Monday, September 5, 2011

ይቅር በሉን

ከሳምንት በፊት ‹‹ቤተክርስትያን ትዘጋ›› (http://andadirgen.blogspot.com/2011/08/blog-post_30.html) የሚል ሰላማዊ ሰልፍ August 30 2011 ሐረር መንገድ በቦርደዴ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ቤተክርስትያን ላይ አክራሪ የሚባሉ ሙስሊሞች ወጥተው ለአካባቢያቸው ወረዳ አስተዳደር ሰላማዊ ሰልፍ አድርገው መጠየቃቸውን እና መንግስት በጊዜው የወሰደውን እርምጃ በመግለፅ መዘገባችን ይታወቃል፡:

በጊዜው መንግስት ይህን ስራ የሰሩትን ሰዎች ገሚሶቹን በማፈስ ወደ እስር ቤት ያስገባቸው ሲሆን በአካባበቢው ላይ የሚገኙ የእስልምና አባቶች መፍትሄ  ለመሻት ይህን ጉዳይ በእርቅ ለመፍታት ከአካባቢው ክርስትያኖች ጋር በመነጋገር ይህን የሰሩት ሰዎች ይቅርታ እንዲሉ እና ክርስትያኖቹም ይቅር እንዲሏቸው ከአሁን በኋላ የዚህ አይነት ነገር በአካባቢያቸው እንደማይከሰት የተነጋገሩ ሲሆን የቤተክርስትያኒቱ አባቶችም ነገሩን በመመልከት ይቅር ብለዋቸው ችግሩን በመፍታት አካባቢው ላይ ሰላም ማውረድ ችለዋል፡፡ 

ሐሰት አንናገርም፤ እውነትንም አንደብቅም 
‹‹እግዚሐብሔር ቤተክርስትያንን ይጠብቅ ››

No comments:

Post a Comment