- የደቀመዛሙርቱ አካዳሚክ፣ አስተዳደራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ ወደ ግለሰቦች ኃላፊነት ማስነሳት
በሚል ቅድመ ሁኔታ ተቀይሯል፡፡
- “ተቃውሞውን አስተባብረሃል” በሚል ታስሮ የነበረው ደቀመዝሙር ከእስር ትናንት ተፈትቷል፡፡
- የተሃድሶ ኑፋቄ አራማጅ የሆኑ ተማሪዎች ተቃውሞውን ኦርቶዶክሳውያንን ከኮሌጆ ቁልፍ ቦታ በማስወገድ
በመናፍቃን ለመተካት በኅቡዕ እየተንቀሳቀሱ ነው፡፡
(አንድ አድርገን
መጋቢት 19 2005 ዓ.ም)፡- የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት በኮሌጁ ስላለው የአስተዳደር ጉድለት ፣ የትምህርት
ጥራት ማነስና የምግብ አቅርቦት ጥራት መጓደል ተቃውሟቸውን በትምህርት ማቆምና የረሃብ አድማ በማድረግ እየገለጹ ነው፡፡ በርካታ
መገፋት ቤተክህነቱ እያደረሰባቸው የሚገኙት የነገረ መለኮት ምሩቃንና
ደቀ መዛሙርት ያቀረቡት ተቃውሞ የቤተክህነቱን አስተዳደረዊና መንፈሳዊ ድቀት ርቀት እንደ ማሳያ ተደርጎ ተወስዶአል፡፡
ደቀ መዛሙርቱ በኮሌጅ ቆይታቸው
ጥራቱ የተጓደለ ምግብ ፣ ፍታሃዊ ያልሆነ የውጤት ምዘና ሥርዓት ፣ የአስተማሪዎች ንቀትና ስድብ ፣ በተሃድሶ መናፍቃን ቡድን ቅሰጣና
በአስተማሪዎች የአቅም ማነስ ይማረራሉ፡፡ ከኮሌጅ ተመርቀው ሲወጡ የሚከፈላቸው ደመወዝ ለዕለት ኑሮ አለመብቃትና በጥቂት መናፍቃን
ምክንያት በምእመናን ዘንድ ለደቀ መዛሙርቱ ያለው አመለካከት የተዛባ መሆኑ ቤተክርስቲያን ከምሩቃኑ ልታገኝ የሚገባትን አገልግሎት
እንዳታገኝ እያደረጋት ነው፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ያቀረቡት የመብትና የአስተዳደራዊ ለውጥ ጥያቄ ሁሉንም የኮሌጁ ደቀ መዛሙርት ባሳተፈ
መልኩ እያቀረቡ ሲሆን ተቃውሞውን ከሚመሩት የደቀ መዛሙርት ተወካዮች (ካውንስል አመራር አባላት መካከል የተሃድሶ ኑፋቄ አራማጆች መሆናቸው ማስረጃ የቀረበባቸው)
አጋጣሚውን ተጠቅመው የኮሌጁን አስተዳደር ቁልፍ መዋቅር ኦርቶዶክሳውያንን በማስነሳት አዝማቾቻቸው በሆኑት ሁለት መምህራን ለመተካት
እንቅስቃሴ ላይ መሆናቸው ተመልክቶአል፡፡