Friday, October 12, 2012

መስኪድ የሚያሰሩት ሚኒስትር

  • አቶ ጁነዲን ሳዶ በእናታቸው ግቢ በአርሲ ሁሩታ አርብ ገበያ አካባቢ መስኪድ እያሰሩ ነበር
(አንድ አድርገን ጥቅምት 2 2004 ዓ.ም)፡- ከሳምንታት በፊት “ቀይ መብራት” በሚል  ጽሁፍ በአሁኑ ሰዓት ሃይማኖትን ተገን አድርገው ስለሚሰሩ ስራዎች ትንሽ ለማስዳሰስ መሞከራችን የሚታወቅ ነው ፤ ብዙዎች ህዝብ የጣለባቸውን ሃላፊነት በአግባቡ በመወጣት ስራቸውን በአግባ የሚሰሩ ብዙ ባለስልጣኖች እንዳሉ ሁሉ በርካቶች ደግሞ ህዝብና መንግስት የጣለባቸውን ሃላፊነት ወደ ኋላ በማለት ለሚከተሉት ሃይማኖታቸው ቅድሚያ በመስጠት በርካታ ስራዎች መስራታቸው ይታወቃል ፤ ከነዚህ ሰዎች አንዱ በአሁኑ ጊዜ የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር ኃላፊ አቶ ጁነዲን ሳዶ አንዱ ናቸው ፤ አቶ ጁነዲን ሳዶ ተወልደው ያደጉበት ቀዬ በአርሲ ክፍለ ሀገር ሁሩታ አርብ ገበያ  የገጠር አካባቢ መሆኑ ይታወቃል ፤ እኝህ ሰው በስልጣን በነበሩበት በርካታ ዓመታት በአካባቢያቸው ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ ጥቂት መስኪዶችን አስገንብተዋል ፤ በቅርቡ በእናትና በአባታቸው የመኖሪያ ግቢ ውስጥ ትልቅ መስኪድ እያስገነቡ መሆናቸው ይታወቃል ፤ ይህ መስኪድ በሚሰራበት ወቅት ከዋናው የገጠር መንገድ ወደ መስኪዱ ልዩ መንገድ እንዲሰራ ከፍተኛ ግፊት ያደርጉ እንደነበር የቅርብ ሰዎች ይናገራሉ ፤ በኦህዴድ ውስጥ ስራ አስፈጻሚ በመሆን እያገለገሉ የነበሩት አቶ ጁነዲን ስልጣናቸውን ያለአግባብ በመጠቀም በቅርቡ መንግስት እርምጃ ወስዶባቸዋል ፤ ከ2 ወር በፊት የመንግስት ልዩ ሃይል እኚህ ሰው ላይና በዙሪያቸው የሚገኙ ሰዎች ላይ ባደረገው ልዩ ክትትል ወንጀል አግኝቶባቸዋል፡፡



በተገኝው መረጃ መሰረት አቶ ጁነዲን በእናታቸው  ቃል መሠረት በመኖሪያ ቤታቸው ላይ መስጅድ ለማስገንባት፣ በሚኒስትርነታቸው ሳይሆን በግለሰብ ደረጃ ለመስጅዱ ማስጨረሻ ከሳዑዲ ዓረቢያ ኤምባሲ ዕርዳታ በመጠየቃቸው፣ የመስጅዱ የመጀመሪያ ደረጃ ምርቃት ሲደረግ በኢትዮጵያ የሳዑዲ ዓረቢያ አምባሳደር ተገኝተው 500 ቅዱስ ቁርአንና 50 ሺሕ ብር ዕርዳታ መስጠታቸውን ራሳቸው አቶ ጁነዲን በጻፉት ደብዳቤ መንግስት ሊያረጋግጥ ችሏል፡፡

ከሳምንታት በፊት የአቶ ጁነዲን ባለቤት ከአንድ የአረብ ኢምባሲ በሚገቡበት ወቅት የፌደራል ፖሊስ ልዩ ኃይል ከመግቢያው በር ላይ ተበታትነው ይጠብቋው ነበር ፤ እኝህ ወ/ሮ ኢምባሲው ውስጥ ገብተው ሲወጡ በእጃቸው የተገኝው ነገር ቢኖር በርካታ የእስልምና እምነት መጽሐፍቶች ፤ በ50 ሺህ ብር እና መሰል ለሌላ አላማ የሚጠቀሙባቸው ሰነዶች ይዘው ሲወጡ በፌደራል ፖሊስ አማካኝነት እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል፤ ባለቤታቸው አምባሳደሩ የሰጡትን 50 ሺሕ ብር ለመቀበል ኤምባሲ ሄደው ተቀብለው ሲወጡ፣ ለሽብር ተግባር የሚውል ገንዘብ ተቀብለዋል በሚል ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር መዋላቸው እና ወደ እስር መውረዳቸው ይታወሳል፡፡ አቶ ጁነዲን የሚስታቸውን መታሰር በማስመልከት የተቀበሉት ብር እናት አባቶቻው መንደር ለሚሰራው መስኪድ ማስጨረሻ መሆኑን በግልጽ ተናግረዋል ፤ ይህ ማለት አቶ ጁነዲንን እና መሰል በስልጣን ላይ የተቀመጡ መንግሥትና ህዝብ የጣለባቸውን ኃላፊነታቸውን መወጣት ያቃታቸው ባለስልጣናት በእንደዚህ አይነት ተግባር ላይ ለመሰማራታቸው አብይ ምሳሌ ሆኖ ተመልክተናል ፤ ይህ መስኪድ በእምነቱ ሰዎች ቢሰራ ማንም ምንም ላይመስለው ይችል ይሆናል ፤ ነገር ግን ህዝብን እንዲያገለግል በመንግስትና በህዝብ የተመረጠ ባለስልጣን አማካኝነት መሰራት መቻል ግን አግባብ አይደለም ፤ አሁንም በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ስልጣናቸውን ተገን አድርገው ይህን መሰል ስራ የሚሰሩ ባለስልጣናት እንደሚኖሩ ይገመታል፡፡

