(በዲ/ን ታደሰ ወርቁ)
(አንድ አድርገን ጥር 29 2012 ዓ.ም) ፡- ትናንት ዳር ዳሩን ሲገድሉን የነበሩት ዛሬ ደግሞ መሐል ከተማ ገብተው ይገድሉን ጀምረዋል፡፡ ትናትም ሆነ ዛሬ እየተገደልን ያለነው በገዳዮቻችን ጥንካሬ ሳይሆን÷በእኛ ልፍስፍስነት፤በአባቶቻችን ጥብዓት አልባነት፤በመንግሥት ይሁንታነት ነው፡፡ ትዕግስታችንን እንደልምጥምጥነት፤ ጨዋነታችንን እንደፍርሐት፤የሀገራዊ አንድነትና ሰላም ጠባቂነታችንን እንደባለዕዳ እየተቆጠረብን ነው፡፡
የትናት ሌሊቱ የኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች ግድያ÷የግድያችን ሁሉ ማብቂያ ልናደርገው ይገባል፡፡ ለገዳዮቻችን ንብ በሕይወት የምትቆየው እስከትነድፍና መርዟን እስክትጨርስ ብቻ መሆኑን በተግባር ልናሰተምራቸው ይገባል፡፡ ይኼን ምዕራፍ ዘግተን ወደሌላኛው ምዕራፍ ልንሸጋገር ይገባል፡፡ከቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ጀምሮ ሁሉም ኦርቶዶክሳዊ በተግባር የምንፈተንበት ጊዜና ሰዓት ላይ ደርሰናል፡፡








