Saturday, February 28, 2015

የሆሳዕና ደብረ ገነት ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን በእሳት ቃጠሎ ከፍተኛ ጉዳት ደረሰባት

(አንድ አድርገን የካቲት 21 2007 ዓ.ም)፡- በየካቲት ማርያም ቀን 2007 . በሃድያ እና ስልጤ ሃገረ ስብከት በሆሳዕና ከተማ የምትገኘውና 1901 . እንደተተከለች የሚነገርላት የ106 ዓመት ባለቤት ሆነች   የሆሳዕና ደብረ ገነት ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን በእሳት ቃጠሎ ከፍተኛ ጉዳት ደረሰባት፡፡

ይህች ቤተ ክርስቲያን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች ብቻ ሳይሆኑ ለማያምኑትም እና መናፍቅና አህዛብ ለሆኑትም የአካባቢው ሕዝቦች ጭምር ምሥክር እንደሆነች ይነገርላታል፡ የሀድያ አካባቢ ምዕመን የዕድሜ ባለፀጋ የሆኑ የብዙ አብያተ ክርቲያናት ባለቤት ነው፡፡ ሆሳዕና ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ሆሳዕና አቡነ ተክለ ሃይማኖት፣ ሆሳዕና ቅዱስ ሚካኤል፣ ሆሳዕና እግዚአብሔር ወልድ /በዓለ ወልድ/ መስመስ ቅዱስ ሚካኤል /1034 . አካባቢ እንደተተለ የሚነገርለት/ እኝህና ሌሎችንም ጨምሮ ረጅም ዓመታትን ያስቆጠሩ ቅዱሳት መካናት በአካባቢው እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡

/የጎርባቾቭ የካቲት 21 ቀን 2007 ./


1 comment: