Thursday, September 8, 2011

የሐረሩ ስልጠናና ውጤቱ



  • ገበየሁ ይስማው ሥልጠናው መካሄዱን አመነ የሠልጣኖች ምልመላ ሂደትን አብራርቷል
  • የምስራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ለጉባኤ ከአዲስ አበባ ሳባኪ እንዳይጠራ ወሰነ
  • ማኅበረ ቅዱሳን በተሐድሶ ሰራዊትነት የሰለጠነ አባል የለኝም አለ
  • ከድሬዳዋ ለተሐድሶ ሰራዊትነት ሥልጠና ወደ ሐረር የተጓዙ በሀሳብ ባለመግባባት ለሦስት ተከፈሉ
    ገበየሁ ይስማው
    ገበየሁ ይስማው
በቅርቡ በሐረር ከተማ በሉተራን 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በተሐድሶ ሰራዊትነት ዙርያ የተሰጠው ሥልጠና ልዩ ልዩ ውጠየቶችን እያስከተለ እንደሆነ የምስራቅ ኢትዮጵያ የገብር ኄር መንጮች ገለጹ፡፡
ሐረር
የሐረር ከተማ እንዳንድ ምዕመናን ግብረ ተሐድሶን በተመለከተ ቅሬታቸውን እየገለጹ ነው፡፡ እነዚህ ምዕመናን ‹‹በሌሎች አህጉረ ስብከቶች የታገዱ መምህራን ለምን ሐረር ላይ እንዲያስተምሩ ይፈቀድላቸዋል? በከተማው እየተፈጸመ ባለው ግብረ ተሐድሶ ላይ ሀገረ ስብከቱ አፋጣኝ እርምጃ ለምን አይወስድም›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡


የምስራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት አስተዳደር ጉባኤ በሀገረ ስብከቱ እና በሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ያሬድ ሰባሳቢነት ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ ከመስከረም 1 ቀን 2004 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ቀን በክብረ በዓላት ወቅት በሀገረ ስብከቱ ልዩ ፈቃድ ካልሆነ በስተቀር አንድም ‹‹መምህር›› ለስብከተ ወንጌል አገልግሎት ከአዲስ አበባ እንዳይጠራ ወስኗል፡፡ በስብሰባው ‹‹ምእመናን መማር ያለባቸው በሀገረ ስብከቱ ከሚገኙ ሊቃውት መሆን አለበት፡፡ እኛ ሊቃውንቱን መድረክ ስለነሳናቸው ነው ሕገ ወጦች አውደ ምህረቱን የተቆጣጠሩት ›› የሚል ሃሳብ ተሰንዝሯል፡፡

ብጹዕ አቡነ ያሬድም በሀገረ ስብከታቸው እየተፈጸመ ያለውን ግብረ ተሐድሶ በተጠናቀረ መረጃ ለጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ እንደሚያቀርቡ ገልጸዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ የሀዋሳዎችን አሰረ ፍኖት የተከተሉ የሐረር ከተማ ትጉኀን ምእመናን በከተማችው በሀገረ ስብከታቸው እንዲሁም በምስራቅ ኢትዮጵያ ያለው የተሐድሶ ክንፍ ምን እየሠራ እንደሆነ የሚያሳይ በበቂ መረጃዎች የተደራጀ ቪሲዲ ለማሰራጨት ዝግጅታቸውን በማጠናቀቅ ላይ መሆናቸው ታውቋል፡፡ ዘለግ ላሉ ዓመታት በተሐድሶ ሴራ የተሰቃዩ የሐረር ምእመናንም ቪሲዲው የተንኮለኞችን ሴራ በማጋለጥ እፎይታ እንደሚሰጣቸው ተስፋ አድርገዋል፡፡
ድሬዳዋ
ከድሬዳዋ ለተሐድሶ ሰራዊትነት ሥልጠና ወደ ሐረር የተጓዙ ውሉደ ተሐድሶ ድርጊታቸው በመጋለጡ በሀሳብ ባለመግባባት ለሦስት ተከፍለዋል፡፡ በሦስት ሠልጣኞች ሦስት የተለያዩ ሀሳቦች ታይተዋል፡፡ የመጀመሪያው በግልጽ ወደ ሥልጠናው ሲገባ እና ሲወጣ በተቀረጸው የቪዲዮ ምስል እየታየ ለሚጠይቁት ሁሉ ‹‹እኔ ዘመድ ልጠይቅ ወደ ሩቅ ሀገር ሄጄ ነበር የማውቀው ነገር የለም፡፡ ከናካቴውም ሐረርን አላውቃትም ሔጄም አላውቅም›› በማለት ራሱን ከደሙ ንጹህ ለማድረግ ሲሞክር ታይቷል፡፡
የድሬዳዋ ተሳታፊዎች
ሁለተኛው ግለሰብ ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን በሐሰት አቀናብሮብኝ ነው እንጂ እኔ የማውቀው ጉዳይ የለም ›› በማለት እንደ ኦሪት ኃጢአተኛ በደሉን የሚሸከምለት ፍየል ለመፈለግ ሞክሯል፡፡ አክሎም ‹‹ከዛሬ ስድስት ዓመት በፊት ጀምሬ ሰዎች በእኔ ላይ ማስረጃዎችን እንደሚያሰባስቡ አውቃለሁ ተገኘ የሚባለው ነገር ፍጹም ሐሰት ነው›› በማለት ቀርበው ለጠየቁት ግለሰቦች ሲመልስ ተሰምቷል፡፡
‹የሥልጠናውን ሂደት የቀረጹት የሚያሳድዱኝም ሸዋዎች ናቸው› በማለትም ለኑፋቄው የዘረኝነት መከላከያ ጭንብል ሊያጠልቅለት ሞክሯል፡፡



የድሬዳዋው መልማይ
ከላይ የጠቀስናቸው ሁለቱ ግለሰቦች የአንድ ደብር ‹‹ሰባክያነ ወንጌል›› ሲሆኑ ቀጥለን የምንገልጸው የግብር አጋራቸው ድርጊታቸውን እንዳጋለጠባቸው ይጠረጥራሉ፡፡

ሥስተኛው ሰው ሁለቱ ወዳጆቹ የከፈቱለትን ቀጭን መውጫ ቀዳዳ በመጠቀም አንድ አካል መረጃ እንዲያጠናቅርለት ልኮት እንጂ አምኖበት ወደ ስልጠናው እንዳልሄደ ቅርብ ለሚላቸው ወዳጆቹ ተናግሯል፡፡ ጨምሮም ያሰባሰበውን መረጃ ለማኅበረ ቅዱሳን መላኩን ገልጿል፡፡በሌላ በኩል ከሰልጣኞች መካከል የማኅበረ ቅዱሳን አባል የሆነ አንድ ግለሰብ መኖሩን የተረዱ ምእመናን በማኅበረ ቅዱሳን የድሬዳዋ ማዕከልን እንዴት ከእናንተ መካከል እንዲህ ያለ ሰው ይገኛል በማለት ጠይቀዋል፡፡ ማዕከሉም እንዲህ አይነት አባል የለንም በማለት አስተባብሏል፡፡ ለማኅበሩ ቅርበት ያላቸው አስተያየት ሰጪዎች ከስድሳ ሺህ በላይ አባላት ካሉት ማኅበር እንዲህ ያለ መልስ አይጠበቅም፡፡ ማኅበሩ ሁሉንም አባላት የት እንደሚዉሉና እንደሚያድሩ በማያውቅበት ሁኔታ ድፍን ያለ መልስ ከመስጥት ተቆጥቦ የደረሰውን ጥቆማ በመቀበል ጉዳዩን በጥልቀት መርምሮ በመረጃ የተደገፈ ምሁራዊ ውሳኔ መስጠት ይኖርበታል ብለዋል፡፡

ገብር ኄር ግን የሚመለከታቸው አካላት ጉዳዩን ችላ የሚሉት ከሆነ ከአስተባባሪው ከገበየሁ ይስማው ጀምሮ በሁሉም ላይ ያሉትን ዝርዝር መረጃዎች ለምእመናን የሚያሳውቅ መሆኑን ለመግጽ ይወዳል፡፡

በተያያዘ ዜና የገብር ኄር ዜና ዘገባ እንደ ሐሩር እሳት ያቃጠለው የአሰበ ተፈሪው ገበየሁ ይስማው ‹‹ሥልጠናው እንደተባለው ኢየሱስን ማለማመድ ሳይሆን ሰባክያነ ወንጌል የዓለም ሃይማኖቶችን አንድ ለማድረግ እንዴት ማስተማር ይገባቸዋል የሚል ነበር›› ብሏል፡፡ የሠልጣኞች ምልምላን በተመለከተ ‹‹እኛ ሁሉንም ነው የጠራነው ደፍሮ የመጣውን አሠልጥነናል›› በማለት ገልጿል፡፡ ሴራው በመጋለጡ የተደናገጠው ገበየሁ ‹‹የቀረጹትንም ሆነ ፎቶ ያነሱትን እናውቃቸዋለን በመንግስት ጭምር እየተፈለጉ ነው ለሕግ እናቀርባቸዋለን›› በማለት የሐረር ምእመናን የተሐድሶን ሴራ ለማጋለጥ በሚያደርጉት ጥረት እየደረሰባት ያለውን ውርደት ለመከላከል አልሞት ባይ ተጋዳይነቱን አሳውቋል፡፡

መረጃው የደረሳቸው የምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ማቴዎስ መረጃው ጠቃሚ እንደሆነና በሀገረ ስብከታቸው የእርምት እና የጥንቃቄ እርምጃዎችን ለመውሰድ እነደሚገደዱ መናገራቸውን ምንጮች ገልጸዋል፡፡

 by ገብር ኄር      በማቴዎስ አጥምዛ (gebrher33@gmail.com) 
እግዚአብሔር ቤተክርስቲያናችንን ይጠብቅልን!!!

No comments:

Post a Comment