Thursday, February 6, 2020

እነርሱ እየገደሉን እኛ አስክሬን ልንቆጥር አይገባም ፤ አሁንስ በቃችሁ…


(በዲ/ን ታደሰ ወርቁ)
(አንድ አድርገን ጥር 29 2012 ዓ.ም) ፡-  ትናንት ዳር ዳሩን ሲገድሉን የነበሩት ዛሬ ደግሞ መሐል ከተማ ገብተው ይገድሉን ጀምረዋል፡፡ ትናትም ሆነ ዛሬ እየተገደልን ያለነው በገዳዮቻችን ጥንካሬ ሳይሆን÷በእኛ ልፍስፍስነት፤በአባቶቻችን ጥብዓት አልባነት፤በመንግሥት ይሁንታነት ነው፡፡ ትዕግስታችንን እንደልምጥምጥነት፤ ጨዋነታችንን እንደፍርሐት፤የሀገራዊ አንድነትና ሰላም ጠባቂነታችንን እንደባለዕዳ እየተቆጠረብን ነው፡፡

የትናት ሌሊቱ የኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች ግድያ÷የግድያችን ሁሉ ማብቂያ ልናደርገው ይገባል፡፡ ለገዳዮቻችን ንብ በሕይወት የምትቆየው እስከትነድፍና መርዟን እስክትጨርስ ብቻ መሆኑን በተግባር ልናሰተምራቸው ይገባል፡፡ ይኼን ምዕራፍ ዘግተን ወደሌላኛው ምዕራፍ ልንሸጋገር ይገባል፡፡ከቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ጀምሮ ሁሉም ኦርቶዶክሳዊ በተግባር የምንፈተንበት ጊዜና ሰዓት ላይ ደርሰናል፡፡

የመንግሥት ይፋዊ ጦርነት‼

(በዲ/ን ብርሃኑ አድማስ)
(አንድ አድርገን ጥር 29 2012 ዓ.ም) ፡- ትናንት ሌሊት ላይ በአዲስ አበባ 24 አካባቢ በኦርቶዶክሳውያን ላይ በመንግሥት የተፈጸመው ሽብር በእጅጉ አሳዛኝ እና አሳፋሪ ነው።  ነገሩ በሌሉት የተደረገው ጉዳዩ ሕግ ለማስከበር ሳይሆን መንግሥት ከቤተ ክርስቱያናችንና ከኦርቶዶክሳዊያን ጋር ይፋዊ ጦርነት መጀመሩን ለማወጅ ይመስላል፡፡

በሕልም ዐለም ውስጥ ያሉ የሚመስሉኝ ኦርቶዶክሳውያን ምንም ያህል ቢሉለት ለእኔ እስከሚገባኝ ድረስ ይህ መንግሥት ጸረ ኦርቶዶክስ መሆኑ ግልጽ ከሆነልኝ ሰነባብቷል።  አንዳንዶቹ ባለሥልጣናት ምንም ያህል ቢያስመስሉም እውነታውን ሊደብቁት አልቻሉም።  በርግጥ ማስመሰላቸው የማይታወቅባቸው አደገኛ ጸረ ኦርቶዶክሶች እንደሚኖሩም እጠረጥራለሁ።  ነገር ግን ጌታ በወንጌል የማይገለጥ የተከደነ ነገር የለም እንዳለ ለጊዜው ነው እንጂ ሁሉም ግልጥ የሚሆንበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም። የዚያን ጊዜ ደግሞ በሰፈሩት ቁና መሰፈር የማይቀር መሆኑ የተፈጥሮ ሕግ ነው።

ወንድሞቻችንን የነጠቁን ለፓስተሩ ሲሉ ነው?


