Sunday, April 5, 2020

ይህ ጊዜ እንዲያጥር ፀለዩ

 (አንድ አድርገን መጋቢት 27 2012 ዓ.ም )፡-  ትፈልጉኛላችሁ አታገኙኝም !!!  ማስቀደስ የማንችልበት ጊዜ እንዲያጥር ፀለዩ ፤ አብያተ ክርስቲያናት ተዘግተው የሚቆዩበት ጊዜ እንዲያጥር ፀለዩ ፤ ታቦቱን ከመንበሩ ካህኑን ከደብሩ አንዳይለይብን ፀለዩ፡፡

ቤተ መቅደስ በሌሊት ተገኝቼ ሥርዓተ ከመከታተል ይልቅ እንቅልፍ የመረጥኩበትን እነዚያን ዘመናት ሳስብ ነፍሴ በኀዘን ውስጥ ወደቀችብኝ  ዛሬ በጽኑዕ ብንፈልግ ብንናፍቅም መቅደስ ገብተን ያንን ሰማያዊ ሥርዓት እንከታተል ዘንድ የማንችልበት ዘመን ላይ ቆመናልና አቤቱ ይቅር ይለን ዘንድ ፀልዩ።
በመተላለፋችን ምክንያት አብያተ ክርስቲያናት እንዲህ ሆነው ከማየት በላይ ምን ህማም ይበልጣል? የቤተክርስቲያን ቅጥር በመነኮሳት ሳይሆን በፖሊስ ተከበው ምእመናን እንዳይደርሱ ማየትስ ቅጣት አይደለምን? ይህም ጊዜ እንዲያጥር ፀለዩ፡፡
ይህ የበደላችን፣ የመተላለፋችን የደንዳና ልባችን የማንቀላፋታችን የመራቃችን የመሠይጠናችን ውጤት ነው !!! ዛሬ የዓለም መድኃኒት መድንዓለም ክርስቶስ መጋቢት 27 በታላቅ ድምቀት የቃልኪዳኑ ታቦት ወጥቶ ይነግስ ነበረ እኛም ልጆቹ ለመባረክ መባ ጧፍ ዣንጥላ ዘቢብ እና የቤተመቅደስ ንዋይ ይዘን እንመጣ ነበረ። ዝማሬ እልልታ በካህናቱ ወረብ ውዳሴ ቅዳሴ እናሳልፍ ነበረ ነበር *** " ነበር" ኮሮና ምክንያት ሆኗል በድንገት በሮቹ እንዲህ ተዘግተዋል፡፡

ዛሬ ቅዳሴው ከውስጥ ይሰማል ካህናቱ ያለ ልጆቻቸው ይቀድሳሉ ያለ ቆራቢ ያገለግላሉ እኛ እነሱን እነሱም እኛን እንናፍቃለን በቃ አሁን መሸሸጊያና መጠለያችንን በገዛ ኃጢአታችን አጥተነዋል በሩ ተዘግቷል።

የመከራውን ጊዜ ያሳጥርልን 
#አባት ሆይ በርህን አትዝጋብን !!!


#ይናፍቃል_ለካ?



ማለዳ ተነሥቶ ነጠላን አጣፍቶ በቤቱ መገኘት

የቤተክርስቲያን ደጅ ዝቅ ብሎ መሳም በእምነት ማሻሸት
ሰዓታት ኪዳኑን በጥዑመ ዜማ በካህናት መስማት

#ይናፍቃል_ለካ ተቀብሎ ማዜም በአንድነት በኅብረት።
አሐዱ አብ ተብሎ ቅዳሴን ማስቀደስ
በፍቅር በኅብረት ተሰጥዖን መመለስ
በዕጣኑ መዐዛ በመስቀል መቀደስ
ደጀ ሰላም ገብቶ ፀበል ጸዲቅ መቅመስ

#ይናፍቃል_ለካ በካህኑ መስቀል በእጆቹ መዳሰስ።
እያወክ በድፍረት ሳታውቅም በስህተት
እግዚአብሔር ይፍታህ ለሠራኸው ኃጢአት
መባል በካህኑ ከእሥራት መፈታት

Wednesday, February 12, 2020

ጎጠኞች ቤተ ክርስቲያንን ካቆሰሏት በላይ ያቆስሏት ዘንድ ዕድል አይሰጣቸው!!


የኦሮሚያ ቤተ ክህነት አደራጅ ኮሚቴ ብሎ ራሱን የሾመው አካል በከፍተኛ የመተማመን ወይም የመቅበዝበዝ ስሜት ውስጥ ሆኖ እንደሆነ ግራ በሚገባ መልኩ አስቸኳይ የሲኖዶስ ስብሰባ መጠራቱ ከተነገረበት ጊዜ ጀምሮ እየፎከረ ነው፡፡ ቀሲስ በላይ ከአሜሪካእስኪ ውግዘቷን ይሞክሯትና እንታያያለንሲል ኃይለ ሚካኤል ደግሞ ከሀገር ቤት በተደጋጋሚ የቀጥታ ሥርጭት እየገባ ለሰኞ የተጠራውን የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤእናንተ ፖለቲከኞች ለፖለቲካችሁ ስትሉ ነው የጠራችሁት፣ ብታርፉ ይሻላል፣ ጉባኤው የጉባኤ ከለባት (የውሾች ጉባኤ) እንዲሆን አንፈልግም፣ ቄሮና ቀሪቲ ለሁሉም ነገር ራሳችሁ አዘጋጁበማለት ከወዲሁ ጉባኤውን ዘልፎ፣ ነቅፎና አውግዞ ይባስም ብሎ ውሳኔውን በአመፃ ለመመለስ የራሱን ሠራዊት አሰልፎ እየጠበቀ ይገኛል፡፡

Tuesday, February 11, 2020

ቅዱስ ሲኖዶስ ቤተ ክርስቲያን ጥቃት ላይ መኾኗን ያውጅ !

ዲያቆን አባይነህ ካሴ
(አንድ አድርገን 02/6 2012 ዓ.ም):-  ለየካቲት ቀን ፳፻፲፪ .. አስቸኳይ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ጥሪ መቅረቡን ከሲኖዶሱ ዋና ጸሐፊ ከአቡነ ዮሴፍ ከተሰጠው መግለጫ ለማወቅ ተችሏል፡፡ አስቸኳይ ጉዳይ ሲገጥም እንዲህ መፋጠን ይገባልና በአክብሮት ተቀብለነዋል፡፡ ጉባኤው ከመሰብሰብ ባሻገር ጠልቆ ይመለከታል ብለንም ተስፋ እናደርጋለን፡፡

ቅዱስ ሲኖዶስን በተመለከተ ሁሉም ኦርቶዶክሳዊ የሚግባባበት አንድ ጉዳይ አለ፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ ይወሥናል አፈጻጸሙን ግን አይመረምርም፡፡ ለዚህም ምክንያቱ እና መፍትሔው ምን እንደኾነ ብዙ ጊዜ ስንወተውት ቆይተናል፡፡ አሁንም የአስቸኳይ እና የመደበኛ ስብሰባ ሸብረብ እንጅ የወሠናቸው ጉዳዮች ከምን እንደደረሱ፣ ምን እንቅፋት እንደገጠማቸው፣ ምን ዓይነት ማረሚያ እንደሚሹ በጥሞና ለመመልከት ትዕግስቱ ሊኖረው ካልቻለ ከጉባኤው ማግሥት ታላላቆቹ አጀንዳዎቹ ሁሉ ውኃ ይበላቸዋል፡፡