Wednesday, January 25, 2023

አቡነ አብርሃም ዛሬም ታሪክ ሰሩ


“እናንተ እዚህ አራት ኪሎ ተቀምጣችሁ፤ ሌላው ቦሌ ሆኖ መንግሥት መስርቻለሁ ቢል ዝም ብላችሁ ትቀበላላችሁ፣ በሽምግልና እንፍታው ትላላችሁ?”
||| 

በዛሬው ዕለት መደበኛ የቋሚ ሲኖዶስ ስብሰባ በሚደረግበት ወቅት የመከላከያ ሚንሰቴሩ አብርሃም በላይ እና የሃይማኖት ተቋማት አባቶች ቀጠሮ ሳያስይዙ ድንገተኛ በሆነ መልኩ በመንበረ ፓትርያርክ ጽ/ቤት በመሄድ አቡነ አብርሃምን ተጭነው የሹመቱን ጉዳይ ለማሳመን እና ጉዳዩ በሽምግልና ይፈታ ብለው ቢጠይቁም ሌሎችም የቋሚ ሲኖዶስ አባላት በሽምግልና ስም የመጡትን ሃሳባቸውን ውድቅ አድርገው ዳግም በዚህ መልኩ መምጣት እንደሌለባቸው አሳስበው መልሰዋቸዋል፡፡ 

አቡነ አብረሃም፡- 
“ይሄ ጉዳይ የሃይማኖት፣ የቀኖና፣ የሥርዓተ ቤተክርስቲያን እና የህግ የበላይነት ጉዳይ ነው፡፡ ስለዚህ በእርቅ የሚፈታ አይደለም፡፡” ብለው ቁርጥ አርገው ሲናገሩ፡፡ 

ሌሎቹም ጳጳሳት ለመከላከያ ሚንስቴሩ ለአብርሃም በላይ “እናንተ እዚህ አራት ኪሎ ተቀምጣችሁ፤ ሌላው ቦሌ ሆኖ መንግሥት መስርቻለሁ ቢል ዝም ብላችሁ ትቀበላላችሁ፣ በሽምግልና እንፍታው ትላላችሁ?” ብለው ምላሽ በማሳጣት ሽምግልና የመጡትን ሁሉም በአንድ አቋም ምላሽ አሳጥተው መልሰዋቸዋል፡፡

No comments:

Post a Comment