Monday, December 12, 2011

የእግዚአብሔርን ስራ አድንቁ ፤ ‹‹ በንብ ሰራዊት የሚጠበቀው ቤተክርስትያን ››

በንብ የሚጠበቀው የቦሌ በሻሌ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ሚካኤል፣ ቅዱስ እስጢፋኖስ ወአቡነ ሠላማ ቤተክርስቲያን በሕዳር 12 / 2004 ዓ.ም ለሚከበረው የቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓል ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በዋዜማው ሕዳር 11 ቀን ዋዜማ ቆመው ሳለ ከምስራቅ አቅጣጫ አውራውን አስቀድሞ እየተመመ የመጣው የንብ መንጋ ቤተክርስቲያኗን ዞሮ ጣራዋ ሸራ ግድግዳዋ ሳጠራ ወደሆነችው ቤተመቅደሷ ብቻ በተሰራው (ቅድስት እና ቅኔ ማኅሌት የሌለው አነስተኛ መጠን ያላታ ቤተክርስቲያን ላይ) የቃልኪዳኑ ታቦተ ሕግ ባረፈበት መንበር ውስጥ መንጋው ንብ ገብቶ ሰፍሯል። የንቡ መንጋ ወደ መንበሩ ሲገባ በአገልግሎት ላይ ያሉትን ካህናት ሳይነካ አገልግሎቱም ሳይታጎል አድሯል። በሕዳር 12 ምንም እንኳን ካህናቱ ስጋት ቢገባቸውም ታቦተ ሕጉን ማውጣት ግዴታ ነውና አስፈላጊውን ስርዓተ አምልኮ ከተፈፀመ በኋላ ታቦተ ሕጉ ከመንበረ ክብሩ ሲወጣ የንቡም ሠራዊት ከመንበሩ በምስራቅ በኩል ወተው አንድም ምዕመን ሳይነድፉ አብረው ከታቦቱ ጋር አክብረው ወደ መንበሩ ሰፍረዋል። አሁንም በመንበሩ ውስጥ ይገኛሉ። የመንበር ውስጥ ማርም ማኅበረ ምዕመናኑ እየበላ ከቅዳሴ ፀበሉ ጋር እየጠጣ ድኅነተ ሥጋና ድኅነተ ነፍስን እያገኙ ይገኛሉ።


ሊቃውንት ይህን ተዓምር ሲተረጉሙ፡ 
ንቡ ሠራዊተ መላእክት (ነገደ ቅዱስ ሚካኤል) ናቸው ብለው በዕለቱ አስተምረውናል ይህም በተግባራቸው የተገለጸ ነውና እንደምን ቢሉ ከቀናት ተመርጦ በሕዳር 12 ዋዜማ መምጣታቸው ሕዳር 12 ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት ተብሎ የተሾመበት እስራኤላውያንን ከግዞት አውጥቶ በምድረበዳ የመራበት መናን ያዘነበበት መታሰቢያ ዕለት ነውና በበዓለ ሲመቱ ክቡራን ንዑዳን የሚሆኑ ሠራዊተ መላዕክት በምስራቅ በኩል በምትገኘው በስተምስራቅ በኩል ስብሐተ እግዚአብሔር በሚደርስበት ሰዓት መተዋልና ነው። አንድም በአካባቢው የተለያዩ ዛፎች እንዲሁም መኖሪያ ቤቶች ሳሉ በዚህች ቅድስት ቤተመቅደስ ውስጥ የቅዱስ ሚካኤል እና የቅዱስ እስጢፋኖስ ታቦተ ሕግ ባለበት መግባታቸው ሠራዊተ መላእክት ናቸው  በማለት ተዓምሩን ተርጉመዋል።

