Friday, September 9, 2011

አክራሪ ሙስሊሞች 3 ክርስትያኖችን በድንጋይ ገደሉ



ደሴ አሬራ እየተባለ በሚታወቅ አካባቢ በሚገኘው የደብረ ሣህል ቅዱስ ዐማኑኤል ፀበል ተፀብለው ወደ መኖሪያ ቤታቸው እየተመለሱ በነበሩ ወጣቶች ላይ፣  ጳጉሜን 3 ቀን 2003 ዓ.ም ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ላይ በአካባቢው ያሉ አክራሪ ሙስሊሞች  አስበው እና አልመው ሲጠብቋቸው በነበሩ ክስርትያኖች ላይ የድንጋይ ናዳ በማውረድ ጥቃት አድርሰውባቸው ወዲያው አንድ ሰው የገደሉ ሲሆን ፤  ሌሎች ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸው ደሴ ሪፈራል ሆስፒታል ከገቡት ብዙ ክርስትያኖች ውስጥ አንዲት ሴት እና አንድ ወንድ በህክምና ላይ እያሉ የደረሰባቸው ጉዳት ከፍተኛ በመሆኑ ህይወታቸው ሊያልፍ ችሏል፡፡በአሁኑ ሰዓት የተለያዩ አካላቸውን በጥቃቱ የተጎዱ ክርስትያኖች በሆስፒታሉ ይገኛሉ፡፡የመጀመሪያው ሟች ከፍተኛ ጉዳት ልቡ ላይ ደርሶበት ነው፡፡


በአካባቢው የነበሩ የአይን ምስክሮች ጠይቀን እንደተረዳነው ጉዳቱ የደረሰባቸው በጠመጠሙ አክራሪ ሙስሊሞች መሆኑን የተረዳን ሲሆን ደጀሰላም ላይ የተዘገበው ግን ‹‹አንዳንድ ምንጮች ለጥቃቱ በሰኔ ወር የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የእገዳ ውሳኔ ያስተላለፈባቸው “መምህር ግርማ” የተባሉትን አጥማቂ ተከታዮች›እንደሚጠረጠሩ ብለው የዘገቡት የተሳሳተ እና የተዛባ መረጃ ስለሆነ እንዲስተካከል ስንል እንጠይቃለን፡፡ ይህን መረጃ ቦታው ድረስ ሄደው ወይንም ጉዳቱ ደርሶባቸው በሆስፒታል ያሉትን ሰዎች አናግሮ እና አጣርቶ መዘገብ ያለበለዚያ ደግሞ ጉዳዩ እስኪጣራ እና ጉዳት ያደረሱት ሰዎች እስኪለዩ ድረስ በይሆናል የተሳሳተ መረጃ ለክርስትያኑ ማድረስ ተገቢ አለመሆኑን በዚህ አጋጣሚ ለመግለፅ እንወዳለን፡፡

ሀሰት አንናገር እውነትን አንደብቅም
‹‹እግዚሐብሔር ቤተክርስትያንን ይጠብቅ››

4 comments:

  1. እግዚአብሔር ይስጣችሁ:: ለእውነት ስለቆማችሁ እግዚአብሔር በረከቱን ያብዛላችሁ::

    ReplyDelete
  2. This is continuous tragic event. Christians should unit and stop this for ever.

    ReplyDelete
  3. ኢትዮጵያ ታበፅሕ እደዊሃበ ለ እግዚአብሔር ።

    ባጎረስኩኝ እጄን ተነከስኩኝ።

    ህዝባችን ና አገራችን ከህሊና ባርነት ነፃ እናውጣ።

    አሜን።

    ReplyDelete
  4. እግዚአብሔር ይስጣችሁ:: ለእውነት ስለቆማችሁ እግዚአብሔር በረከቱን ያብዛላችሁ::

    ReplyDelete