            ዲያቆን አባይነህ ካሴ
(አንድ አድርገን ጥር 29 2012 ዓ.ም) ፡- አዲስ አበባ ከተማ ቅዱስ ገብርኤል ሆስፒታል አካባቢ ቀበሌ ፳፬ ላይ የነበረው ክፍት ቦታ በመዋቅራዊ ፕላኑ መሠረት ለመናፈሻነት (Green Area) የተጠበቀ እንደነበር ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ መንግሥት ሊያለማ ቀርቶ የቆሻሻ መጣያ እና ለኗሪው የደኅንነት ስጋት እስኪኾን ድረስ ወንጀሎች ይፈጸሙበት የነበረ ቦታ መኾኑ ኗሪውን ሲያሳስበው ቆይቷል፡፡ በዚህም የተነሣ መጠነኛ የማልማት ሥራዎች ማኅበረሰቡ በራሱ ተነሣሺነት ሲያደርግበት የነበረ ቦታ ነው፡፡
 
በዚህ መካከል በቦታው ላይ ለሕዝቡ አገልግሎት ይሰጥ ዘንድ ቤተ ክርስቲያን ለመትከል ምእመናን እንቅስቃሴ ይጀምራሉ፡፡ የሚመለከተው የቤተ ክህነት መዋቅርም ጉዳዩን ዐውቆት አስፈላጊውን ድጋፍ ስላደረገ ጥያቄውን ለመንግሥት አካላት ያቀርባል፡፡ በዚህ መካከል አንድ እሽቅድምድም ይጀመራል፡፡

‹‹ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስ››



(አንድ አድርገን ጥር 29 2012 ዓ.ም) ፡- ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ጥንታዊት፣ ታሪካዊትና ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን እንደመሆኗ መጠን  ኢትዮጵያ አሁን ከደረሰችበት  የእድገት ደረጃ ከመድረሷ በፊት ብራና ዳምጣ፣ ቀለም በጥብጣና ፊደል ቀርጻ  ትምህርት ያስጀመረች፣  የፍትሕ ሥርዓቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ መዋቅራዊ አደረጃጀት ሳይኖረው ፍርድ እንዳይጓደልና ደሃ እንዳይበደል በማሰብ የፍትሐ-ነገሥት መምህራኖቿን በዳኝነት መድባ የፍትሕ ሥርዓትን የመሠረተች፣ ዜጎችን በሥነ-ምግባርና በግብረ-ገብነት ትምህርት ኮትኩታ በማሳደግ ሀገር ወዳድ ትውልድ በማፍራት መሠረት የጣለች ቤተክርስቲያን ሆና ሳለ ዛሬ ዛሬ በዘመናችን የምናየው እና የምንሰማው ነገር ‹‹ወርቅ ላበደረ ጠጠር›› በመሆኑ …...ትላንት ከሺ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምንሰማው የአብያተ ክርስቲያናት መቃጠል እና የምዕመኗ ሞት ዛሬ እጅግ በመበራከቱ ፤  ምዕመና  ስለ  አንዲት  ቅድስት  ቤተክርስቲያንን በሚመለከት ዕለት በዕለት  የሚታየዉ ፤ የወደፊት ስጋት ምን እንደኾነ ኹሉም  የእናት ቤተክርስቲያን ልጆች እንዲያውቁት የበኩላቸውንም መፍትሔ እንዲፈልጉ ሐሳብ እንዲሰጡ በክርስትናቸው የሚጠበቅባቸውን ሓላፊነት እንዲወጡ የክርስቶስን መስቀል ለመሸከም  የማይሰቀቅ ክሣደ ኅሊና አንዲኖራቸው ለስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮዋ መሳካት ፤ ለኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ህልውና መጠበቅና ለፍጹም አንድነቷ እንዲነሡ የበኩላችንን ኃላፊነት እንዲወጡ ‹አንድ አድርን›  blog ወደ ቀደመ ስራዋ  የተመለሰች መሆኗን ለማሳወቅ እወዳለን፡፡ 