ሌላ ተዓምር
 በሕዳር 21 ቀን 2004 ዓ.ም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ የሆነችው ታቦተ ጽዮን ዳጎንን ድል አድርጋ በክብር የተመለሰችበትን በዓል በሚከበርበት ዕለት ካህናት በሥርዓተ ቅዳሴ ላይ ሳሉ ከየት መጣ ተብሎ የማይታወቅ እጅግ ብዙ የሆነ የንብ መንጋ ዳግም ወደዚህች ቤተክርስቲያን መጣ። ድምፁ ያስደነገጣቸው ቀዳስያን ካህናት እና ምዕመናን (በቁጥር እጅግ ጥቂት የሆኑ) ምን መጣ? ወይስ የመንበሩ ንቦች ወጡን? በማለት ሲደናገጡ ከዲያቆናት መካከል አንዱ ወጥቶ ቢመለከት በጉልላቱ ስር የመስቀል ምልክት ሰርተው በጣራው ላይ ብዙሃኑ ሲያርፉ የቀረው ቤተክርስቲያኗን ይዞራል። “በልዎ ለእግዚአብሔር ግሩም ግብርከ፡ እግዚአብሔርን ስራህ ድንቅ ነው በሉት” እንዳለ እጹብ ከማለት በቀር ምን ማለት ይቻላል? ይህም የንብ ሠራዊት ሥርዓተ ቅዳሴው ሲያበቃ አዲስ በተሰራችው፣ በመጠኗ አነስተኛ የሆነውችው ቤተልሔም ውስጥ ገብቶ ሰፍሮ ይገኛል። ከደብሩ አገልጋይ ካህናት ውስጥ አንዱ ቄስ ገብተው ሲያጥኑና የንቡን ሁኔታ ሲመለከቱ ከመግባቱ ገና በ10ኛ ቀኑ ማር ለመስራት የሚያስፈልገውን የመጀመሪያ ደረጃ እንደጀመረ የደብሩ አስተዳዳሪ መልዓከ ፀሐይ ሲራክ ገበየሁ በታሕሳስ 1 ቀን 2004 ዓ.ም በተዘጋጀው ልዩ መርሐ ግብር ላይ ለምዕመናን ተናግረዋል።
በደብሩ እየተደረጉ ካሉ ተዓምራት ውስጥ ለአብነት ያህል፡
  • በከባድ የራስ ምታት በሽታ  (ማይግሬን) ለ15 ዓመታት ሲሰቃዩ የነበሩ አንድ ምዕመን ከመንበሩ ውስጥ በወጣችው አንድ ንብ ራሳቸውን ተነድፈው ድነዋል።
  • በእብድ ውሻ ተነድፎ ይሰቃይ የነበረ ምዕመን በህክምና ማዕከል የውሻውን አንገት ካላመጣህ ልትድን አትችልም ተብሎ እየተሰቃየ የነበረ ፤ በቦታው መጥቶ በሁለት ንቦች የተነከሰበት ቦታ ተነድፎ ከበሽታው ሙሉ በሙሉ ድኗል።
  • አንዲት ምዕመን ለ5 ዓመታት ያህል በአእምሮ በሽታ አብዳ ቤተሰቦቿን የማታውቅ የነበረች ከማሩ ጸበል ወስደው ቢያጠጧት በ5ኛው ቀን ድና ምስክርነት ሰጥታለች።
  • በኪንታሮት በሽታ ለብዙ ዘመናት ሲሰቃይ የነበሩ ምዕመን ከመንበሩ የተቆረጠውን ማር ተቀብተው ድነዋል።
  • ለብዙ ጊዜ መስማት ተስኖት የነበረ ምዕመን ማሩን በጥብጦ በጆሮው ውስጥ ቢከት ወዲያው ድኖ መስማት ችሏል።
  • እጅና እግሯ ሲንቀጠቀጥ የነበረች ሴት በፀሎት ላይ ሳለች በአንድ ንብ ተነድፋ ወዲያውኑ ከበሽታዋ ድናለች።
  • በአስም፣ በጨጓራ፣ በኩላሊት፣ በደም ግፊት፣ በጭንቀት በሽታ ሲሰቃዩ የነበሩ ምዕመናንም ማሩን ጠጥተው፤ ከመንበሩ በሚወጡ ንቦች ተነድፈው ድነው ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።

“ምንተ ንግበር አሀዊነ፡ ወንድሞች ሆይ ምን እናድርግ።” (ሐዋ. 2፡ 37)
ይህች ቅድሰት ቤተክርስቲያን እጅግ ብዙ የሆነ ገቢረ ተዓምራትን እያደረገች የምትገኝ የሠማይ ደጅ ናትና ገና ብዙ ምዕመናን ድኅነተ ሥጋንና ድኅነተ ነፍስን የሚያገኝባት ናትና እኛ ሕዝበ ክርስቲያን በረከተ ሥጋ ወነፍስ የሚያሰጡ አገልግሎቶች ላይ እንድንሳተፍ ቤተክርስቲያኗ ጥሪ እያደረገች ትገኛለች። ከሁሉ በፊት በጸሎት እንዲያስቡን እየጠየቅን በሃሳብ፣ በጉልበት፣ በገንዘብ ከቤተክርስቲያናችን በረከትን እንዲያገኙ ቢችሉ ወደ ቦታው ድረስ በመምጣት እንዲያዩ፤ ያልቻላችሁ በመደወል አስፈላጊውን መረጃ በሰፊው ማግኘት ትችላላችሁ እንላለን። አሁን ቤተክርስቲያኗ ምን ያስፈልጋታል?

