Tuesday, December 25, 2012

የዋልድባ አካባቢ እየታረሰ ነው


(አንድ አድርገን ታህሳስ 16 2004 ዓ.ም)፡- የእርቀ ሰላሙ ጉዳይ የዋልድባን ጉዳይ ወደ ኋላ እንዲል አድርጎታል ፤ ምዕመኑ “እርቀ ሰላሙ ካልቀደመ ፓትርያርክ ምርጫው መደረግ የለበትም” ሲል አባቶች ደግሞ የአራት ቁጥርና የስድስት ቁጥር ነገር አስጨንቋቸዋል ፡፡  ከቀናት በፊት ከስኳር ኮርፖሬሽን ያገኝንው የፎቶ መረጃ ቦታው ላይ ምን እየተሰራ እንደሆነ ጥሩ አመላካች ሆኖ አግኝተነዋል ፤ ይህ የምታዩት ፎቶ ከስሩ ይህ ጽሁፍ ሰፍሮበት ይገኛል  “The Gorge of Zarema River where the MayDay Dam will be in place at Wolkayite” ይላል ፡፡
ይህ ፎቶ በአካባቢው ላይ በገዳሙ የሚገኙ አባቶች ከሚናገሩት በተጨማሪ በቦታው ላይ የሚሰራው ስራ ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፡፡  በርካታ ዶዘሮች መሬቱን ሲያርሱ  በርካታ ገልባጭ መኪኖች ደግሞ እየተርመሰመሱ የሚጫንላቸውን አፈር ወደ ሌላ ቦታ በማዞር ላይ እንዳሉ ፎቶ ያሳያል፡፡ እስከ አሁን ድረስ በአካባቢው የሚሰራውን ስራ በግለሰብ ደረጃ በግልጽ በቪዲዮም ሆነ በፎቶ ማስቀረት በጣም የተከለከለ መሆኑ ይታወቃል ፤ ሰዎች ወደ ቦታው ለጸሎትም ሆነ ክብረ በአል ለማክበር ሲሄዱ ካሜራ እና ቪዲዮ ይዘው እንዲዘልቁ አይፈቀድላቸውም ፡፡ መንግሥት ግን ቦታው ከማረስ ወደ ኋላ አላለም ፤ ዋልድባ አካባቢው እንደምትመለከቱት መልክአምድሩ እየተቀየረ ይገኛል ፤ መንግስት እየሰራ ባለው ስራ ገዳማውያን የአመት ቀለባቸውን ማግኝት እየተሳናቸው ነው፡፡ እንደ ጾሙና ጸሎቱ ሁሉ ሥራን የጽድቅ መሠረት አድርገው በማኅበር የሚኖሩት ከሦስት መቶ ኀምሳ በላይ ማኅበረ ደናግሉ፤ በአሁኑ ሰዓት በሚሰራው የስኳር ልማት ፕሮጀክት አማካኝነት እና ተያያዥነት ባለቸው ጉዳዮች  ከፍተኛ ሙቀትና በሌሎችም የአካባቢ ለውጦች ሳቢያ ራሳቸውን የሚረዱባቸው የዳጉሳና የማሽላ ሰብሎቻቸው ፍሬ ሊሰጧቸው ስላልቻሉ አስቸኳይ የምግብ እና የአልባሳት እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸውም ማስታወቃቸው ይታወቃል፡፡


( አዲስ አድማስ  የዘገበው ለማንበብ ይህን ይጫኑ  የዋልድባ መነኰሳት “ኳሬዳ” በተሰኘ ትልና ምስጥ ተቸግረዋል
 


የስኳር ኮርፖሬሽን ኃላፊው አቶ አባይ ጸሀዬ በፕሮጀክቱ ተገኝተው ስራውን እንደጎበኙት

2 comments:

  1. Ato Abay: until the comes,you will continue to destroy our holy monastry until you will be destroyed! Sure, you will follow Meles and Paulos. Our God is the one who Listens and sees us. And we believe in HIM. He will do it. We do not have any hesitancy. You are atheist, like many other members of TPLF. In the name of development, you were not supposed to destroy our identity.

    ReplyDelete
  2. Let us wait for God's hand to do its miracle. Then they will stop giving hard time for our Gedamat.

    ReplyDelete