Our Official Links :-

Saturday, February 9, 2019

‹‹የቤተ-ክርስቲያን ደውል ተደውሎ ቤት አልቀመጥም›› ብሎ አምልጦ በወጣ ወዲያው “ልጅሽ ሞተ› ተብሎ ተነገረኝ



(አንድ አድርገን የካቲት 03 2011 ዓ.ም )፤- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በየዓመቱ ጥር 21 የሚከበረው የአስተርእዮ ማርያም በዓት ዕለት በሱማሌ ክልል ርዕሰ ከተማ ጅግጅጋ ግጭት ተከስቶ ነበር፡፡ ከጅግ-ጅጋ ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ-ክርስቲያን ተነስተው 110 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ የምትገኝው እጅግ ጥንታዊቷ ገሪ ቆጨር ቅድስት ማርያም ቤተ-ክርስቲያን ተጉዘው መንፈሳዊ በዓሉን አክብረው በመመለስ ላይ ያሉ የጅግ-ጅጋ ከተማ ምዕመናን ‹‹ዱደሂሳን›› የሚባል ቦታ ላይ ሲደርሱ ከሱማሌ ገሪ ጎሳ የተወጣጡ ግለሰቦች “የጃርሶ ጎሳ አባላት ከመካከላችሁ አውጡ” በማለት በአራት የሕዝብ መኪናዎች ላይ የድንጋይ ናዳ ማውረድ ጀመሩ፡፡ በዚህ ጥቃት ምክንያት የአንዲት እናት ጥርስ ከመርገፍ ጀምሮ  በአራቱም መኪናዎች ላይ የሚገኙ ምዕመናኖች ላይ  ጉዳት በመድረሱ በጅግ-ጅጋ በዕለቱ ከፍተኛ ውጥረት ሊነግስ አንደቻለ በግጭቱ ዙሪያ ያነጋገርናቸው የከተማዋ ነዋሪዎች ለመረዳት ችለናል፡፡

Monday, December 31, 2018

Help the Martyrs' families - የሰማዕታቱን ቤተሰቦች እንርዳ

Click here to support

በሀገራችን ከተከሰቱ የቅርብ ጊዜያት ቀውሶች ሁሉ በዘግናኝነቱ ተወዳዳሪ የሌለው ክስተትና የጅምላ ጭፍጨፋ ባለፈው 2010 ሐምሌ ወር መጨረሻ በሀገራችን በሱማሌ ክልል በሚኖሩ "መጤ" በተባሉ ዜጎች መድረሱ ይታወቃል፡፡ በደረሰው የጅምላ ግድያና ዘረፋ በተለይም በእናቶች እና ሕጻናት ላይ ደርሶ የነበረው የጅምላ ደፈራ፣ የካህናት በቤተ መቅደሳቸው ውስጥ መታረድ፣ በድንጋይ ተወግረው መገደልና በአገልግሎት ላይ እያሉ ማቃጠል፣ የአብያተ ክርስቲያናት መውደም እንዲሁም የብዙኃን ለዘመናት ከኖሩበት ቦታ መፈናቀልና መበተን ዘመን የማይሽረው ክስተት ሆኖ አልፏል፡፡  
ከዚያ ዘግናኝ ጭፍጨፋ የተረፉትም ቢሆን በከፍተኛ የአእምሮ መታወክ ውስጥ እና በሕክምና እርዳታ ጥላ ሥር እንዳሉም ይታወቃል፡፡ "መጤ" የተባሉ ነዋሪዎች በሙሉ የዚያ ጭፍጨፋ ሰለባ እንደነበሩና ንብረታቸውም በጅምላ የወደመና የተዘረፈ እንደሆነም ይታወቃል፡፡ 

Abune Tewophilos and Emperor Haile Selassie I: Their Invaluable Contributions to the Ethiopian Orthodox Church


by Fikre Mariam Workneh

As a former celibate priest or monk, I had the privilege of serving both Abune Tewophilos and Emperor Haile Selassie I, and I would like to share my indelible memories about these two giant Ethiopians.
From left, Abune Tewophilos and Emperor Haile Selassie I.
Abune Tewophilos:
It has been nearly forty years since His Holiness Patriarch Tewophilos was murdered by the Ethiopian military/communist government in 1979. This barbaric act by the Ethiopian government against His Holiness was performed with the blessing of some members of the Orthodox Church clergy. Although many years have passed since His Holiness was strangled to death, for me it feels as though it happened just few days ago. I am still going through a profound sadness, an overwhelming sorrow and outrage about the fact that he was murdered in such an inhumane manner. No one had to die with such savagery. The Church, instead of preaching the gospel of love, mercy and forgiveness, became a collaborator to the military regime’s brutality. The Ethiopian Orthodox Church was left with an immeasurable loss of a wise leader. Those who came after him did not measure up to his intellectual caliber or vision.

