Sunday, September 20, 2015

ጠቅላይ ቤተ ክህነት: በአራዳ ጊዮርጊስ የሕንፃዎች ግንባታ በጀት ላይ ጥያቄዎች አነሣ


  •   መመሪያያልተሰጠበትየደብሩየሚሊዮንብሮችየበጀትጥያቄእንዲዘገይአዟል 
  •  የሀገረ ስብከቱን ሥራ አስኪያጅና ምክትላቸውን እያወዛገበ ነው


  (Addis Admass ) :-  
የአራዳው መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ደብር፣ እያሠራው የሚገኘው የሁለገብ ሕንፃ ግንባታ፣ ተደርጎለታል ባለው የዲዛይን ማሻሻያ ሳቢያ በልዩነት የሚያስፈልገው ከመቶ ሚሊዮን ብር በላይ ወጪና ከባለሀብቶች ጋር በመተባበር ለማስገንባት ያቀዳቸው የሌሎች ሁለት ሕንፃዎች ግንባታና በጀት እንዲጸድቁለት ያቀረባቸው ጥያቄዎች፣ ለፓትርያርኩ ቀርበው መመሪያ ያልተሰጠባቸው በመሆናቸውበአሉበት ሁኔታ እንዲቆዩየመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት /ቤት አዘዘ፡፡

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስተዳደር ጉባኤ፣ በደብሩ ግንባታዎችና የበጀት ይጸደቅልኝ ጥያቄዎቹ ላይ ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር መጨረሻ ያሳለፋቸው ውሳኔዎች ለአፈጻጸም ወደ መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ /ቤቱ ሳይላኩለት የቆዩበት ምክንያት እንዲብራራለትም ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ከትላንት በስቲያ ለሀገረ ስብከቱ በጻፈው ደብዳቤ ጠይቋል፡፡

Friday, September 18, 2015

ጠቅላይ ቤተ ክህነት በሕግ የሚጠየቁ ሙሰኛ ኃላፊዎች በዝርዝር እንዲቀርቡለት አዘዘ



-    የተቋቋመውን ኮሚቴ ለመደለልና ለማስፈራራት ተጠርጣሪዎቹ እየሠሩ ነው
 በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማትና አድባራት፣ ቤተ ክርስቲያኒቱን ተጠቃሚ በማያደርጉ የመሬት እና የገቢ ማስገኛ ተቋማት የኪራይ ውሎች፣ የተጧጧፈ ዘረፋና ምዝበራ መፈጸሙን በጥናት ያረጋገጠው የጠቅላይ ቤተ ክህነት /ቤት÷ በጥምርና በተናጠል በሕግ ተጠያቂ የሚኾኑ የሥራ ሓላፊዎችና ሠራተኞች በስም ዝርዝር ተለይተው እንዲቀርቡለት ለአጥኚ ኮሚቴው ትእዛዝ ሰጠ፤ በመሬት፣ በሕንጻዎች፣ በሱቆች፣ በመቃብር ቦታዎች፣ በመኪና ሽልማትና በመሳሰሉት የልማት ሥራዎች ዙሪያ በቀጣይ ትኩረት ሊሰጣቸው ስለሚገቡ ነጥቦች፣ ለሀገረ ስብከቱ ጥብቅ መመሪያም አስተላልፏል።

የግብፅ ኦርቶዶክስ ፓትያርክ ከመስከረም 15 ጀምሮ ኢትዮጵያን ይጎበኛሉ




የግብፅ ኮፒት ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ቴዎድሮስ 2 ከመስከረም 15 ቀን 2008 . ጀምሮ የአምስት ቀናት የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ወደኢትዮጵያ እንደሚመጡ ታወቀ።
ፓትርያርኩ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ታሪካዊው የመስቀል በዓል ላይ የሚታደሙ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለሥልጣትን ጨምሮ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ቡድን ጋር ተገናኝተው በሁለቱ ሀገራት የጋራ ጉዳዮች ላይ ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ፓትርያርክ ቴዎድሮስ 2 መንፈሳዊና ታሪካዊ ቦታዎችንም እንደሚጎበኙ፣ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስት ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ አቡነ ማቲያስ ጋርም እንደሚመክሩ ታውቋል።
ፓትያርኩ ወደኢትዮጵያ የሚመጡት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አቡነ ማቲያስ በቀረበላቸው ግብዣ መሠረት መሆኑ ተጠቁሟል። 

Source :- http://www.sendeknewspaper.com

Sunday, September 6, 2015

ሙሰኛ ሓላፊዎች በሕግ እንዲጠየቁ የተላለፈውን ውሳኔ ቋሚ ሲኖዶሱ አጸደቀ


  • የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር፤ 900 በላይ የቤተ ክርስቲያኒቱን ልኡካን እያወያየ ነው
  • እንደ ሌላው መድረክ አታስቡት፤ ለዓላማና ለለውጥ የሚደረግ ጉባኤ ነው” /ሚኒስትሩ/

  (አዲስ አድማስ ፡- ነሐሴ 30 2007 ዓ.ም)    በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት፣ በቤተ ክርስቲያኒቱ ንብረቶች አላግባብ ሀብት ያፈሩና ለግል ጥቅማቸው ሲሉ ቤተ ክርስቲያኒቱን ለምዝበራ ያጋለጡ የአድባራት ሓላፊዎች ጉዳይ በሕግ እንዲታይ የቀረበውን ውሳኔ ቋሚ ሲኖዶስ አጸደቀ፡፡
በሙሰኛ የአድባራት ሓላፊዎች ላይ ለተላለፈው ውሳኔ መሠረት የኾነውንና 58 አድባራት የገቢ ማስገኛ ተቋማት ዙሪያ በሚታዩ የአፈጻጸም ችግሮች ላይ የተዘጋጀውን ጥናታዊ ሪፖርት ያዳመጠው ቋሚ ሲኖዶሱ፣ የመፍትሔ ሐሳቦቹንም በሙሉ ድምፅ ተቀብሎ ለጠቅላይ /ቤቱ ተጨማሪ መመሪያዎችን ሰጥቷል፡፡