Wednesday, October 3, 2012

መንግሥት ሃይማኖታዊ መልዕክቶችን የሚከለክል ሕግ ለማውጣት እያሰበ ነው


(አንድ አድርገን መስከረም 23 2004 ዓ.ም)፡- ከወራት በፊት በየአብያተክርስቲያናቱ በር ላይ ማንም ሳይፈቅድላቸው የምዕመኑን ጆሮ የሚያደነቁሩ  የነጋዴዎችን ጉዳይ በማንሳት በቅርቡ ህግ እንደሚወጣላቸው “አንድ አድርገን” ላይ አንዲት ጽሁፍ መከተባችን ይታወሳል  በአሁኑ ሰዓት ይህ ጉዳይ ሌሎች ነገሮች ተጨምረውበት አዲስ ህግ ሊወጣ መሆኑን ሪፖርተር ጋዜጣ በ23/01/2004 ባወጣው እትሙ ላይ አስነብቦናል ፤ ይህ ህግ በጣም ብዙ ጠቃሚ ነገሮች እንደሚኖሩት ይታሰባል ፤ በየደብሩ ያለፍቃድ የካሴትና የሲዲዎች ሽያጮችን የሚያስቀር ይሆናል ፤ አንዳንድ ሰባኪያን በተለያየ እምነት የሚገኙ ስለሌላው እምነት በሚናገሩት ነገር ተጠያቂ የሚያደርጉ ነገሮች ይካተቱበታል ፤ እንደ ፓስተር ዳዊት ያለን ሰው የሌላውን እምነት የማያከብር ጎረምሳ የሚጠየቅበት አንቀፆች ይኖሩታል ፤ የማህበረሰቡን ሰላም ለማስጠበቅ ሲባል በየቦታው ያለፍቃድ የሚደረጉ ሃይማኖታዊ የካሴት ሽያጮች ፤ የሞንታርቦ ጩህቶችን የሚቀንስ ይሆናል ፤ በተለያዩ የመንግስት እና የህዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ውስጥ ሃይማኖታዊ ጉዳዮችን  የሚያንጸባርቁ ጥቅሶች ንግግሮች እና መሰል ነገሮች መስመር ያበጅላቸዋል ተብሏል ፤ ለማንኛውም ይህ ህግ የሚያመጣው መልካም ነገሮች እንዳሉት ሁላ ትንሽ ጫናም ሊፈጥር እንደሚችል ባለሙያዎች ይናገራሉ ፤ በአሁኑም ሰዓት የተለያዩ የእምነት ተቋማት ጋር ለማወያየት መርሀ ግብር መያዙን ሰምተናል ፤ ይህ ጉዳይ በዋናነት የፌደራል ጉዳዮችን መስሪያ ቤት እና የተለያዩ የእምነት ተቋማት ይሳተፉበታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ትልቁ ነገር አብያተክርስቲያናት የንግድ ቦታ እንዳይሆኑ ይከለክላል ፤ ቤተክርስቲያን ሳትፈቅድ ማንም በማንኛውም ጊዜ በሯ ላይ ቆሞ ንግድ ማካሄድ አይቻልም ፤ ያለፍቃድ ንግድ  ሲያካሂዱ የተገኙትን ሰዎች ከ10ሺህ ብር ጀምሮ መቀጫ ይኖረዋል ፤ ይህ የኛ ያልሆኑት ወገኖች ካሴቶቻቸውን እንደ በፊቱ ንግስን እየጠበቁና የሚያካሂዱትን ንግድ ያስቆማል ተብሎ ይጠበቃል  ፡፡


ከሪፖርተር ጋዜጣ የተገኝ (በዮናስ አብይ)
በአገሪቱ ውስጥ በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፉና ሃይማኖታዊ ግጭቶችን እየፈጠሩ ነው የሚባሉ ማናቸውም ሃይማኖታዊ መልዕክቶችን የሚያስተላልፉ ምስሎች፣ ጥቅሶች፣ ድምፅን የሚበክሉ የጐዳና ላይ ስብከቶችና መዝሙሮች፣ ከሕዝባዊ ቦታዎች የሚከለክል አዲስ ሕግ አውጥቶ በሥራ ላይ ለማዋል እየተንቀሳቀሰ መሆኑን መንግሥት አስታወቀ፡፡ ሃይማኖታዊ ጉዳዮች የሚመለከቱት የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር፣ ሃይማኖት ጥልቅና ጥንቃቄ የሚያሻው ጉዳይ በመሆኑ፣ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በጥልቀት እየመረመረው መሆኑንም ገልጿል፡፡

በፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆኑት አቶ አበበ ወርቁ በተለይ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ መንግሥት በአሁኑ ጊዜ ሃይማኖታዊ መልዕክት ያላቸውን ይዘቶች በተመለከተ፣ የአምልኮ ሥርዓት ምን መምሰል እንዳለበትና የድምፅ ብክለትን ጨምሮ የሚፈጠሩ ችግሮችን ከሕዝባዊ ቦታ እንዴት ማራቅ እንደሚቻል፣ ሕግ እንደሚያስፈልግ ከምንጊዜውም በላይ እያሰበበትና እየተዘጋጀ ነው፡፡

