·
ሼክ መሃመድ አሊ አላሙዲን እና ቤተሰቦቻቸው
40 ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርገዋል፡፡
(አንድ አድርገን መጋቢት 7/2009 ዓ.ም )
:- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ቆሼ በተሰኘው አካባቢ መጋቢት 2 ቀን
2009 ዓ.ም ምሽት 1፡30 በደረሰ አደጋ ህይወታቸውን
ላጡ ወገኖች ከመጋት 7/2009 ዓ.ም ጀምሮ ለሰባት ቀናት የሚቆይ ጸሎተ-ፍትሐት በመላው ገዳማት እና አድባራት እንደሚደረግ ገለጸ፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ በአደጋው ለተጎዱና መጠለያ ላጡ ወገኖች የሚውል የ200 ሺህ ብር እርዳታ እንዲሰጥ
መወሰኗንም አስታውቋል፡፡የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳይ ጠቅላይ ምክር ቤትና የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት እያንዳንዳቸው ለተጎጂዎች የሚውል የ100 ሺህ ብር ድጋፍ አድርገዋል፡፡ የሚድሮክ ኢትዮጵያ እህት ኩባንያዎች እና የሚድሮክ ኢትዮጵያ ሊቀ መንበር ሼክ መሃመድ አሊ አላሙዲን እና ቤተሰቦቻቸው ለተጎዱ ወገኖች የሚውል የ40 ሚሊየን ብር ድጋፍ ሲያደርጉ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በበኩሉኩ የ5 ሚሊየን ብር ድጋፍ ማድረጉን አስታውቋል::
በተጨማሪ ኢትዮ ቴሌኮም ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች የአንድ ሚሊየን ብር ድጋፍ ሲያደርግ የኮተቤ
ሜትሮ ፖሊታን ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ሰራተኞችና መምህራን ለተጎጂ በተሰቦች የ324 ሺህ ድጋፍ አድርገዋል፡፡ እስከ ዛሬ ድረስ የሟቾች ቁጥር 113 የደረሰ ሲሆን በአደጋው ህይወታቸውን ካጡት ውስጥ 38ቱ ወንዶች ሲሆኑ፤ 75 ደግሞ ሴቶች መሆናቸው
ታውቋል ፤ የከተማዋ አስተዳደሩ የአስከሬን ፍለጋው ወደ መጠናቀቁ
እንደሚገኝ ገልጿል፡፡የከተማ አስተዳደሩ ጉዳት የደረሰባቸው ነዋሪዎቹን በዘላቂነት ለማቋቋም በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ከማስታወቁ
በተጨማሪ በአደጋው ህይወታቸውን ላጡ ሰዎች የቀብር ማስፈጸሚያ የሚውል የገንዘብ ድጋፍም አድርጓል።

ኦርቶዶክሳዊት
ቤተክርስቲያን "በደረሰው ሕልፈተ ሕይወት ለተጎዱ ቤተሰቦች እግዚአብሔር አምላክ መጽናናትና ብርታትን እንዲሰጥ፤ የሟቾችንም ነፍስ በመንግስቱ እንዲቀበል ፀሎት ይደረጋል"
ብላለች፡፡
No comments:
Post a Comment