Friday, August 3, 2012

ፍልሰታ ለማርያም



(አንድ አድርገን ሐምሌ 27 2004 ዓ.ም) ፡- ይህስ ለሚያምኑት ነው «ለእናንተ የእግዚአብሔርን መንግስት የማወቅ ስልጣን ተሰጥቷቹኋል» ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምሳሌ በሚያስተምርበት ጊዜ ደቀ መዛሙርት ለምን በምሳሌ እንደሚያስተምር በጠየቁት ጊዜ የሰጣቸው መልስ ከላይ ያለውን ይመስል ነበር። ዛሬም የእግዚአብሔር መንግስት ስልጣን እና ስራ ሁሉን ቻይነት እና አድራጊነት ያልተረዱ ሁሉ እግዚአብሔርን አሰራር የሚቃወሙበት ብዙ አጋጣሚ አለ። ይህ ደግሞ በጣም አስቸጋሪ ነው ምክኒያቱም ሰው የእግዚአብሔርን ስራ ተቃወመ ማለት አምላክነቱን እና መለኮታዊ የሆነውን ስልጣኑንም ተጋፋ ማለት ነው። በመሆኑንም እኛ ለምናምነው የእግዚአብሔር ኃይል ስለሆነው እና ሕዝቡንም ሁሉ ለመንግስቱ ተገዢ ስላደረገው ስራ ሁሌም ቢሆን በእምነት እና በድፍረት እንናገራለን።


ፍልሰታ ለማርያም «ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር» ፍልሰታ ማለትፈለሰከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ማዛወር የነበሩበትን ሀገር ለቆ ወደ ሌላ ሀገር መሰደድ መፍለስ ማለት ነው፡፡ ጾመ ፍልሰታ ሲባልም የእመቤታችን ሥጋ ከጌቴሰማኒ ወደ ገነት መፍለስን በኋላም በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር ከነበረበት መነሣቱን ለማመልከት የሚነገር ነው፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም 64 ዓመት በዚህ ዓለም ኖራ በሞት ከተለየች በኋላ እንደ አንድ ልጅዋ ሞታ መነሣቷንና ዕርገቷን ያዩ ዘንድ ሐዋርያት ከነሐሴ 1 እስከ 16 የጾሙት ጾም ነው፡፡

ጾመ ፍልሰታ ከሰባቱ ዐበይት አጽዋማት አንዱ ሆኖ በቀኖና እንዲጾም ከተወሰነበት ጊዜ ጀምሮ ምእመናን ይጾሙታል፡፡ እመቤታችን 5485 . ከአባቷ ከኢያቄም ከእናቷ ከሐናእም ሊባኖስ ትወጽዕ መርዓት፡፡ ከሊባኖስ ሙሽራ ትወጣለችተብሎ በተነገረው መሠረት ነሐሴ 7 ቀን ተጸነሰች፡፡ ግንቦት አንድ ቀን ሊባኖስ በምትባል ወረዳ በብጽአት እንደተወለደች የቤተክርስቲያን ታሪክ በሰፊው ያስረዳል፡፡ በጾም በጸሎት በአስተብቁዖት የተገኘች ናት፡፡ ንጽሕት በመሆኗም ማኅደረ እግዚአብሔር ሆናለች፡፡ እመቤታችን ከእናትና ከአባቷ ዘንድ ሦስት ዓመት፣ በቤተ መቅደስ 12 ዓመት፣ ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ 33 ዓመት ከሦስት ወር፣ ከዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ዘንድ 14 ዓመት ከዘጠኝ ወር ጠቅላላ ድምር 64 ዓመት ሲሆናት ጥር 21 ቀን 49 ዓመተ ምሕረት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች፡፡ ነቢያት አስቀድመው ስለ እመቤታችን እረፍትና ትንሳኤ በምሥጢር ተናግረዋል፡፡