በማናቸውም አገልግሎት መስጫ ተቋማት እንደ ታክሲ፣ ሆቴሎች፣ ሕዝባዊ ተቋማትና አደባባዮች ላይ የሚለጠፉ ሃይማኖታዊ ነክ መልዕክቶችን፣ ሕዝብን ከሕዝብ፣ ሃይማኖትን ከሃይማኖት ሊያጋጩ የሚችሉ በኤሌክትሮኒክስ የሚተላለፉ መልዕክቶች በሙሉ በሕግ ተደንግገው የሚከለከሉበት ሥራ በመሠራት ላይ ነው፤ብለዋል አቶ አበበ፡፡

የሃይማኖት ጉዳይ ጠለቅ ያለ ነገር ስለሆነ ጠለቅ ያለ ሕግና ደንብ ያስፈልገዋል፡፡ ስለሆነም የአዋጁንና የደንቡን ይዘት እያዘጋጀን ለሚመለከታቸው አካላት እያሳየን ነው፡፡ የድምፅ ብክለትን በተመለከተ አዋጁና ደንቡ በማውጣት ሥርዓት ለማስያዝ እየተሠራ ነው፤ሲሉ አስረድተዋል፡፡

ነገር ግን እስካሁን ድረስ ቃል በቃል የሚጠቀስ ዝርዝር ይዘት ያለው ረቂቅ ሕግ ወይም አዋጅ ገና እንዳልተዘጋጀ አቶ አበበ ለሪፖርተር አስታውቀዋል፡፡

ለምሳሌ ታክሲዎችንና ሆቴሎችን ብናይ የሕዝብ ተቋማት እንደሆኑ ይታወቃል፡፡ አገልግሎታቸውም ለሁሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች መሆኑ እየታወቀ በውስጣቸው የአንድን ሃይማኖት ፍላጐት ብቻ የሚያንፀባርቁ መልዕክቶች ይተላለፍባቸዋል፡፡ እነዚህ አገልግሎቶች የሕዝብ መጠቀሚያ እንጂ የማንም ሃይማኖት ተከታይ መጠቀሚያ ብቻ መሆን የለባቸውም፡፡ በእነዚህ ቦታዎች የሚለጠፉ መልዕክቶች የአንዱን ሃይማኖት ከፍ አድርገው የሌላውን ማንኳሰስ የሚታይባቸው ነው፡፡ በመሆኑም ከፈቃድ አሰጣጥ ጀምሮ ሕዝብን ከሕዝብ ሊያጋጩ በማይችል ሁኔታ አገልግሎት እንደሚሰጡ መታሰብ አለበት፤ሲሉ አስረድተዋል፡፡

8 comments:

  1. i like it good job eprdf

    ReplyDelete
  2. It is very good idea. We know that the Ethiopian Government is very smart. It very good for our church as well as for our country but it is too bad for those who have been killing the innocent scholars of the church and shedding the pure blood of the children of the church

    ReplyDelete
  3. This may also help to avoid worship places amidest residential areas. Such places are easily acquired and converted to worship place and disturb residents. And we know which religions are accustumed to do this

    ReplyDelete

  4. what are you going to do MK? From now on, there is no buth to hide yourself. I am sure. you will pay the praize. you who many innocent scholars of church were blackmailed by you and your supporters. now you see? God never forget but sometimes He late for waiting till people stop acting their sin and returnign to Him.

    ReplyDelete
  5. in the long term or short term it will not benefit Orthodox at all.

    ReplyDelete
  6. Dear Andirgen,

    You may think the intent is to make peace and stop scoundrels like the so called "pastor Dawit" but you should understand that this is especially targeted against EOTC. This government is bent on destroying EOTC. May the Lord rid us of their vices!

    ReplyDelete
  7. they will tell us what we should believe and not believe.
    Maverick Bahetawian would have no influence at all. Well they don't anymore actually.
    Right now, we are in era of clean cut/modern theology school graduates.Right under our nose, we have witnessed the burning and destroying of many monasteries. Also the disappearing of traditional schools.
    Just like the jews did to the Catholic church, the same thing will happen to Our church. They will detect the contents of the Mezmures and teachings. The government will not protect the church but will detect and mold the church the way their bosses want it. This government, since its main agenda is to prepare Ethiopia for Global elites(their bosses); the one entity - our church, which stands against this plan have to be destroyed or re-modified. This is where this so called tehadiso crap will come in. Btw, Tahadiso is just one stage in the process of becoming pentaye. You know what, before I get carried away with my analysis; Andaregen - can you get your hands on the draft of this so called law and share it with us ? Then we can break it down line by line. However, anything that comes out of this regime is anti-Orthodox to begin with.

    ReplyDelete
  8. The generation of Ato Meles that started the social turbulence some forty years ago was chanting, rights of speech, rights for demonstration, rights for writing, rights for publishing etc. At the end of their chanting they came to power by the force of arms, dictated their terms, imposed their will and literally closed down all rights that were thriving at the time of the king. Now they are bracing to actually officially shut our mouths, lock down our tongues so we can’t praise the Lord. Ethiopia is exclusively a land of the praising of the Lord since ancient times. Foreign driven faiths or philosophies including Islam, communism, protestantism and the current democracy-chanting-monocracy, all crept into Ethiopia to disrupt her established Christianity which was an elaborately organized system for praising the Lord. These forces of foreign creed chipped away the Ethiopian established system of praise (took away the daily sacrifice) bit by bit and day by day and now, they tell us they will sweepingly forbid many forms of praise. We can’t publish, we can’t sing, we can’t display the tokens of our faith. This is exactly what was foretold by the prophets in the bible. We should submit continuous supplication to the Lord so these days of temptation and testing will be shortened.

    ReplyDelete