Tuesday, October 23, 2012

ላያቸው ተዋህዶ ፤ ውስጣቸው ተሐድሶ የሆኑ መጻህፍት




(አንድ አድርገን ጥቅምት 13 2005 ዓ.ም)፡- ባሳለፍነው ዓመት በወርሀ ግንቦት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ላይ አንድ ወሳኝ ውሳኔ መወሰኑን ይታወቃል ፤ በውሳኔውም በርካቶች የተወገዙበት ቀሪዎቹ ደግሞ መዝገባቸው በይደር እንደቆየ የምናስታውሰው ነው ፤ በጊዜው  በፕሮቴስታንቶች እየተደገፉ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ትምህርተ ሃይማኖት፣ ሥርዐተ እምነት፣ ክርስቲያናዊ ትውፊትና ታሪክ በኅቡእና በገሃድ ተደራጅተው ለማፍረስና ለማፋለስ እየተንቀሳቀሱ  ድርጅቶች ፍጹም ውግዘት የሚገባቸውን የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ እንቅስቃሴ አራማጅ ማኅበራትና ግለሰቦች በመለየት ማኅበረ ሰላማ፣ ማኅበረ በኵር፣ የምሥራች አገልግሎት፣ አንቀጸ ብርሃን፣ የቅድስት ልደታ ለማርያም መንፈሳዊ ማኅበር፣ የኢትዮጵያ መንፈሳዊ ተሐድሶ ኅብረት፣ አሸናፊ መኰንን፣ አግዛቸው ተፈራ፣ ጽጌ ስጦታው እና ግርማ በቀለ የመሰሉት ሰዎችና ላያቸው ማር የተቀቡ ውስጣቸው ግን ነጣቂ የሆኑ ተቋማት ተለይተው መለየታቸው ይታወቃል፡፡


በጊዜው የተወገዙት ሰባቱ  ድርጅቶች ውስጥ  ከሣቴ ብርሃን ፤ ማኅበረ ሰላማ ፤  የምሥራች አገልግሎት ፤ የቅድስት ልደታ ለማርያም መንፈሳዊ ማኅበር ፤  አንቀጸ ብርሃን (ከድርጅቱ ጋራ አሸናፊ መኰንንና ዳንኤል ተሾመ) ፤ የእውነት ቃል አገልግሎት ፤ ማኅበር በኵርና የኢትዮጵያ መንፈሳዊ ተሐድሶ ኅብረት ይገኙበታል ፡፡ ከእነዚህ በተጨማሪ ከተወገዙት 16 ሰዎች  የክህነትና የክብር ማዕርጋቸው ተሽሮ የበፊቱ አቶ የሚለው ስም ከተመለሰላቸው ውስጥ በግንባር ቀደምነት  አቶ አሸናፊ መኰንን ይገኝበታል፡፡

ይህ ሰው ለዘመናት ኦርቶዶክሳዊ በመምሰል የእኛ ያልሆነ ትምህርት ኑፋቄ የተቀላቀለበት መጽሃፍቶችን በመጻፍ በርካታ ብሮችን መሰብሰብ ከመቻሉም በተጨማሪ ምንፍቅናውን በበርካታ መጽሃፍቶች መዝራት ችሏል ፤ አሁን ግን ይህ ሰው ስራው ታውቆበት ከቤተክርስትያን ከተባረረም በኋላ የመጽሀፍት ነጋዴዎች በማወቅም ይሁን ባለማወቅ መጽሀፍቶቹ ከትክክለኛ መጽሀፍቶች ጋር በመደባለቅ በገበያ ላይ ይዘዋቸው  ይገኛሉ ፤ ስለዚህ ምዕመናን የዚህን ሰው ትምህርት እና መንገድ ቤተክርስትያን ስላወገዘች መጽሀፍቶቹን እና ትምህርቱን በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ከመጠቀም ወደ ኋላ እንዲሉ “አንድ አድርገን” መልዕክቷን ታተላልፋለች፡፡ ለዚህም ማስረጃ ይሆን ዘንድ መጽሀፎቹን ላያቸው ተዋህዶ ፤ ውስጣቸው ተሐድሶ የሆኑ መጻህፍት የፊት ሽፋን በመውሰድ በቀላሉ መለየት እንድትችሉ በዚህ መልክ አቅርበንላችኋል፡፡”የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውሥጣቸው ግን ነጣቂዎች ተኵላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ።” የማቴዎስ ወንጌል 7፤15

እነዚህ ሁሉ መጻህፍት በአቶ አሸናፊ የተጻፉ ናቸው ፤ ስለዚህ የምንሰማው ስብከት እና የምናነባቸው መንፈሳዊ መጻህፍት የእነማን እንደሆኑ ለይተን ማወቅ መቻል አለብን ፡፡

እነዚህ በጣም ጥቂቶች ናቸው..ሌሎቹን በሌላ ጊዜ እናቀርባለን

5 comments:

  1. ብላቴናዋ ከጀርመንOctober 23, 2012 at 8:58 AM

    ሰላም አንድ አድርገኖች እንደምን ከረማችሁ በርቱ ያቀረባችሁልን መረጃ በጣምጠቃሚና አስፈላጊም ነው የነዚህን ተኩላ ማንነት የላወቀ እንዲጠነቀቅና ለይቶም እንዲያውቃቸው መድረግ ተገቢ ነው ስራችሁን እግዚአብሄር ይባርክላችሁ አሜን!

    ReplyDelete
  2. your boss who was supposed to protect the truth but sided with the other side is not longer here. He is answering summoned from above and will answer why. It is a matter of time before you will be called as well. Don't be a false witness. If you have facts from these books bring them out and let us discuss. Don't be blinded by hate, it is the opposite of love.

    ReplyDelete
  3. Have you read one of these books? I and many people have read them. To your surprise they are very interesting and God glorifying books which have changed the lives of many including me.
    You can't stop the truth and the work of God, by any means.
    The more you oppose them, the more they are spread out.
    Do you know the book 'yikrta' has been published for the tenth time?
    Sorry and Shame on you to blame him without any evidence, just first read them and judge yourself. I am saying these to all. Please read at least one, and bring what is the mistake. Don't blame the whole blindly as Anonymous said above.
    God forgive you.

    ReplyDelete
  4. I have read yikirta and it is my favorite book of all time. It is truly life changing. I don't know what reasons you have to say this about the writer but from what i've read i can only say he is an amazing teacher.

    ReplyDelete
  5. All these are designed to expand and propagate the "purity" of the believers
    beliefs.Your findings are important to us to read them critically.we will be able to read what is in their hearts and minds. It would have been nice if you
    had pinpointed particularly the points that cannot be swallowed be the Orthodoxians.We know the intentions of the writers very well.However,the faults
    in their books on the basis of Dogma need to be exposed.

    ReplyDelete