- ኢትዮጵያ ሐዘኗን ገለፀች
የሆሳዕና በዓልን በግብፅ ሁለት ከተሞች በሚያከብሩ የኮፕት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን ላይ በደረሰው የሽብር አደጋ ኢትዮጵያ ሐዘኗን ገለፀች፡፡

የኮፕቲክ ፖፕ አቡነ ቴዎድሮስ ዳግማዊ የሆሳዕናን ሥርዓተ ቅዳሴ በመሩበት በወደቧ ከተማ እስክንድርያ፣ የቅዱስ
ማርቆስ ካቴድራል በደረሰው የአጥፍቶ ጠፊ ፍንዳታም ሦስት የፖሊስ መኰንኖችን ጨምሮ 17 ሲገደሉ 48 ቆስለዋል፡፡
በእስክንድርያ ቅዱስ ሚና ገዳም ሥርዓተ ቀብራቸው ወዳጅ ዘመድ በተገኘበት በማግስቱ ሲፈጸም አንዱ ሐዘንተኛ፣
‹‹የት ሄደን እንፀልይ? የት እናምልክ? በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ጥቃት እየፈጸሙብን ነው፡፡ እንድንፀልይ
አይፈልጉም፤ ይሁን እንጂ በደጀ ሰላማችን መጸለይ ማምለካችንን አናቋርጥም፤›› ሲል መሰማቱን የዜና ምንጮች
ዘግበዋል፡፡ በሁለቱ ከተሞች ጥቃቱን ያደረሰው ‹‹እስላማዊ መንግሥት›› በመባል የሚታወቀው ቡድን መሆኑን ራሱ ተናግሯል፡፡
አደጋውን ተከትሎ የግብፅ መንግሥት ለሦስት ወራት የሚዘልቅ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በመላ አገሪቱ አውጇል፡፡
በማስረጃነት የተያዘ፣ በግብጽ ታንታ ከተማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ውስጥ
Source:- www.ethiopianreporter.com
በማስረጃነት የተያዘ፣ በግብጽ ታንታ ከተማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ውስጥ
Source:- www.ethiopianreporter.com
No comments:
Post a Comment