ነቢዩ ዳዊት በመዝሙር መዝ 136:8 “አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ አንተና የመቅደስህ ታቦትብሎአል፡፡ ፈጣሪዬ ሆይ ምእመናንን ወደምታሳርፍበት ወደ መንግሥተ ሰማያት የመቅደስህን ታቦት ድንግል ማርያምን ይዘህ ተነሥ ሲል ነው፡፡ ይህም እመቤታችን እንደ ልጅዋ ትንሣኤ መነሣቷን የሚያመለክት ነው፡፡ ታቦት ያላትም ማደሪያው ስለሆነች ነው፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞንወዳጄ ሆይ ተነሺ ውበቴ ሆይ ነይ እነሆ ክረምት አለፈ ዝናቡም አልፎ ሄደ አበቦች በምድር ላይ ተገለጡ፡፡ የዜማም ጊዜ ደረሰ የቀረቃል በምድራችን ተሰማ፡፡ በለሱ ጐመራ ወይኖችም አበቡ መዓዛቸውንም ሰጡ፡፡ ወዳጄ ሆይ ተነሺ ውበቴ ሆይ ነይሲል ስለ እመቤታችን በምሳሌ ተናግሮአል፡፡ መኃ 2:1-13 ወዳጁን ውበቱን ተነሺ ነይ እያለ የተጣራው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ተጠሪዋም እመቤታችን ናት፡፡ እነሆ ክረምት አለፈ ማለት በስደት በአይሁድ የዘወትር ጠላትነት በልጅዋ መከራና ስቅላት ስምዖን በቤተ መቅደስ እንደተናገረ ልቧ በሀዘን ሠይፍ የተከፈለበት በሀዘን ፍላጻ የተወጋበት የመከራ ክረምት /ወቅት/ አልፎ የክርስቶስ ሕማሙ ሞቱ፣ ቤዛነቱ ተፈጽሟል፡፡ ትንሣኤው በምድር ላይ ተገልጧል፣ ተሰብኳል ማለት ነው፡፡ በምድራችን አበባ ታይቷል ማለት የሐዋርያት ድምፅ በምድር ሁሉ ደርሷል ማለት ነው፡፡ ነቢዩ ዳዊት ድምፃቸው ወደ ምድር ሁሉ ቃላቸውም እስከ ዓለም ዳርቻ ወጣ ብሎ ስለ ሐዋርያት የተናገረው በዓለም ያለውን መከራ ስድት ሲገልጽ ነው፡፡ መዝ 18:4:: የዜማም ጊዜ ደረሰ ያለው የመከራን ጊዜ ነው፡፡ ሸለቆችም በእህል ተሸፈኑ በደስታ ይጮሃሉ፣ ይዘምራሉም ተብሏል፡፡ መዝ 14:13 የመከር ጊዜ ደረሰ የተባለው መከር የፍሬ ጊዜ በመሆኑ ክርስትና አፍርቷል ማለት ነው፡፡ በለሱ ጐመራ ማለት ደግሞ በጐ ምግባረ ፍሬ ሳያፈሩ የነበሩ ሰዎች በጐ ምግባር መሥራት መጀመራቸውን የሚያሳይ ነው፡፡ በመጨረሻም ወይኖች አብበዋል፣ መዓዛቸውንም ሰጥተዋል እንደተባለ በመላው ዓለም አብያተ ክርስቲያናት በሃይማኖት ማበብ መዓዛ ምግባራቸውን ማቅረብ ከጀመሩ በኋላ እመቤታችን ዐረፈች፡፡
እመቤታችን ጥር 21 ቀን ዕረፍት በሆነበት ዕለት ሐዋርያት የእመቤታችንን ሥጋ ለማሳረፍ ወደ ጌቴሰማኒ መካነ ዕረፍት /የመቃብር ቦታ/ ይዘው ሲሄዱ አይሁድ በቅንዓት መንፈስ ተነሣሥተው ቀድሞ ልጅዋን በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተነሳ፡፡ በአርባኛው ቀን ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ እንደገናም ተመልሶ ይህን ዓለም ለማሳለፍ ይመጣል፡፡ እያሉ በማስተማር ሕዝቡን ፈጽመው ወስደውታል፡፡ አሁን ደግሞ ዝም ብለን ብንተዋት እርሷንም እንደ ልጅዋ ተነሣች ዐረገች እያሉ በማስተማር ሲያውኩን ሊኖሩ አይደለምን: ተሰብሰቡና በእሳት እናቃጥላት ብለው ተማክረው መጥተው ከመካከላቸው ታውፋኒያ የተባለው ጐበዝ አይሁዳዊ ተመርጦ ሄዶ የእመቤታችንን ሥጋ የተሸከሙትን አልጋ ሽንኮር ያዘ፡፡ የአልጋውን ሽንኮር በያዘ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ በእሳት ሠይፍ ሁለት እጁን ስለ ቆረጣቸው ከአልጋው ሽንኮር ላይ ተንጠልጥለው ቀሩ፡፡ ታውፋንያ በፈጸመው ድርጊት ተጸጽቶ ወደ እመቤታችን ስለተማጸነ በኅቡዕ ተአምር የተቆረጡ እጆቹን እንደ ቀድሞ አድርጋ ፈውሳዋለች /ስንክሳር ዘጥር/፡፡ የእግዚአብሔር መልአክ የእመቤታችን ሥጋ ከሐዋርያው ዮሐንስ ጋር ተድላ ደስታ ወደ አለባት ገነት በመንፈስ ቅዱስ ተነጠቁ፡፡ ጌታም የእመቤታችንን ሥጋ ታወጣ ዘንድ ምድርን እንዲጠሩዋት ሰባቱን የመላእክት አለቆች አዘዛቸው፡፡ እነርሱም ትወጪ ዘንድ እግዚአብሔር አዞሻል አሏት፡፡ ያን ጊዜም ከዕፅ ሕይወት በታች ካለ መቃብር የእመቤታችን የማርያም ሥጋዋ ወጣ፡፡ ጌታችንም ዘላለማዊ ወደሆነ መንግሥተ ሰማያት መላእክት እና ሰማዕታት እየሰገዱላት አሳረጓት፡፡ ንጉሥ ዳዊትበወርቅ ልብስ ተጐናጽፋ ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለችእንዳለ፡፡ መዝ 44:9:: ወንጌላዊ ዮሐንስም ከእርሷ በረከትን ተቀብሎ ተመልሶ ከሰማይ ወረደ፡፡ ሐዋርያት ተሰብስበው ስለ እመቤታችን ሥጋ ፈጽሞ ሲያዝኑና ሲተክዙ አገኛቸው፡፡ እርሱም እንዳየ እንደሰማ ሥጋዋም በታላቅ ክብር ማረጉን ነገራቸው፡፡ ሐዋርያትም ዓመት ሙሉ ቆዩ፡፡ የነሐሴም ወር በባተ /በገባ/ ቀን ዮሐንስ እንዲህ አላቸው፡፡ የእመቤታችንን ሥጋዋን ለማየት ኑ፤ ሁለት ሱባኤ በመጾም እንለምን አለ፡፡ በጾም በጸሎት ሱባኤ ያዙ፤ ጌታም የእመቤታችንን ሥጋ አምጥቶ ስለሰጣቸው በታላቅ ዝማሬ፣ በውዳሴና በጽኑ ምሕላ ወስደው ቀድሞ በተዘጋጀው መካነ እረፍት በጌቴሴማኒ ቀበሯት፡፡ የእመቤታችን የቀብር ሥነ ሥርዓት በተፈጸመ ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ቶማስ አልነበረምና ከሀገረ ስብከቱ በደመና ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመጣ እመቤታችን በተቀበረች በሦስተኛው ቀን እንደ ልጅዋ ትንሣኤ ተነሥታ ስታርግ ያገኛታል፡፡ ትንሣኤዋን ሌሎቹ ሐዋርያት አይተው ለእርሱ የቀረበት መስሎት ተበሳጭቶበመጀመሪያ የልጅሽን ትንሣኤ አሁን ደግሞ የአንቺን ትንሳኤ ሳላይ ቀረሁብሎ ከማዘኑ የተነሣ ከደመናው ተወርውሮ ሊወድቅ ቃጣው፡፡ እመቤታችንም ከእርሱ በቀር ሌሎቹ ሐዋርያት ትንሳኤዋን እንዳላዩ ነግራው አጽናንታው ሄዶም ለሐዋርያት የሆነውን ሁሉ እንዲነግራቸው አዝዛው ምልክት ይሆነው ዘንድ ሰበኗን /መግነዟን/ ሰጥታው ዐረገች፡፡ ሐዋርያው ቶማስም ኢየሩሳሌም በደረሰ ጊዜ እመቤታችንን እኮ ቀበርናት ብለው ነገሩት እርሱምሞት በጥር በነሐሴ መቃብር እንዴት ይሆናል?” አላቸው፡፡አንተ እንጂ የጌታን ትንሣኤ ተጠራጠርክ አሁንም አታምንምን!” ብለው በቅዱስ ጴጥሮስ መሪነት ወደ እመቤታችን መካነ መቃብር ይዘውት ሄደው መቃብሩን ቢከፍቱ ሥጋዋን አጡት፡፡ ደነገጡም፡፡ ቶማስምአታምኑኝም ብዬ እንጂ እመቤታችን ተነሥታ ዐርጋለችብሎ የሆነውን ሁሉ ነገራቸው፡፡ ለማረጋገጫ ምልክት እንዲሆን የሰጠችውን ሰበኗን አሳያቸው፡፡ ሰበኗን /መግነዟን/ ለበረከት ቆራርጠው ከተከፋፈሉ በኋላ ወደየአህጉረ ስብከታቸው ሄደዋል፡፡ ሐዋርያትም ትንሣኤሽን ቶማስ አይቶ እኛ እንዴት ይቀርብናል ብለው ከነሐሴ አንድ ቀን ጀምረው ሱባኤ ገቡ፡፡ በሱባኤው መጨረሻ በነሐሴ አሥራ ስድስት ቀን ጌታችን ጸሎታቸውን ተቀብሎ እመቤታችንን መንበር፣ ቅዱስ ጴጥሮስን ንፍቅ /ረዳት/ ቄስ፣ ቅዱስ እስጢፋኖስን ገባሬ ሰናይ /ዋና/ ዲያቆን አድርጐ ቀድሶ ሁሉንም ከአቆረባቸው በኋላ የእመቤታችንን ዕርገቷን ለማየት አብቅቷቸዋል፡፡

