Friday, August 23, 2013

ድንግልማ በእውነት ተነሥታለች

በዲ/ን ብርሃኑ አድማስ

እንኳን ለእመቤታችን በዓለ ዕርገት አደረሳችሁ፡፡

ዘሰ ይብል አፈቅረከኪ ወኢያፈቅር ተአምርኪ[ትንሣኤኪ ወዕርገትኪ] ክርስቲያናዊ፤
ኢክርስቱን ውእቱ አይሁዳዊ ወሠርፀ እስጢፋ ሐሳዊ፤
አንሰ እቤ በማኅሌተ ሰሎሞን ሰንቃዊ፤
አፈቅሮ ለፍግዕኪ ወለተ ይሁዳ ወሌዊ፤
ከመ መርዓቶ ያፈቅር ጽጌኪ መርዓዊ፡፡

(አንድ አድርገን ነሀሴ 17 2005 ዓ.ም)፡-እንደ ይሁዳ ስሙን የሚቃረን ግብር ሁልጊዜም የሚሠራውና ራሱን ‹‹ አባ ሰላማ ›› ብሎ የሚጠራው የተሐድሶዎች ብሎግ አንድ የሚያስደንቅ ጽሑፍ ሰሞኑን አስነብቦናል፡፡ የሚያስደንቅ ያልኩት ራሴን ባስደነቁኝ ሦስት ምክንያቶች ነው፡፡ የመጀመሪያው ለርእስነትና ሐሳቡን ለማስተላለፍ መሪ አድርጎ የተጠቀመው ጥቅስ መልእክቱ ከነገረ ጉዳዩ ያለውን ርቀትና አንድ ሰው ከካደ በኋላ ጥቅሶችን እስከምን ድረስ ሊያጣምም እንደሚችል ሳስብ አሁንም እደነቃለሁ፡፡ ሁለተኛ ደግሞ ክርስትና ከተመሠረተበትና በይፋ በብዙዎች ተቀባይነት እያገኘ ከመጣበት ከዘመነ ሐዋርያት ጀምሮ ብዙ የዓይን ምስክሮች አይተው ያስተላለፏቸውን ትውፊቶች ሁሉ ምን ያህል እንደሚጠሉ ሳስብ በዚያ ዘመን የነበሩ አይሁድ በአካለ ሥጋ የመመለስ እድል ገጥሟቸው ቢጠየቁ እንኳ  ‹‹ እንዴት ከእኛ በላይ ጠላችኋቸው›› ብለው የሚገረሙባቸው ስለሚመስለኝ እደነቃለሁ፡፡ ሦስተኛውና ሁልጊዜም ኢትዮጵያ ውስጥ ባሉ ተሐድሶዎች የምደነቀው ደግሞ ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብና ማኅበረ ቅዱሳን ላይ ባላቸው ጥላቻ ነው ፡፡

ሰውን መልአክ እያደረግን ሙት አመት ማሰብ አግባብም ስርዓትም አይደለም

  • አቶ መለስ ለአንድም ቀን ተሳስተው እንኳ ‹‹እኔ ከአብ ዘንድ ተልኬ መጣሁ!›› ሲሉ ተሰምቶ አይታወቅም   አናንያ ሶሪ

(አንድ አድርገን ነሀሴ 17 2005 ዓ.ም)፡- የዛሬ ዓመት በዚህ ሰዓት በፆመ ፍልሰታ ነሀሴ 9 ቀን ብጹእ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ አረፉ ፤ ነሀሴ 15 ከስድስት ቀን በኋላ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ማረፋቸውን ኢቲቪ በጠዋት ዜና አቀረበ፡፡ አሁን ሁለቱም ካለፉ አንድ አመት ሞላቸው ፤ መንግሥትም በዝግ የፓርላማ ስብሰባ የመለስ ዜናዊ ፋውንዴሽን እንዲቋቋም ወሰነ ፤ የቦርዱ ሰብሳቤዎች ወ/ሮ አዜብ መስፍንና አቶ ካሳ ተክለብርሀን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ ተደርገው በአፍሪካ ሕብረት አዳራሽ ተመረጡ ፡፡ በየተንቀሳቀሱበት የመንግሥት ፤ የግል ተቋማትና መንፈሳዊ አገልግሎት የሚሰጡ ቢሮዎች ውስጥ የመለስን ፎቶ ከአንዳድ ጥቅሶች ጋር ተሰቅለው ይመለከታሉ ፡፡ ፎቷቸውን ኢቲቪ ለበርካታ ወራት የዜናው background  አድርጎትም ተስተውሏል ፤ ኢቲቪ ልብ ገዝቶ ፎቶውን ዘወር ሲያደርግ የኦሮሚያ ቴሌቪዥን እስከ አሁን ድረስ ፎቶውን ከዜና አቅራቢው ጀርባ ላይ አለማንሳቱም ይታወቃል ፤ ሲጀመር ‹‹የአቶ መለስን አስከሬን መቀበር የለበትም በሙዚየም መቀመጥ አለበት›› የሚሉ ጥቂት ሰዎች ሃሳብ በማንሳታቸው መንግሥትም ሃሳባቸውን በመቀበል ‹‹ለማሰራት ያሰብኩት ሙዚየም ሲያልቅ አስከሬኑን በግልጽ በሙዚየም አስቀምጠዋለሁ›› የሚል አቋም መያዙ ይታወቃል ፤ አንድ ደፋር መናፍቅም ‹‹እግዚአብሔር አመላክቶኛል መለስ አልተሞተም›› እያለ ለቀናት ቤተ-መንግሥቱ በር ላይ እንደሰነበተ እንደሚያስነሳውም ሲናገር ነበር ፤ በማወቅም ባለማወቅም በየቦታው የተሰቀሉት ፎቶዎች ማኅረሰቡ ላይ የማይታይ ተጽህኖ በመፍጠራቸው ሰውየውን ከመላዕክት ከጻድቃንና ሰማዕታት ጋር በማሰለፍ እጃቸውን ወደ ላይ አድርገው ፤ በጉልበታቸውም ተንበርክከው ለፎቶ የሰገዱ ብዙዎች ነበሩ ፡፡

