(በዲ/ን ታደሰ ወርቁ)

እነዚህ ስዎች የያያዙት ሀገራዊ ስላምንና አንድነትን መጠበቅ ሳይሆን ፥ ማናጋት ነው። ምዕመኑን ነካክተው ነካክተው በእጁ የያዘውን የፍቅርና የሰማዕትነት ምልክት የሆነውን ጧፋን ፥ሀገር ወደሚያወድም እሳት እንዲለውጥ ግፊት የማድረግ የትንኮሳ ሥራ ነው። ኪዚያም መምህራችንን በማስር የማንቂያ መርሐ ግብሩን እንዲስትጓጎል በማድረግና ተጋድሏችንን ወደ" መምህራችን ይፈታነት" ለማስቅየር የተዘየደ የፖለቲካ ጫወታ መሆኑ ነው።
እንዲህ ዐይነቱ ፖሊሳዊ እብደት ለሀገራዊ ስላምና አንድነት ጠንቅ ነውና፥ መንግሥት የእርምት ርምጃ ሊወስድ ይግባል። ውዷ ቤተ ክርስቲያናችንም ከመምህር ምሕረተ አስፋ ጎን በመቆም ተቋማዊ ከለላነት ልትሰጠው ይገባል።ዛሬ በመምህራችን የተጀመረው ማዋከብ ፥ነገ ሊቃነ ጳጳሳትን ወደ ማዋከብ የማያድግበት ምክንያት የለምና፥ቅዱስ ሲኖዶስም አበክሮ ሊመክርበት ይገባል። ለእኔ ምሕረት የምሕረትን ወንጌልን ስበከ እንጁ፥ወንጀልን አልስበከም። እኔም ምሕረተ አብ ነኝ!!
No comments:
Post a Comment