ቤተክርስቲያናችንም ሥርዓት ሠርታ ከሰባቱ ዓበይት አጽዋማት ተርታ አስገብታ ይህን ታላቅ የበረከትና የምሥጢር መግለጫ ጾም እንድንጾም አድርጋናለች፡፡ ሐዋርያት ያዩትን ድንቅ ምሥጢር የእመቤታችንን ትንሳኤና ዕርገት ለማየትና ከሐዋርያት አበው በረከት ለመሳተፍ ጌታችንልጆቼይላቸው ለነበሩ ሐዋርያት አምሳል ሕፃናትና ወጣቶች፣ ሴቶችና ወንዶች፣ አረጋውያንም የጻመ ፍልሰታን መድረስ በናፍቆት እየጠበቁ በየዓመቱ በጾም በጸሎት ያሳልፉታል፡፡ የእመቤታችን ትንሣኤና ዕርገት መታሰቢያ /በጾመ ፍልሰታ/ ወቅት ብዙዎች ከቤታቸው ተለይተው በመቃብር ቤት ዘግተው፣ አልጋና ምንጣፍ ትተው፣ በመሬት ላይ ተኝተው ዝግን ጥሬ እፍኝ ውኃ እየቀመሱ በጾምና በጸሎት በመትጋት በታላቅ ተጋድሎ ይሰነብታሉ፡፡ በሰሙነ ፍልሰታ ምእመናን ለእመቤታችን ያላቸውን ጽኑና ጥልቅ ፍቅር የሚያሳዩበት ነው፡፡ ጌታችን ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት በከርሰ መቃብር ቆይቶ ሙስና መቃብር ሳያገኘው፣ መግነዝ ፍቱልኝ መቃብር ክፈቱልኝ ሳይል በሥልጣኑ እሑድ በመንፈቀ ሌሊት እንደተነሣ ሁሉ እርሷም በተቀበረች በሦስተኛው ቀን ማኅደረ መለኮት ናትና ሙስና መቃብር ሳያገኛት መግነዝ ፍቱልኝ፣ መቃብር ክፈቱልኝ ሳትል የልጅዋ ሥልጣን ኃይል ሆኗት መነሣቷን ትንሣኤዋከመ ትንሣኤ ወልዳ፤ እንደ ልጅዋ ትንሣኤነው ተብሎ ሲከበርላት ይኖራል፡፡ በዚሁ በነሐሴ 16 ቀን የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ፍልሰቱ ነው፡፡ ሥጋው ከፋርስ ሀገር ወደ ሀገሩ ወደ ልዳ በክብር የፈለሰበት ነው፡፡ ፍልሰቴን ከፍልሰትሽ አድርጊልኝ፣ ብሎ ለምኗት ስለነበር ፍልሰቱ ከእመቤታችን ፍልሰት ጋር እንዳሰበው ሆኖለታል፡፡ ስለዚህም እርሷን መውደዱ የሚያውቁ ሥዕሉን ከሥዕሏ አጠገብ ይስላሉ፡፡ በስሙ ለሚማጸኑ የድኅነት ወደብ ይሆን ዘንድ፡፡
ሌላው ታሪክ ድግሞ እናታችን ድንግል ማርያም ሞትን ድል አድርጋ ልክ እንደ ልጇ ተነስታ ባረገች ጊዜ ለቶማስ የሰጠችውን ሰበን ሐዋሪያት ተከፋፍለው ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ጋራ ይዘው ወደየ አገረ ስብከታቸው በዓለም ወንጌልን ለመስበክ ዞረዋል በሄዱበት ስፍራ ሁሉ ከጌታችን መስቀል ጋራ የድንግል ማርያምን ሰበንም ይዘው ዞረዋል። ዛሬም ይህን ምሳሌ በማድረግ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ጋራ የሚይዙት ጨርቅ የዚህ ምሳሌ ነው። ድንግል ትንሳኤሽ እስከምናይ ድረስ…….. ትንሳኤ ማለት ከሞት በኌላ በነፍስ ብቻ ሳይሆን በስጋምና በነፍስ ሕይወት ማግኘት ማለት ነው። ትንሳኤ ከትንታዊና ተስፋን ያዘለ እንደሆነ መጽሐፍ ቅሱስ ይነግረናል፡ «ሙታን ሕያዋን ይሆናሉ ሬሳቸውም ይነሳሉ» .