Tuesday, December 1, 2015

በወሎ አካባቢ በድርቅ የተጎዱ አካባቢዎችን በቦታው ተገኝነተን እኛ እንዳየናቸው




(አንድ አድርገን ህዳር 21 2008 ዓ.ም )፡- በአሁኑ ሰዓት በመላ ሀገሪቱ የተከሰተውን የድርቅ አደጋ ለመቃኝት አምስት ሰዎችን ያካተተ አንድ ቡድን ወደ ደቡብ ወሎ እና ሰሜን ወሎ ወረዳዎችንና ቀበሌዎች  ቃኝተን ለመምጣት በገባነው ቃል መሰረት ላለፉት ለ12 ቀናት የቆየ ጉብኝት ከደሴ እስከ አምባሰል ፤ ከሳይንት እስከ ወግዲ ፤ ከመካነ ሰላም እስከ ወረ ባቦ ፤ ከሰጎራ እስከ አምባ ማርያም ፤ ከመጓት እስከ አባ መላ ፤ ከኢላላ እስከ ገንቦሬ ፤ ከኩታበር እስከ ደላንታ ፤ ከአቅስታ እስከ መቅደላ ፤ ከማሻ እስከ ወረኢሉ ያሉትን ወረዳ እና ቀበሌዎች በመቃኝት የችግሩ መጠንና ስፋት ምን ያህል አደጋ ሊያደርስ እንደሚችል ለማየት ሞክረናል፡፡ ጉዞው በሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡሶች ፤ በድንጋይ ገልባጭ መኪናዎች እና በእግር የተደረገ በጣም አድካሚ እና በፈተናዎች የተሞላ ሲሆን በዘመናችን የመጣውን ችግር እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ሃላፊነታችንን ለመወጣት በሃላፊነት የአቅማችንን መረጃ ለማድረቅ ከቅን መንፈስ ተነስተን ያደረግነው መሆኑን ለማስገንዘብ እንወዳለን ፡፡ በቦታዎቹ ተገኝተን ያገኝነውን መረጃ በምስል እና በድምጽ ቀርጸን ያስቀረን ሲሆን ለአንባቢያን በሚያመች መልኩ ከዛሬ ጀምሮ የምናቀርብ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን፡፡ መረጃዎቹ ከ12 ዓመት እረኛ እስከ 90 ዓመት አዛውንት ፤ ከአራስ እናት እሰከ መምህራን ፤ ከቀበሌ ሹማምንቶች እሰከ እርዳታ ማስተባበሪያ ሥራ የሚሰሩ ሰዎች በተሰበሰበ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን፡፡ በአንኳር ከምንዳስሳቸው ነጥቦች ውስጥ የሚከተሉትን ይገኙበታል

  • መንግሥት በቦታው ፍቃድ የሌላቸው ጋዜጠኞች እንዳይዘልቁ ስለሚያደርገው ጥብቅ ፍተሻ
  • ‹‹አባ ቦሩ እና ወር ጠጅ›› ነዋሪ አልባ መንደሮች
  • ድርቁን ወደ ርሃብ ሊያሸጋግር አቅም ያለው የውሃ ችግር
  • በየጊዜው ስለሚደረጉ የወረዳ ካቢኔዎች ስብሰባ
  • የሕዝቡን ችግር ያልቀረፈው የሴፍቲኔት ፕሮግራም
  • 150 ኪሎ ስንዴ ለ15አባራዎች ፤ 20 ሊትር ዘይት ለ 60 አባዎራዎች ያከፋፈለች ቀበሌ እና ርዳታውን ለመቅረጽ ስለመጡ ጋዜጠኞች
  • ችግሩን ወደ ባሰ ደረጃ ለማሸጋገር የሚጥሩ ነጋዴዎች
  • አንድ እንጀራ 8 ብር የሚሸጥበት ጎጥ
  • በ1977 ዓ.ም የተከሰተው ርሀብ መንግስት ስላደረገው ርዳታ ፤ ስለ ሰፈራ እና ሂደቱ (ሕዝቡ የተሰበሰበበት እና ስለሰፈረበት ቦታ ፤ በ Helicopter እህል የተዘረገፈበት ቦታ )
  • ውሃ ችግሩ ያፋጠጣቸው ቀበሌዎችና በውሃ ችግር ምክንያት ውሃ ወለድ በሽታ ስላጠቃት ጎጥ
  • ውሃ ችግሩ ወደ ፈረቃ እንዲያመሩ ያደረጋቸውና በአራት ቀን አንድ ጄሪካን ብቻ እንዲቀዱ የተገደዱ ቀበሌዎች
  • ለከብቶች አቅርቦት የሚሆን ውሃ ባለመኖሩ ከብቶቻውን ወደ በሽሎ ወንዝ በመውሰድ ችግሩ እስኪቃለል መዋያ ማደሪያቸውን ያደረጉ ቀበሌዎች…
  • በከፍተኛ ድርቅ የተጎዱ ቆላማ አካባቢዎች ፤ድርቁ ማኅበረሰቡ ላይ ስለፈጠረው የስነልቦና ቀውስ
  • …… ሌሎችም እዚህ ላይ ያልጠቀስናቸውን ነጥቦች በማንሳት ለአንባቢያን ያየነውን ፤ የሰማነውን ፤ በምስል ያነሳነውንና በድምጽ የቀረጽነውን መረጃ ለማድረስ እንሞክራለን፡፡
ይጠብቁን

1 comment:

  1. እናንተን እግዚአብሔር ይባርካችሁ፡፡ ከሁሉም የገረመኝ 150 ኪሎ ስንዴ ለ15አባራዎች ፤ 20 ሊትር ዘይት ለ 60 አባዎራዎች ያከፋፈለች ቀበሌ እና ርዳታውን ለመቅረጽ ስለመጡ ጋዜጠኞች ይህንን እየሰጠ ነው ብዙ ችግር የለብንም ረሀቡን ተቆጣጥረነዋል የተባለው????????????????????

    ReplyDelete