  1. ቤተክርስቲያንን መስራት፡ አሁን ያለችበት ቤተክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በቆርቆሮ የተሰራ ሲሆን ይህም የመጀመሪያዋን ቤተክርስቲያን ከሸራና ሳጣራ መጠኗ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ቆርቆሮ በቆርቆሮ ለብሳለች ፤ እንዲሁም ካህናት ቅኔ ማኅሌት የሚቆሙበት፣ ምዕመናን የሚያስቀድሱበትና ክቡር ሥጋውንና ክቡር ደሙን የሚቀበሉበት ግድ በመሆኑ ከመቅደሱ ተቀጥሎ በፎቶው ላይ እንደምታዩት ቆርቆሮ የለበሰ ቅኔማኅሌትና ቅድስት ተሰርቷል። ይህ ግን ለዘላቂው የሚሆን ሳይሆን ለጊዜው ለአገልግሎቱ ተብሎ ሲሆን ለዘላቂው ግን ቋሚ ቤተክርስቲያን መስራቱ ግድ ነው። ይህንንም የደብሩ ሕንፃ አሰሪ ኮሚቴ አስፈላጊውን እያደረገ ሲሆን እርሶም ይህ ሕንፃ ቤተክርስቲያን በመልካም ተጀምሮ እንዲፈጸም በጸሎቶ ያስቡን። እንዲሁም ለቤተክርስቲያኗ ማሰሪያ ይሆን ዘንድ በማቴርያል ወይም በገንዘብ ለቤተክርስቲያኗ በደረሰኝ መስጠት እንደምትችሉ እና ከበረከቱ እንድትሳተፉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።



ለበሻሌ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ሕንፃ ግንባታ የሚያስፈልጉ
1
ሲሚንቶ
340 ኩንታል
2
አሸዋ
79 ሜትር ኩብ
3
ጠጠር
46 ሜትር ኩብ
4
ድንጋይ
30 ሜትር ኩብ
5
ብሎኬት
2592 በቁጥር
6
የብረት መስኮት
1.8 x 4.75 (8.55 ካሬ)= 3 በቁጥር
0.9 x2.5 (2.25ካሬ) =10 በቁጥር
0.8 x1.9 (1.52ካሬ)= 7 በቁጥር
1.2 x1.4 (1.68ካሬ) =3 በቁጥር
7
መስታወት
76 ካሬ ሜትር
1. ቀለም ስራ እስቱኮ
36 ኪሎ
2. ግሎ
ኪሎ
3. ቀለም 
112 ሊትር
4. ጂፕሰም
18 ኪሎግራም
8
የእንጨት በር
0.9 x2.5= 3በቁጥር
1.2 x2.6
1በቁጥር
9
ቆርቆሮ ጣሪያ
252 በቁጥር
10
አሸንዳ
90 ሜትር
11
1. ባህር ዛፍ አጠና (10-12)
20 በቁጥር
2. ምስማር
ኪሎግራም
12
ባህር ዛፍ ውቅረት
1. አጠና (8-10)
32 በቁጥር
2. ምስማር
7ኪሎግራም
3. ሞራሌ (5x7)
37 በቁጥር
4. ምስማር
ኪሎግራም
13
ከፈፍ ጣውላ
1. ጣውላ
36 በቁጥር
2. ምስማር
12 ኪሎግራም
14
ኮርኒስ
1. ሞራሌ(5x5)
300
2. ቺፕውድ
280 ካሬ ሜትር 100 በቁጥር
3. ምስማር(6 cm)
18 ኪሎግራም
4. ምስማር (3cm)
18 ኪሎግራም
15
ወለል
ሊሾ 225 ሜትር ካሬ
16
ቶንዲኖ ብረት (ፌሮ)
6 =136 ኪሎግራም
8= 442 ቤርጋ
10= 4 ቤርጋ
12 =132 ቤርጋ
14= 49 ቤርጋ
16= 38 ቤርጋ
20=12 ቤርጋ


