቡዬ በዘመናቹ ሁሉ የልባችሁን መሻት ይፈፅሙላችሁ! ! !!.

    ReplyDelete