Tuesday, December 18, 2012

‹‹የጳጳሱ ቅሌት›› መጽሐፍ ጸሐፊ በ‹‹የጳጳሱ ስኬት›› መጽሐፍ ይቅርታ ጠየቀ


(አንድ አድርገን ታህሳስ 8 2005 ዓ.ም)፡- የቀድሞ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በነበሩት ብጹዕ አቡነ ሳሙኤል ላይ “የጳጳሱ ቅሌት” በሚል ርእስ መጽሐፍ የጻፈውና ‹‹ተከስ ዘሪሁን›› በተባለ ኅቡእ ስም የሚታወቀው ጸሐፊ  “የጳጳሱ ስኬት” በተሰኝ ሌላ መጽሐፍ  ሊቀ ጳጳሱንና  በቀደመ መጽሐፉ ‹‹አለስማቸውና አለግብራው ተጠቅሰዋል›› ያላቸውን ግለሰቦች በመዘርዘር ይቅርታ ጠይቋል፡፡ በ‹‹ጳጳሱ ቅሌት›› መጽሐፍ ውስጥ የተገለጹት ‹‹ሳሙኤል›› ከሊቀ ጳጳሱ ብጹዕ  አቡነ ሳሙኤል ጋር በምንም መልኩ ግንኙነትየሌላቸው ናቸውያለው ጸሐፊው ‹‹ የሊቀ ጳጳሱን ስም ለማጥፋት ዘመኑን በአስተሳሰብና በተግባር በመዋጀት በሰጡት ከፍተኛ አመራር  ለቤተክርስቲያን ያበረከቱት አስተዋጽኦ ለማጠልሸት  ብሎም ቤተክርስቲያኒቱን ለመናፍቃን አሳልፎ ለመስጠት ያሴሩ ናቸው›› ባላቸው ግለሰቦች ፍላጎት በመገዛቱ መጸጸቱንና ሊቀ ጳጳሱን አቡነ ሳሙኤልን ይቅርታ እንደሚጠይቅ ገልጧል፡፡

ቀድሞ ቤተክርስቲያኒቱን ቀኖና ለማፈራረስ እና ምዕመኑን ከመናፍቃን ጋር ለመቀላቀል የረዥም ጊዜ እቅድ ነድፈው  ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የውስጥ አርበኞች መኖራቸው ይታወቃል ፤ አሁንም እንዳሉ እሙን ነው ፡፡ የያዙትን አላማ ለማስፈጸምም በርካታ ገንዘብ በመመደብ ብዙ ቅጥረኞችን በስራቸው በማሰራት የምዕመኑ እይታ ላይ ብዥታ ሲፈጥሩ ተስተውሏል ፤ በውጭ እምቢ ያላቸውን አካሄድ ወደ ውስጥ በማስረግ መድረሻቸው እስኪደርሱ ድረስ ማወካቸው ውስጥ ውስጡን መስራታቸው የማይቀር ነገር ነው ፤ ይህም ግለሰብ ራሱ እንደተናገረው “ቤተክርስቲያኒቱን ለመናፍቃን አሳልፎ ለመስጠት ያሴሩ ናቸው” ባለቸው ሰዎች ሆዳው አምላካቸው በሆኑ ሰዎች አማካኝነት ይህን የስም ማጥፋት ስራ መስራት ችሎ ነበር ፤ ወደ አእምሮው ሲመለስ የሰራው ስራ መልካም ያለመሆኑን በመገንዘብ ይቅርታ ሊጠይቅ ችሏል ፤ እኛም ቤተክርስቲያንን ለተሃድሶያውያን እና ለመናፍቃን አሳልፈን ላለመስጠት ሁላችን እንደ  ምዕመን ልንነቃ ያስፈልጋል፡፡
 ቸር ሰንብቱ

No comments:

Post a Comment