Sunday, August 18, 2013

የአቡነ ጳውሎስ አንደኛ ዓመት መታሰቢያ




የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን 20 ዓመታት በአምስተኛ ፓትርያርክነትና ርእሰ ሊቃነ ጳጳስነት የመሯትና አምና ያረፉት የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ አንደኛ ዓመት መታሰቢያ ነሐሴ 10 ቀን 2005 .. በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በታላቅ መንፈሳዊ ሥርዓት ሊቃነ ጳጳሳት፣ ካህናት፣ ምዕመናንና ቤተ ዘመድ በተገኙበት ታስቧል፡፡ ለቤተ ክርስቲያኒቱ  በሁሉም አቅጣጫ ያስመዘገቧቸውን የሥራ ውጤቶች የተዘከሩ ሲሆን፣ በከፊል በተጠናቀቀው የመታሰቢያ እብነ በረድ ላይም መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ተፈጽሟል፡፡ የአበባ ጉንጉንም የተለያዩ ወገኖች አስቀምጠዋል፡፡ ከረፋድ እስከ እኩለ ቀን የዘለቀውን የማሕሌት፣ የጸሎተ ፍትሐትና የቅዳሴ ሥነ ሥርዓት የመሩት አዲሱ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ናቸው፡፡  
from REporter

Thursday, August 15, 2013

‹‹ጸልዩ በእንተ ሰላመ ቤተ ክርስቲያን አሐቲ ቅድስት ጉባኤ እንተ ሐዋርያት ርትዕት በእግዚአብሔር››


 ‹‹ጸልዩ በእንተ ሰላመ ቤተ ክርስቲያን አሐቲ ቅድስት ጉባኤ እንተ ሐዋርያት ርትዕት በእግዚአብሔር›› ብለን የምንታዘዘው በመላው ዓለም ላለችው በእምነትና በጥምቀት አንድ ሆነን በቅዱስ ሥጋውና በክቡር ደሙ ተዋሕደን አንድ የክርስቶስ አካል በሚያደርገን ምሥጢር ለሚሳተፉት ሁሉ ነው፡፡ በዚህም መሠረት የአንዱ አካላችን ብልቶች የሆኑት የግብጽ ክርስቲያኖችና በዚያ ያለችው ቤተ ክርስቲያን በታላቅ መከራ መሆኗን እናስብ ፡፡ ከቀደመው ጊዜ ጀምሮ በሶርያ ያሉ ወንድሞቻችን መከራውን እንደተቀበሉ እናውቃለን፤ አሁንም በመቀበል ላይ ናቸው፡፡ ስለእነዚህ ሁሉ በእውነት ልንጸልይ ግዴታችን መሆኑን በቀኖናው የታዘዘ ቢሆንም በጸሎተ ቅዳሴያችንም ጊዜ ቢታወጅልንም ኅሊናችን እነርሱን ሁሉ እያሰበ መጸለይ ይገባል፡፡ እንገፋለን እንጂ አንወድቅም! ክርስቲያን እንደ ሚስማር ሲመቱት የሚጠብቅ ነው-እግዚአብሔር አምላክ በሶሪያ በግብጽ በኢራቅ  እና በሌሎች የዓለም አካባቢዎች በፅንፈኞች አማካኝነት እየተሰየፉ እና እየተቃጠሉ በሰማዕትነት በክብር ላረፉ ክርስቲያን ወገኖቻችን መንግሥቱን ያውርስልን!