Thursday, July 26, 2018

‹‹ኦርቶዶክስ ሀገር ናት ፤ በጣም ደስ ብሎኛል እንኳን ደስ አላችሁ ›› ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አሕመድ

  • ሀገራችን ካለ እናንተ ጸሎት ውጪ ሰላሟም ልማቷም ሊረጋገጥ አይችልም
  • ዛሬ በኢትዮጵያ ወገኖቻችን ላይ ተገንብቶ የኖረው የመጀመሪያው የጥላቻ ግንብ ዋንኛው ምሰሶ በይፋ ተንዷል


(አንድ አድርገን ሐምሌ 19 2010 ዓ.ም)፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አሕመድ በእርቀ ሰላም ጉባኤ ላይ የተናገሩትን እንዲህ አቅርበነዋል


‹‹በጣም ደስ ብሎኛል እንኳን ደስ አላችሁ ፤ ኢትዮጵያ ከዚች ታላቅ ቤተ ክርስቲያ ውጪ አትታሰብም ፤ እርቁ እንዲመጣ ያስፈለገበት ምክንያት ኦርቶዶክስ ሀገር ስለሆነው ነው ፤ ታላቅ ታሪክ ፣ ዝና እና ክብር ያላት ቤተክርስቲያን ናት ፤ እዚህ ሰላም ሲሆን ሁላችንም ሰላም እንሆናለን ፤ እዚህ ሰላም ሲጠፋ ደግሞ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪነት እያንዳንዳችንን ይነካናል ፤ አንድነቷ ከተጠበቀ ሌሎችን መርዳት ትችላለች ፤ የታሪክና የትውፊት ባለቤት የሆነች ቤተ ክርስቲያን ራሷ አንድነቷን በማጣቷ እሷ እያለች ሌሎች እኛን ሲያግዙን ኖረዋል ፤ የእሷ አንድነት ከምስራቅ አፍሪካ አልፎ ለአፍሪካ ትልቅ ዜና ፣ ትልቅ ብስራት እንደሆነ ይሰማኛል ፣ በተግባርም የምናየው ይሄንኑ ነው ፤ በህብረት ውስጥ የሚገኝ ትርፍ ፣ ሥምና ዝና አጥተናል ፤ ኦርቶዶክስ አንድ ሆና ቢሆን ኖሮ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ጉዳይ እርቀ ሰላም እስከ አሁን ባልዘገየ ነበር፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰው ከራሱ እንዲጣላ ፣ ከጎረቤትና ከሃይማኖቱ እንዲጣላ ፤ የሃይማኖት አባቶችን እንዳያከብር ፤ ሲገሰጽ እንዳይመከር ያደረገው አንዱ ነገር በዚች ታላቅ እና ቅድስት ቤተክርስቲያ ያጋጠመው ጸብ ነበር ማለት ይቻላል፡፡ እኛ አንድ ስንሆን ለክርስትና እምነት ብቻ ሳይሆን ለእስልምናና ኢትዮጵያ ውስጥ ላሉ ዜጎች በሙሉ ክብር ፣ አንድነትና ሰላም የሆነ ዜና መስማት እጅጉን የሚያስደስት ነገር ስለሆነ ዛሬ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናት ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ሙስሊሞችም እንኳን ደስ አላችሁ ማለት እፈልጋለሁ፡፡

Saturday, July 21, 2018

እርቀ ሰላም



( አንድ አድርገን  ሐምሌ 15 ፤ 2010 ዓ.ም ) መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል “ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም ፤ ነገር ግን  ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው ። ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል።” 

