Monday, April 29, 2013

ዘሰሙነ ሕማማት




(አንድ አድርገን ሚያዚያ 21 2005 ዓ.ም)፡- ሰሙነ ሕማማት በነብዩ ኢሳያስ ‹‹ነስአ ደዌነ ወፆረ ሕማመነ ፤ በእውነት ደዌአችንን ተቀበለ፤ ሕማማችንንም ተሸከመ ፤ እኛ ግን እንደተመታ ፤ በእግዚአብሔር እንደተቀሰፈ ቆጠርነው፡፡ እርሱ ግን ስለመተላለፋችን ቆሰለ ፤ ስለበደላችን ደቀቀ ፤ የደኅንነታችንም ተግሳጽ በእርሱ ላይ ነበረ ፤ በእርሱም ቁስል እኛ ተፈወስን›› ኢሳያስ 53 ፤4 ተብሎ የተነገረው ቃል ተፈጽሞ ፤ ጌታችን ለድኅነተ ዓለም ሲል በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ የተቀበለውን ጸዋትወ መከራ የሚዘከርበት ሳምንት ነው፡፡ ከሆሳህና ማግስት እስከ ትንሳኤ ያለው የጾመ እግዚእነ መዝጊያ ሳምንት ሰሙነ ሕማማት ይባላል፡፡ 


በማኅበረ ቅዱሳን የሚታተመው የስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ ልዩ የ2004 ዓ.ም እትም ስለ ሰሙነ ሕማማት ፤ ሥርዓተ ሰሙነ ሕማማት ፤ ሃይማኖታዊና ትውፊታዊ ክንዋኔዎች በሰሙነ ሕማማት ፤ ሕማማተ እግዚእነ በልሳነ አበው ፤ በሰሙነ ሕማማት የሚነሱ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው ፤ መጽሐፈ ግብረ ሕማማት እና ፍኖተ መስቀል በሚል አብይ አርዕስቶች የተከፋፈለ ባለ 30 ገጽ ትንሽ መጽሐፍ አሳትሞ ነበር ፡፡ አንድ አድርገን ይህን መጽሐፍ በዚህ ወቅት ማግኝት ላልቻሉ በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ ለሚኖሩ ምዕመናን ወደ ፒዲፍ በመቀየር አቅርባላችኋለች ፡፡ በርካታ እውቀትን ይገኙበታል ያንብቡት…

የሳምንቱ የአንድ አድርገን ስጦታ

1 comment:

  1. Dear Andadrgen

    May GOD bless u all, Thanks for sharing such magnificent books.

    Excellent Job

    ReplyDelete