 መልዕክት
እኛም ከቆምንለት አላማ አንዱ የእግዚአብሔርን ተዓምር ለእናንተው ከማድረስ በተጨማሪ ፤ የሚሰሩ አብያተክርስትያናትን ሰዎች በቻሉት መጠን እንዲረዱ መንገድ ማሳየት ስለሆነ እርስዎም ለዚህ ቤተክርስትያን ከቻሉ በአካል በመገኝት ተመልክተው ፤ ካልቻሉ በተቀመጠው ስልክ ተጠቅመው የአቅምዎን እንዲረዱ በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን::  

እዚህ ቦታ ለመድረስ ከፈለጉ ከመገናኛ ሀያት አደባባይ ትራንስፖርት ከያዙ በኋላ አደባባዩ ጋር ወርደርው በስተቀኝ በኩል የ30 ደቂቃ መንገድ በእግር ገባ እንዳሉ ያገኙታል፡

ለበለጠ መረጃ ስልክ፡ 
0911563714 
(መልዓከ ፀሐይ ሲራክ የቤተክርስቲያኗ ዋና አስተዳዳሪ) ይደውሉ።

“በኃይልህ ሰላም፥ በጌጠኛ ቤትህም ልማት ይሁን።”
 መዝ. 122፡7
ምንጭ፡ የደብረ ፀሐይ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን አስተዳደር ጽ/ቤት ታሕሳስ 1/ 2004 ዓ.ም

from  www.holyfathersundayschool.blogspot.com

15 comments:

  1. kalehiwot yasemalen

    ReplyDelete
  2. Egziabehere altawaneme aytawaneme.

    ReplyDelete
  3. ሀይ... አንድ አድርገን...እንዴት ናችሁ...ስለ ኃይማኖታችን ፖስት ምታደሪጓቸው ነገሮች በጣም አስደሳች አስተማሪ ነገሮች ናቸው በዚህ በርቱ እላለሁኝ፡፡ ነገርግን የራሴን አስተዋጽኦ ለማበርከት ያመቸኝ ዘንድ የሚላከው ገንዘብ በትክክል ለተፈለገው አገልግሎት በትክክል መድረሱን እና በምን መልኩ መላክ እንደሚቻል (ለማን ፣ የት) በትክክል የቤተክርትያኑማህተም ያረፈበትን አድራሻ በአስቸኳይ ብታሳውቁን ደስ ይለናል፡፡
    ልዑል እግዚአብሔር እትዮዽያን ይባርክ፡፡
    አሜን

    ReplyDelete
  4. Eziabehere kegna gare yehun!

    ReplyDelete
  5. BOTAW YET AGER NEW?

    ReplyDelete
  6. This comment has been removed by a blog administrator.

    ReplyDelete
  7. Ke Hayat Adebabay be Sunshine realestate korekonch menged ketita sihedu yagegnutal and Kemeri bebajaj beru lay yadersotal.... zare nege saylu yehidu

    ReplyDelete
  8. ሴጣን ሊያሳስት ሃገራችን ላይ ቢሮጥም ቸሩ እግዚአብሔር ግን ይህችን ሃገር ከቶ እንዳልተዋት ዛሬም እያሳየን ነውና ክብርና ምስጋና ለአምላካችን ይሁን:: እናንተም ይህን መልካም ተዓምር ስላካፈላችሁን እግዚአብሔር ይስጥልን:: ሁላችንንም ለዚህ በረከት ተካፋዮች ያድርገን::

    ReplyDelete
  9. For the infromation u post I want thanks u alot. But I want to say something that is please try to explain the location in details to give the society full information

    ReplyDelete
  10. egig betam des yilal bertu egiziabhier kenantegar yihun

    ReplyDelete
  11. Thank you for the correction of the source site.
    Egziabher Yebarkachehu and keep it up!

    ReplyDelete
  12. Egziabher Yebarkachehu Betam Enameseginalen Kebetekirstianachin Gon bemehonachehu.
    God Bless you all

    ReplyDelete
  13. kale hiwot yasemalen

    ReplyDelete
  14. ግሩም ነው በርቱ ተበራቱ አባቶችን መሳደብ ትታችሁ እንደዚህ አይነት መልእክት ብታስተላልፉ እኛም ከጎናችህ ነን።

    ReplyDelete