የፍቅር እጦት እንጂ ሰውም በወንድሙ ላይ በክፋትና በአመፅ አይነሳምና ቃየል አቤልን በምቀኝነትና በጥላቻ ተነሳስቶ እንደገደለው ሁሉ ዛሬም ብዙ ቃየላውያን በወንድሞቻቸው ላይ በትዕቢት እና በእብሪት ተነሳስተው የሚሞት ስጋቸውን ለመግደል ያሴራሉ። መግደል ለእነርሱ እጅግ የቀለለ ተግባር ነው፤ ቀድመው ህሊናቸውን ገድለዋልና። ማሳት ለእነርሱ እጅግ የቀለለ ተግባር ነው፤ ቀድሞ ህሊናቸውን ስተዋልና። ነገር ግን ዛሬም አሁንም በዚች ቅጽበትም በንስሃ ለተመለሰ ሁሉ ምህረት አለ። ከጥፋት መንገድ ዘወር ላለ መዳን ይሆንለታል። ነገር ግን እንደቀደመው ጊዜ በክፋትና በተንኮል ለመመላለስ ልቡን ያደነደነ፣ ፍቅርን የገፋ፣ ምህረትን የናቀ፣ ለወገኖቹ መጥፊያ ያሴረ፣ ጥላቻን ያነገበ እርቅን የጠላ ሰው ወይም ቡድን የኋላ ኋላ በታላቅ አወዳደቅ መንኮታኮቱ አይቀርም።

Wednesday, May 23, 2018

የወይንዬ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተመረቀ



(አንድ አድርገን ግንቦት 15 2010 ዓ.ም)፡- በኢትዮጵያ በረሃዎችና አውራጃዎች እየተዘዋወሩ በልዩ ልዩ አምልኮ የነበረውን ሕዝብ የክርስቶስ ወንጌለ መንግሥትን አስተምረውና አጥምቀው የክርስቶስን መንግሥት እንዲወርሱ ያደረጉት  ቅዱስ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት እግዚአብሔር በመራቸው መሠረት የሐዋርያ አሠረ ፍኖት በመከተል ዘር ልዝራ ፣ ትዳር ልያዝ ሳይሉ ታላላቅ ተዓምራትን ካከናወኑባቸው ቦታዎች  ውስጥ በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ከደብረ ብርሃን አካባቢ የሚገኝው ወይንዬ ተክለ ሃይማኖት ስፍራ አንዱ ነው፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወይን ተክለው ለ12 ዓመታት በቦታው በመቀመጥ ሲጸልዩበት የነበሩበትና በርካታ ተዓምራትን ያከናወኑበት  ፤ ጸበል አፍልቀው አህዛብን ሲያጠምቁበት የነበረውን ቦታ ያዩበታል፡፡ (በገድለ ተክለሃይማኖት ላይ ምድረ ደርደሬ ይለዋል)፡፡

ይህ ቦታ የሚገኝው ከደብረ ብርሃን ከተማ  በስተሰሜን ምዕራብ አቅጣጫ በግምት 5 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ቀጥ ባለ ገደል ተከቦ ሲሆን እዚህ ቦታ ላይ ጻድቁ አቡነ ህጻኑ ሞአ የተወለዱበትና እንደ በሬ ተጠምደው በማረስ ገድላቸውን የፈጸሙበት ታላቅ ስፍራ ይገኛል፡፡ በዚሁ ስፍራ ላይ ‹‹እስትንፋስ›› የሚባል ቦታ ከመሬት ሳያቋርጥ በሚወጣው እስትንፋስ አማካኝነት በርካቶች ከተለያዩ በሽታዎች የዳኑበትና እየዳኑ የሚገኙበት ልዩ ስፍራ ይገኛል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በቦታው ቀድሞ  ከኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ትላልቅ ገዳማት የመጡ አባቶች የሚያገለግሉበትና የሚገለገሉበት ታላቅ ቦታ  ፡፡