- “ኢጣልያኖች የምኒሊክን ሐውልት ሲያወርዱ የተመለከተ አንድ ትንሽ ልጅ ጮሆ አለቀሰ፡፡ ኢጣልያኖችም ለምን እንደጮህና እንዳለቀሰ ልጁን ጠየቁት፡፡ልጁም የንጉሴን ምስል ስላወረዳችሁ ነው አላቸው፡፡ ኢጣልያኖችም ከሙሶሎኒ ሌላ ንጉስ እንደሌለ ነግረውና ገርፈው አባረሩት…” ኒውዮርክ ታይምስ የካቲት 13 ቀን 1937 ዓ.ም እትም

ቀኖና ፈረሰ ሕገ ቤተክርስትቲያን ተጣሰ በሚል ሰበብ ለ20 ዓመታት የተለያዩትና እስከ መወጋገዝ የደረሱት የቤተክርስቲያኒቱ አባቶች ወደ እርቀ ሰላም እያመሩ መሆናቸው ቢታወቅም ቤተክርስቲያኒቱን ለሁለት የከፈለው ችግር መፍትሄ የማግኝቱ ነገር አጠያያቂ እየሆነ ችግሩም እየተወሳሰበ መምጣቱ ይነገራል ፤ ለምን ? መፍትሄውስ ምንድነው?