Thursday, February 6, 2020

‹‹ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስ››



(አንድ አድርገን ጥር 29 2012 ዓ.ም) ፡- ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ጥንታዊት፣ ታሪካዊትና ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን እንደመሆኗ መጠን  ኢትዮጵያ አሁን ከደረሰችበት  የእድገት ደረጃ ከመድረሷ በፊት ብራና ዳምጣ፣ ቀለም በጥብጣና ፊደል ቀርጻ  ትምህርት ያስጀመረች፣  የፍትሕ ሥርዓቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ መዋቅራዊ አደረጃጀት ሳይኖረው ፍርድ እንዳይጓደልና ደሃ እንዳይበደል በማሰብ የፍትሐ-ነገሥት መምህራኖቿን በዳኝነት መድባ የፍትሕ ሥርዓትን የመሠረተች፣ ዜጎችን በሥነ-ምግባርና በግብረ-ገብነት ትምህርት ኮትኩታ በማሳደግ ሀገር ወዳድ ትውልድ በማፍራት መሠረት የጣለች ቤተክርስቲያን ሆና ሳለ ዛሬ ዛሬ በዘመናችን የምናየው እና የምንሰማው ነገር ‹‹ወርቅ ላበደረ ጠጠር›› በመሆኑ …...ትላንት ከሺ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምንሰማው የአብያተ ክርስቲያናት መቃጠል እና የምዕመኗ ሞት ዛሬ እጅግ በመበራከቱ ፤  ምዕመና  ስለ  አንዲት  ቅድስት  ቤተክርስቲያንን በሚመለከት ዕለት በዕለት  የሚታየዉ ፤ የወደፊት ስጋት ምን እንደኾነ ኹሉም  የእናት ቤተክርስቲያን ልጆች እንዲያውቁት የበኩላቸውንም መፍትሔ እንዲፈልጉ ሐሳብ እንዲሰጡ በክርስትናቸው የሚጠበቅባቸውን ሓላፊነት እንዲወጡ የክርስቶስን መስቀል ለመሸከም  የማይሰቀቅ ክሣደ ኅሊና አንዲኖራቸው ለስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮዋ መሳካት ፤ ለኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ህልውና መጠበቅና ለፍጹም አንድነቷ እንዲነሡ የበኩላችንን ኃላፊነት እንዲወጡ ‹አንድ አድርን›  blog ወደ ቀደመ ስራዋ  የተመለሰች መሆኗን ለማሳወቅ እወዳለን፡፡ 


Our Official Links :-

No comments:

Post a Comment