ኢሳ 2619 ይህ የሚያሳየው የትንሳኤን እውነታ ነው። ምክኒያቱ እስካሁን ድረስ ትንሳኤን የማያምን ሕዝብ እና ሰው ስላለ ነው። በአንድ ወቅት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሰዱቃውያን ትንሳኤ ሙታን የሚባል ነገር የለም ብለው ሲሞግቱት እንዲህ ማለቱን እንመለከታለን «….ኢየሱስም እንዲህ አላቸው መጽሐፍትን እና የእግዚአብሔርን ቃል አታስተውሉም እና ትስታላችሁ» ማቴ.2129 ይልቁንም ቅዱስ ዳዊት እንዳለው እንዲህም ያለ ነገር እናያለን «ስለዚህ ልቤን ደስ አለው ምላሴም አሴት አደረገች ሥጋየ ደግሞ በተስፋ ታድራለች ነፍሴን በሲኦል አትተዋትምና » መዝ.1619 የትንሳኤ ክብር እና የትንሳኤን እውነታ ያስረዳናል። እኛ የሰው ልጆች ትንሳኤ ሙታን መኖሩን ከተረዳን ዘንድ አሁን ደግሞ አንድ ማወቅ ያለብን እውነት አለ ይህም የጌታችን እናት ድንግል ማርያም ልክ እንደ ልጀዋ ማረጉዋን እና መነሳቱዋን ነው። ምክኒያቱም ነቢዩ ሳዊት በትንቢቱ እንዲህ ብሎዋል «ቅዱሱንም መበስበስን ያይ ዘንድ አትተወውም» እንዳለው ድንግል እናታችንም ሞት ድል ለማድረግ የልዋን ኃይል ኃይል አድርጋ ተነስታለች። በመሆኑም እኛ የተዋሕዶ አማኞች ይህን በማመን ሁሌም የድንግልን ትንሳኤ ለማየት እና ከበረከቱዋም ተሳታፊ ያደርገን ዘንድ እንደ ሐዋሪያት በአንድ እና በመንፈስ በመሆን ሱባኤ እንይዛለን፡ በዚህ ወቅት አብዛኞቻችን ልባችንን ፍጹም አሳረፈን ወደ አምላካችን በማቅናት ስለ በደላችንም የምናለቅስበት እና የልቦናችንን ዓይንም ያበራልን ዘንድ የምንጸለይበት ወቅት ነው። የድንግል ማርያም ምልጃ እና በረከት ከሁላችንም ጋራ ይሁን። ለአባቶቻችን ለቅዱሳን ሐዋርያት ጸጋና ኃይልን የሰጠች እመቤታችን በረከትና ጸጋን ታድለን፡፡ አማላጅነቷ አይለየን አሜን፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር
By: Abel Kassahun

6 comments:

  1. Girum ena wekitawi new, kale hiwot yasemalin!!!!

    ReplyDelete
  2. "ማኅደረ መለኮት ናትና ሙስና መቃብር ሳያገኛት መግነዝ ፍቱልኝ፣ መቃብር ክፈቱልኝ ሳትል የልጅዋ ሥልጣን ኃይል ሆኗት መነሣቷን" እናምናለን ፡፡
    ቃለ ሕይወት ያሰማልን

    ReplyDelete
  3. amen wo amen leykun leykun........ye emebetachin dngle maryam amalajinet ena bereket ayileyen.....

    ReplyDelete
  4. አሜን ቃለ ሕይወት ያሰማልን፡፡

    ReplyDelete
  5. አሜን ቃለ ሕይወት ያሰማልን፡፡

    ReplyDelete
  6. አሜን ቃለ ሕይወት ያሰማልን፡፡

    ReplyDelete