መንግስት አክራሪነትን እዋጋለሁ ባለበት በአሁኑ ሰዓት የማይመለከታቸውን ማኅበራት ላይ እጁን ከሚጠቁምና የውሃ ወቀጣ ስራ ከሚሰራ ይልቅ ውስጡን ከእደነዚህ አይነት መሰሪ ሰዎች ቢያጸዳ መልካም ይመስለናል ፤ የኦሕዴድ ሥራ አስፈጻሚ ከመስከረም 21 ቀን እስከ መስከረም 24 ቀን 2005 .. ባካሄደው ዓመታዊ ጉባዔው ላይ፣ በሟች እናታቸው መኖሪያ ላይ እያሠሩት ካለው መስጅድ ጋር በተያያዘ የተገመገሙት ሚኒስትር ጁነዲን፣ ከፍተኛ የዲሲፕሊን ጉድለት መፈጸማቸውንና ካሉበት ኃላፊነትና ሥልጣን አኳያ ተገቢ ያልሆነ ሥራ መሥራታቸው በዋናነት እንደተገመገሙበት ታውቋ፤ በድርጅቱ ውሳኔ መሰረት ወደ ተራ አባል እንዲወርሱና እንዲያገለግሉ ተደርገዋል፡:
አቶ አሊ አብዶን የመሰለ የቀድሞ የአዲስ አበባ መስተዳደር ባለስልጣን ከተማ ከተማውን መስኪድ ሲሰሩ አቶ ጁነዲን ሳዶን የመሰሉ ባለስልጣናት ደግሞ ገጠር ገጠሩም መስኪድ በመስራት የረዥም ዓመት እቅዳቸውን ለማሳካት ሁሉም አማኝ በተቀመጠበት ወንበር የራሱን አስተዋጽኦ እያደረገ ሲያልፍ እየተመለከትን እንገኛለን፡፡   



ስድስት ኪሎ የሚገኝው የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ዳይሬክተር ዶ/ር አህመድ ሀሰን ባለቸው ሃላፊነት ምን ያህል የኢትዮጵያ እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ታሪክ  እየበረዙ  እንደሆነ ሌላ ጊዜ እንመለስበታለን 



ቸር ሰንብቱ 

4 comments:

  1. Thank you for giving us the advice.may God give us
    all a lesson to come out of the narrow circle that
    we are engaged .God has His own time of work.He is
    a second to none engineer.He shall do every thing
    good according to the evil or good or both that
    He has read from our hearts.Every one shall reap
    what he has sown.The day is approaching.Devil also
    tries his best to train servants.We childern of
    God never cease telling and exposing the truth.

    ReplyDelete
  2. መንግስት አክራሪነትን እዋጋለሁ ባለበት በአሁኑ ሰዓት የማይመለከታቸውን ማኅበራት ላይ እጁን ከሚጠቁምና የውሃ ወቀጣ ስራ ከሚሰራ ይልቅ ውስጡን ከእደነዚህ አይነት መሰሪ ሰዎች ቢያጸዳ መልካም ይመስለናል ፤

    ReplyDelete
  3. What I found really baffling is the fact this thugrae government, which born out of thugrae people whom are traditionally somehow conservative Orthodox, has been spearheading the islamization,arbaization,pentaynazation of the lands south of thugray province. Do they think this epidemic will not catch up to them right under their nose in their back yard ? What kind of 'hate' or 'idiology' would strip away their ability for logic ? Where is this thing called 'common sense' ? that good old Ethiopian common sense. It does not matter if they decided to live with Ethiopia or have their own republic in the future - the kind of reckless behavior they have been engaging since their inception would have a deadly consequences for them and the people they seems to represent and the whole region.

    ReplyDelete
  4. ይህ ብሎግ በተቻለ እስልምናንና ሀይማኖቱን የሚደግፍ ሁሉ ለመዋጋት የተመሰረተ መሆኑ ግልጽ ነውና ቀጥታ ከአቶ ጁነዲን ያልተያያዘው የመስጊዱን ጉዳይ ልትጭኑ መሞከራችሁ አስቂኝ ነው::

    ReplyDelete