Saturday, September 24, 2011

ከፈለጋችሁ ሬሳችንን አውጡ

 

  • አቶ በጋሻው ደሳለኝ የምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም ስብከተ ወንጌል ሀላፊ ተደርጎ ተመደበ
  •  የምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም ማኅበረ መነኮሳት  ይህን ነገር እንደሰሙ ይህ ሰው እዚህ ተመድቦ አይሰራም በሚል ተቃዎሟ ቸውን አሰምተዋል
  • ’’በህብረት የሚያምፁት አንድ ላይ በመሰባሰባቸው ስለሆነ በየደብሩ አንበታትናቸው’’   የቤተክህነት ሰዎች ሴራ 
  • ስለ ቤተክርስያን አጥብቀው የሚሟገቱትን አባቶች ወደ ተለያየ ደብሮች ከቤተክህነት በወጣ ደብዳቤ የመደቧቸው ሲሆን የተመደቡት መነኮሳት ምደባውን አልተቀበሉትም፡፡ ከፈለጋችሁ ሬሳችንን አውጡ አንጂ ካደግንበትና ካገለገልንበት ከዚህ ቤተክርስትያን አንንቀሳቀስም በማለታቸው ፤ የተሰራውን ስራ እና የሚሰራውን እየተሰራ ያለውንም በመቃወማቸው የማስጠንቀቂ ደብዳቤ የተሰጣቸው ሲሆን ነገሩን ረገብ ለማድረግ ቤተ ክህነቱ በጉዳዩ ላይ እያሰበበት ይገኛል፡

    የምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም ማኅበረ መነኮሳት “የገዳሙን ት/ቤት እና ሁለገብ የአገልግሎት ሕንጻ ከገዳሙ አስተዳደር በመለየት ከወ/ሮ እጅጋየሁ በየነ ጋራ በዝብዘዋል” ያሏቸውን አስተዳዳሪውን መልአከ ሰላም ተክለ ማርያም ዘውዴን ከወራት በፊት ማባረራቸው ይታወሳል
    ጉዳዩ የደረሰበትን ደረጃ ይጠብቁን........

    እግዚሐብሔር ቤተክርስትያናችንን ይጠብቅ 

    No comments:

    Post a Comment